ኤፌሶን 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤፌሶን 5:1-33

1እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን ምሰሉ፤ 2ክርስቶስ እንደ ወደደን ራሱንም ስለ እኛ መልካም መዐዛ ያለው መባና መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር እንደ ሰጠ እናንተም በፍቅር ተመላለሱ።

3ማንኛውም የዝሙት ወይም የርኩሰት ወይም የሥሥት ነገር ከቶ በመካከላችሁ አይነሣ፤ ይህ ቅዱስ ለሆነው ለእግዚአብሔር ሕዝብ አይገባምና። 4የሚያሳፍርና ተራ የሆነ ንግግር፣ ዋዛ ፈዛዛም ለእናንተ ስለማይገባ በመካከላችሁ አይኑር፤ ይልቁንስ የምታመሰግኑ ሁኑ። 5ደግሞም ይህን ዕወቁ፤ ማንም አመንዝራ ወይም ርኩስ ወይም ስግብግብ፣ ይኸውም ጣዖት አምላኪ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት5፥5 ወይም የክርስቶስና የእግዚአብሔር መንግሥት በሆነው ርስት የለውም። 6ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ የሚመጣው በእንደዚህ ዐይነት ነገር ነው። 7ስለዚህ እንዲህ ካሉ ጋር አትተባበሩ።

8ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ፤ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ። እንደ ብርሃን ልጆች ኑሩ፤ 9የብርሃኑ ፍሬ በበጎነት፣ በጽድቅና በእውነት ሁሉ ዘንድ ነውና። 10እንዲሁም ጌታን ደስ የሚያሰኘውን ፈልጉ። 11ፍሬ ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር ምንም ዐይነት ግንኙነት አይኑራችሁ፤ ይልቁን ግለጡት፤ 12በድብቅ የሚሠሩትን ነገር መናገር ራሱ አሳፋሪ ነውና። 13ብርሃን የበራበት ነገር ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤ 14ምክንያቱም ሁሉን ነገር እንዲታይ የሚያደርገው ብርሃን ነውና፤ ስለዚህም፣

“አንተ የተኛህ ንቃ፤

ከሙታን ተነሣ፤

ክርስቶስም ያበራልሃል” ተብሏል።

15እንግዲህ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንደ ጥበበኞች እንዴት እንደምትኖሩ ተጠንቀቁ። 16ቀኖቹ ክፉ ናቸውና ዘመኑን በሚገባ ዋጁ። 17ስለዚህ ሞኞች አትሁኑ፤ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ። 18በመንፈስ ተሞሉ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ ብክነት ነውና። 19በመዝሙርና በውዳሴ፣ በመንፈሳዊም ዝማሬ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ በልባችሁ ለጌታ ተቀኙ፤ አዚሙም። 20በዚህም እግዚአብሔር አብን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ሁሉ ነገር ሁልጊዜ አመስግኑ።

21ለክርስቶስ ካላችሁ አክብሮታዊ ፍርሀት የተነሣ አንዳችሁ ለአንዳችሁ ተገዙ።

ባልና ሚስት

5፥22–6፥9 ተጓ ምብ – ቈላ 3፥18–4፥1

22ሚስቶች ሆይ፤ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁም ተገዙ 23ክርስቶስ፣ አካሉ ለሆነችውና አዳኟ ለሆናት ቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ ሁሉ፣ ባልም የሚስቱ ራስ ነውና። 24እንግዲህ ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ፣ ሚስቶችም ለባሎቻቸው በማንኛውም ነገር እንደዚሁ መገዛት ይገባቸዋል።

25ባሎች ሆይ፤ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳትና ራሱንም ስለ እርሷ አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ እናንተም ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ 26በቃሉ አማካይነት በውሃ ዐጥቦ በማንጻት እንድትቀደስ፣ 27እንዲሁም ጕድፍ ወይም የፊት መጨማደድ ወይም አንዳች እንከን ሳይገኝባት ቅድስትና ነውር አልባ የሆነች ክብርት ቤተ ክርስቲያን አድርጎ ለራሱ ሊያቀርባት ነው። 28ባሎችም እንደዚሁ ሚስቶቻቸውን እንደ ገዛ ሥጋቸው መውደድ ይገባቸዋል። ሚስቱን የሚወድድ ራሱን ይወድዳል። 29የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ማንም የለም፤ ይመግበዋል፤ ይንከባከበዋል፤ ክርስቶስም ለቤተ ክርስቲያን ያደረገው ልክ እንደዚሁ ነው፤ 30እኛ የክርስቶስ አካል ብልቶች ነንና። 31“ስለዚህም ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ ከሚስቱም ጋር አንድ ይሆናል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ”። 32ይህ ጥልቅ ምስጢር ነው፤ እኔም ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እናገራለሁ። 33ሆኖም ከእናንተ እያንዳንዱ ሚስቱን እንደ ራሱ አድርጎ ይውደድ፤ ሚስትም ባሏን ታክብር።

Thai New Contemporary Bible

เอเฟซัส 5:1-33

1เพราะฉะนั้นท่านทั้งหลายจงเลียนแบบพระเจ้าให้สมกับเป็นบุตรที่รัก 2และจงดำเนินชีวิตในความรักเหมือนที่พระคริสต์ทรงรักเราทั้งหลาย และประทานพระองค์เองเพื่อเราเป็นเหมือนของถวายอันมีกลิ่นหอมและเครื่องบูชาแด่พระเจ้า

3แต่อย่าเอ่ยถึงสิ่งที่ส่อถึงการผิดศีลธรรมทางเพศและความไม่บริสุทธิ์ใดๆ หรือความโลภในหมู่ท่านทั้งหลาย เพราะเป็นสิ่งไม่เหมาะสมสำหรับประชากรบริสุทธิ์ของพระเจ้า 4ทั้งอย่าพูดหยาบโลนลามก เฮฮาไร้สาระ หรือตลกหยาบช้า ซึ่งไม่สมควร แต่ให้ขอบพระคุณพระเจ้าดีกว่า 5ท่านแน่ใจได้เลยว่าคนผิดศีลธรรม คนไม่บริสุทธิ์ หรือคนโลภ คนเช่นนี้เป็นผู้กราบไหว้รูปเคารพ เขาจะไม่ได้รับมรดกใดๆ ในอาณาจักรของพระคริสต์และของพระเจ้า5:5 หรือพระคริสต์และพระเจ้า 6อย่าให้ผู้ใดล่อลวงท่านด้วยวาจาไร้สาระ เพราะเนื่องด้วยสิ่งเหล่านั้นพระพิโรธของพระเจ้าจึงมาถึงบรรดาผู้ที่ไม่เชื่อฟัง 7ฉะนั้นอย่าเป็นหุ้นส่วนกับคนเหล่านั้นเลย

8เพราะเมื่อก่อนท่านเป็นความมืด แต่เดี๋ยวนี้ท่านเป็นความสว่างในองค์พระผู้เป็นเจ้า จงดำเนินชีวิตอย่างลูกของความสว่าง 9(เพราะผลของความสว่างประกอบด้วยความดีทั้งปวง ความชอบธรรมทั้งมวลและความจริงทั้งสิ้น) 10จงหาให้พบว่าอะไรเป็นที่ชอบพระทัยองค์พระผู้เป็นเจ้า 11อย่าเข้าส่วนใดๆ กับกิจกรรมของความมืดอันไร้ผล แต่จงเปิดเผยการเหล่านั้นดีกว่า 12เพราะเพียงเอ่ยถึงสิ่งซึ่งพวกที่ไม่ยอมเชื่อฟังแอบทำกันนั้นก็ยังน่าอาย 13แต่ทุกสิ่งที่ถูกเปิดเผยโดยความสว่างก็เห็นกันแจ่มแจ้ง 14เนื่องจากความสว่างทำให้เห็นทุกสิ่งชัดแจ้ง ด้วยเหตุนี้จึงกล่าวกันว่า

“โอ ผู้ที่หลับอยู่ จงตื่นขึ้น

จงฟื้นขึ้นจากความตาย

และพระคริสต์จะทรงส่องสว่างแก่ท่าน”

15เพราะฉะนั้นท่านจงระมัดระวังในการดำเนินชีวิต อย่าดำเนินชีวิตแบบคนไร้ปัญญา แต่จงดำเนินชีวิตแบบคนมีปัญญา 16จงรู้จักใช้ทุกโอกาสเพราะเวลานี้เป็นยุคอันเลวร้าย 17ฉะนั้นจงอย่าโง่เขลา แต่จงเข้าใจพระประสงค์ขององค์พระผู้เป็นเจ้าว่าเป็นเช่นใด 18และอย่าเมาเหล้าองุ่นซึ่งจะทำให้เสียคน แต่จงเปี่ยมด้วยพระวิญญาณ 19จงสนทนากันด้วยเพลงสดุดี เพลงสรรเสริญและบทเพลงฝ่ายจิตวิญญาณ จงร้องและบรรเลงเพลงในใจถวายองค์พระผู้เป็นเจ้า 20จงขอบพระคุณพระเจ้าพระบิดาสำหรับทุกสิ่งอยู่เสมอในพระนามขององค์พระเยซูคริสต์เจ้าของเรา

21จงยอมเชื่อฟังกันและกันเนื่องด้วยใจเคารพยำเกรงพระคริสต์

สามีภรรยา

(คส.3:18—4:1)

22ผู้ที่เป็นภรรยาจงยอมเชื่อฟังสามีเหมือนที่ยอมเชื่อฟังองค์พระผู้เป็นเจ้า 23เพราะสามีเป็นศีรษะของภรรยา เหมือนพระคริสต์ทรงเป็นศีรษะของคริสตจักรซึ่งเป็นพระกายของพระองค์ ทั้งพระองค์ยังทรงเป็นพระผู้ช่วยให้รอดของคริสตจักรด้วย 24คริสตจักรยอมเชื่อฟังพระคริสต์อย่างไร ภรรยาก็ควรยอมเชื่อฟังสามีทุกเรื่องอย่างนั้น

25ผู้ที่เป็นสามีจงรักภรรยาของตนเช่นเดียวกับที่พระคริสต์ทรงรักคริสตจักร และประทานพระองค์เองแก่คริสตจักร 26เพื่อทรงทำให้คริสตจักรบริสุทธิ์โดยการชำระ5:26 หรือได้ชำระด้วยน้ำผ่านทางพระวจนะ 27และเพื่อพระองค์จะได้มีคริสตจักรอันงามผ่องแผ้วปราศจากมลทินหรือริ้วรอยหรือตำหนิใดๆ แต่บริสุทธิ์และไม่มีที่ติ 28เช่นนั้นแหละสามีจึงควรรักภรรยาของตนเหมือนรักกายของตนเอง ผู้ที่รักภรรยาก็รักตนเอง 29ท้ายที่สุดไม่มีใครเกลียดชังกายของตนเอง มีแต่เลี้ยงดูทะนุถนอมเหมือนที่พระคริสต์ทรงกระทำแก่คริสตจักร 30เพราะเราทั้งหลายเป็นอวัยวะในพระกายพระองค์ 31“เพราะเหตุนี้ผู้ชายจะละจากบิดามารดาของตนไปผูกพันเป็นหนึ่งเดียวกับภรรยา และทั้งสองจะเป็นเนื้อเดียวกัน”5:31 ปฐก.2:24 32ตรงนี้เป็นความลึกลับอันลึกซึ้ง แต่ข้าพเจ้ากำลังพูดถึงพระคริสต์กับคริสตจักร 33อย่างไรก็ตามพวกท่านแต่ละคนต้องรักภรรยาของตนเหมือนที่รักตนเองด้วย และภรรยาก็ต้องเคารพสามีของตน