ዕብራውያን 4 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ዕብራውያን 4:1-16

የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ

1እንግዲህ ወደ ዕረፍቱ ለመግባት የተሰጠው ተስፋ አሁንም የተጠበቀ ስለሆነ፣ ከእናንተ ማንም ለዚያ ሳይበቃ እንዳይቀር እንጠንቀቅ፤ 2ለእነዚያ እንደ ተሰበከ ለእኛም ደግሞ የምሥራቹ ቃል ተሰብኮልናልና። ነገር ግን ሰሚዎቹ ቃሉን ከእምነት ጋር ስላላዋሐዱት4፥2 ወይም ከታዘዙት ጋር ስላላመኑ አልጠቀማቸውም። 3እኛ ያመንነው ግን ወደዚያ ዕረፍት እንገባለን፤ እግዚአብሔርም፣

“ስለዚህ በቍጣዬ እንዲህ ብዬ ማልሁ፤

‘ወደ ዕረፍቴ ከቶ አይገቡም’ ” ብሏል።

ይሁን እንጂ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የእርሱ ሥራ ተከናውኗል። 4ስለ ሰባተኛውም ቀን በአንድ ስፍራ፣ “በሰባተኛውም ቀን እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ ዐረፈ” ብሏልና።

5ቀደም ባለው ክፍል ደግሞ፣

“ወደ ዕረፍቴ ከቶ አይገቡም” ይላል።

6ወደ ዕረፍቱ ገና የሚገቡ አንዳንዶች አሉ፤ ቀድሞ የምሥራቹ ቃል የተሰበከላቸው ባለመታዘዛቸው ምክንያት ወደ ዕረፍት አልገቡም። 7ስለዚህ እግዚአብሔር፣ “ዛሬ” ብሎ እንደ ገና አንድን ቀን ወሰነ፤ ይህም ከብዙ ዘመን በኋላ በዳዊት በኩል፣

“ዛሬ ድምፁን ብትሰሙ፣

ልባችሁን አታደንድኑ”

ተብሎ ቀደም ሲል እንደ ተነገረው ነው።

8ኢያሱ ዕረፍትን ሰጥቷቸው ቢሆን ኖሮ፣ ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር ስለ ሌላ ቀን ባልተናገረ ነበር። 9ስለዚህ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ገና ቀርቶለታል፤ 10ምክንያቱም ወደ እግዚአብሔር ዕረፍት የሚገባ ሁሉ፣ እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ፣ እርሱም ደግሞ ከሥራው ያርፋል። 11እንግዲህ ማንም የእነዚያን አለመታዘዝ ምሳሌ ተከትሎ እንዳይወድቅ፣ ወደዚያ ዕረፍት ለመግባት እንትጋ።

12የእግዚአብሔር ቃል ሕያውና የሚሠራ ነውና፤ በሁለት በኩል ስለት ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፤ ነፍስንና መንፈስን፣ ጅማትንና ቅልጥምን እስኪለያይ ድረስ ዘልቆ ይወጋል፤ የልብንም ሐሳብና ምኞት ይመረምራል። 13ከእግዚአብሔር ዐይን የተሰወረ ምንም ፍጥረት የለም፤ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት በሚገባን በእርሱ ፊት ሁሉም ነገር የተራቈተና የተገለጠ ነው።

ታላቁ ሊቀ ካህናት ኢየሱስ

14እንግዲህ ወደ ሰማያት ያረገ4፥14 ወይም ወደ ሰማይ የሄደ ታላቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፣ እምነታችንን አጥብቀን እንያዝ። 15በድካማችን የማይራራልን ሊቀ ካህናት የለንምና፤ ነገር ግን እንደ እኛ በማንኛውም ነገር የተፈተነ ሊቀ ካህናት አለን፤ ይሁን እንጂ ምንም ኀጢአት አልሠራም። 16እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበልና በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ፣ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

האיגרת אל-העברים 4:1-16

1הבטחת אלוהים, שמאפשרת לכל אדם להיכנס אל מקום מנוחתו, עדיין בתוקף, אך עלינו להיזהר פן נחמיץ את ההזדמנות להיכנס אל מנוחתו זאת. 2כי בשורת אלוהים שמודיעה לנו על ישועתו נמסרה גם לבני־ישראל, בימי משה, אך היא לא הועילה לבני־ישראל משום שלא האמינו בה. 3הכתוב אומר שרק המאמינים והבוטחים באלוהים – ואנחנו ביניהם – יכולים לבוא אל מקום מנוחתו. אלוהים נשבע כי אלה שאינם מאמינים בו לא יבואו לעולם אל מקום מנוחתו. אל תחשבו, חלילה, שמקום מנוחתו לא היה מוכן בזמנו! מקום מנוחתו היה מוכן מאז בריאת העולם, 4כפי שכתוב בבראשית: ”וישבות ביום השביעי מכל מלאכתו“. 5אף־על־פי־כן לא באו בני־ישראל אל מנוחתו, כי אלוהים אמר: ”הם לא יבואו אל מנוחתי“. 6אך הבטחת אלוהים עדיין בתוקף, ויש הבאים אל מנוחתו – אך לא אלה שהחמיצו את ההזדמנות הראשונה, שכן הימרו את פי ה׳.

7משום כך קבע אלוהים מועד נוסף שמאפשר לבוא אל מנוחתו: היום! שנים רבות לאחר הזמנתו הראשונה הודיע לנו אלוהים על מועד נוסף זה באמצעות דוד המלך, אשר אמר: ”היום אם בקולו תשמעו, אל תקשו לבבכם!“

8אילו מקום מנוחתו של אלוהים היה ארץ־ישראל, הוא לא היה קובע מועד נוסף שמאפשר לבוא אל מנוחתו, שהרי יהושע כבר הביא את בני־ישראל אל ארץ־ישראל. 9לפיכך, לעם־אלוהים עדיין צפויה מנוחה שלמה. 10כי מי שנכנס אל מנוחת אלוהים שובת מכל מעשה ומכל מלאכה, כשם שאלוהים שבת מכל מלאכתו לאחר שסיים את בריאת העולם.

11הבה נשתדל כמיטב יכולתנו להיכנס אל מקום מנוחתו של אלוהים, כדי שאיש מאיתנו לא ייכשל ולא ימרה את פי אלוהים, כפי שעשו בני־ישראל. 12כי דבר־אלוהים מלא כוח וחיים, חד מחרב פיפיות, חודר למעמקי מחשבותינו ותשוקותינו, ומגלה את מזימותינו ומניעינו. 13כן, אלוהים יודע הכול על כולם בכל מקום. כל מעשינו ומזימותינו גלויים וחשופים לעיני אלוהים, ועלינו למסור לו דין וחשבון על התנהגותנו.

14אך היות שיש לנו כהן גדול, ישוע בן־האלוהים, אשר עלה לשמים כדי לעזור לנו, לעולם אל נחדל לבטוח בו! 15הכהן הגדול שלנו מבין את חולשותינו, שכן הוא עצמו התנסה כמונו באותם פיתויים, אך הוא לא חטא מעולם. 16משום כך, הבה נתקרב בביטחון לכסא אלוהים, כדי שיעניק לנו את חסדו ורחמיו אשר יעזרו לנו בעת הצורך.