ዕብራውያን 6 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዕብራውያን 6:1-20

1ስለዚህ ስለ ክርስቶስ የተሰጠውን የመጀመሪያ ትምህርት ትተን ወደ ብስለት እንሂድ፤ ከሞተ ሥራ ንስሓ ስለ መግባትና6፥1 ወይም ከከንቱ ሥርዐት በእግዚአብሔር ስለ ማመን እንደ ገና መሠረትን አንጣል፤ 2እንዲሁም ስለ ጥምቀቶች፣ እጆችን ስለ መጫን፣ ስለ ሙታን ትንሣኤና ስለ ዘላለም ፍርድ ትምህርት እንደ ገና አንመሥርት። 3እግዚአብሔር ቢፈቅድ ይህን እናደርጋለን።

4አንድ ጊዜ ብርሃን የበራላቸውን፣ ሰማያዊውን ስጦታ የቀመሱትን፣ ከመንፈስ ቅዱስ ተካፋዮች የሆኑትን፣ 5መልካሙን የእግዚአብሔር ቃልና የሚመጣውን ዓለም ኀይል የቀመሱትን፣ 6በኋላ ግን የካዱትን እንደ ገና ወደ ንስሓ መመለስ አይቻልም፤ ምክንያቱም እነርሱ ለገዛ ጥፋታቸው የእግዚአብሔርን ልጅ እንደ ገና ይሰቅሉታል፤ ያዋርዱታልም።

7ዘወትር በእርሷ ላይ የሚወርደውን ዝናብ የምትጠጣና ለሚያርሷትም ፍሬ የምትሰጥ መሬት ከእግዚአብሔር በረከትን ትቀበላለች። 8ነገር ግን እሾኽና አሜኬላ የምታበቅል መሬት ዋጋ ቢስ ትሆናለች፤ መረገሚያዋም ተቃርቧል፤ መጨረሻዋም በእሳት መቃጠል ነው።

9ወዳጆች ሆይ፤ ምንም እንኳ እንደዚህ ብንናገርም፣ ከድነታችሁ ጋር የተያያዘ ታላቅ ነገር እንዳላችሁ ርግጠኞች ነን። 10እግዚአብሔር ዐመፀኛ አይደለም፤ እርሱ ሥራችሁን እንዲሁም በፊትም ሆነ አሁን ቅዱሳንን በመርዳት ስለ ስሙ ያሳያችሁትን ፍቅር አይረሳም። 11የተሰጠው ተስፋ እስኪፈጸም ድረስ እያንዳንዳችሁ እንዲህ ያለውን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን። 12በእምነትና በትዕግሥት የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንድትሆኑ አንፈልግም።

የእግዚአብሔር የተስፋ ቃል ርግጠኛነት

13እግዚአብሔር ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ፣ የሚምልበት ከእርሱ የሚበልጥ ሌላ ባለመኖሩ፣ በራሱ ማለ፤ 14እንዲህም አለ፤ “በርግጥ እባርክሃለሁ፤ ዘርህንም አበዛዋለሁ።” 15አብርሃምም በትዕግሥት ከጠበቀ በኋላ የተሰጠውን ተስፋ አገኘ።

16ሰዎች ከእነርሱ በሚበልጥ ይምላሉ፤ መሐላውም የተባለውን ነገር ስለሚያጸና በመካከላቸው የተነሣው ክርክር ሁሉ ይወገዳል። 17እግዚአብሔር የማይለወጥ ዐላማውን ለተስፋው ቃል ወራሾች ግልጽ ለማድረግ ስለ ፈለገ፣ በመሐላ አጸናው። 18እግዚአብሔር ከቶ ሊዋሽ አይችልም፤ እርሱ በሁለት በማይለወጡ ነገሮች በፊታችን ያለውን ተስፋ ለመያዝ ወደ እርሱ ለሸሸን ለእኛ ብርቱ መጽናናት እንድናገኝ አድርጓል። 19እኛም የነፍስ መልሕቅ የሆነ ጽኑና አስተማማኝ ተስፋ አለን፤ ይህም ተስፋ ከመጋረጃው በስተ ጀርባ ወዳለው ውስጠኛ መቅደስ ይገባል። 20ይህም ስፍራ ኢየሱስ ስለ እኛ ቀድሞ የገባበት ነው። እርሱም እንደ መልከጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት ሆኗል።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

希伯来书 6:1-20

1所以我们要离开有关基督的初级道理,努力迈向成熟,而不是再次打基础:教导为致死的行为悔改、信靠上帝、 2各种洗礼、按手礼、死人复活、永远的审判等道理。 3上帝若许可,我们会这样做。

4有些人曾蒙上帝光照,尝过天赐恩典的滋味,有份于圣灵, 5尝过上帝之道的甘美,领悟到永世的权能, 6却背弃了真道,让他们重新悔改是不可能的。因为他们等于把上帝的儿子重新钉在十字架上,使祂再度公开受辱。 7一块经常受到雨水滋润的田地若为耕种的人长出庄稼来,就蒙上帝赐福; 8若长出来的尽是荆棘和蒺藜,就毫无价值,它会面临被咒诅的危险,最后必遭焚烧。

9亲爱的弟兄姊妹,虽然我们这样说,却深信你们的光景比这强,有得救的表现。 10因为上帝并非不公义,以致忘记你们为祂所做的工作以及你们过去和现在服侍圣徒所表现的爱心。 11愿你们各人从始至终表现出同样的殷勤,以便对所盼望的有完全的把握。 12这样,你们就不致懒散,可以效法那些凭信心和忍耐承受应许的人。

上帝的应许可靠

13当初,上帝向亚伯拉罕许下诺言的时候,因为没有比自己更大的可以凭着起誓,就凭自己起誓说: 14“我必赐福给你,使你子孙众多。” 15亚伯拉罕经过耐心的等待,得到了上帝的应许。

16人总是指着比自己更大的起誓,并用誓言作保证,了结各样的争论。 17同样,上帝为要向承受应许的人显明祂的旨意绝不更改,就用誓言向他们保证。 18上帝绝不说谎,祂将永不改变的应许和誓言给了我们,使我们这些寻找避难所、持定摆在前面之盼望的人可以大得鼓励。 19我们有这盼望作我们灵魂的锚,既安稳又可靠,一直通往圣幕里面的至圣所。 20耶稣照麦基洗德的模式成了永远的大祭司,祂替我们先进入了圣幕内。