ኤፌሶን 3 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

ኤፌሶን 3:1-21

ለአሕዛብ ሐዋርያ የሆነው ጳውሎስ

1በዚህም ምክንያት እኔ ጳውሎስ ለእናንተ ለአሕዛብ የክርስቶስ ኢየሱስ እስረኛ ሆኛለሁ።

2ለእናንተ ጥቅም ሲባል ስለ ተሰጠኝ የእግዚአብሔር ጸጋ መጋቢነት በርግጥ ሰምታችኋል፤ 3ቀደም ሲል በዐጭሩ እንደ ጻፍሁት፣ በመገለጥ እንዳውቀው የተደረገው ምስጢር ይህ ነው። 4እንግዲህ ይህን ስታነብቡ፣ የክርስቶስን ምስጢር እንዴት እንደማስተውል ለመረዳት ትችላላችሁ። 5ይህም ምስጢር አሁን ለቅዱሳኑ ሐዋርያትና ነቢያት የተገለጠውን ያህል ባለፉት ዘመናት ለነበሩ ሰዎች አልተገለጠም ነበር። 6ይህም ምስጢር አሕዛብ በወንጌል አማካይነት ከእስራኤል ጋር አብረው ወራሾች፣ አብረው የአንዱ አካል ብልቶች እንዲሁም በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነው ተስፋ አብረው ተካፋይ መሆናቸው ነው።

7እኔም በኀይሉ አሠራር በተሰጠኝ በእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ የዚህ ወንጌል አገልጋይ ሆኛለሁ። 8ምንም እንኳ ከቅዱሳን ሁሉ ያነስሁ ብሆንም፣ የማይመረመረውን የክርስቶስን ባለጠግነት ለአሕዛብ እሰብክ ዘንድ ይህ ጸጋ ለእኔ ተሰጠኝ። 9እንዲሁም ሁሉን በፈጠረ በእግዚአብሔር ላለፉት ዘመናት የተሰወረውን የዚህን ምስጢር አሠራር ለሁሉም እገልጥ ዘንድ ተሰጠኝ። 10ሐሳቡም በአሁኑ ዘመን በቤተ ክርስቲያን አማካይነት ብዙ ገጽታ ያለው የእግዚአብሔር ጥበብ በሰማያዊ ስፍራ ላሉት አለቆችና ባለሥልጣናት ይታወቅ ዘንድ ነው፤ 11ይህም በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን በፈጸመው ዘላለማዊ ዕቅዱ መሠረት ነው። 12በእርሱና በእርሱ ላይ ባለን እምነት አማካይነት፣ በነጻነትና በልበ ሙሉነት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንችላለን። 13ስለዚህ ክብራችሁ በሆነው ስለ እናንተ በደረሰብኝ መከራ ተስፋ እንዳትቈርጡ ዐደራ እላችኋለሁ።

ለኤፌሶን ክርስቲያኖች የተደረገ ጸሎት

14በዚህም ምክንያት በአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ 15ከእርሱም በሰማይና በምድር ያለ ቤተ ሰብ ሁሉ ስያሜ3፥15 ወይም አባትነት ሁሉ ያገኛል። 16በውስጥ ሰውነታችሁ እንድትጠነክሩ፣ ከክብሩ ባለጠግነት በመንፈሱ በኩል ኀይል እንዲሰጣችሁ እጸልያለሁ፤ 17ይኸውም በእምነት ክርስቶስ በልባችሁ እንዲያድር ነው። ደግሞም ሥር ሰድዳችሁ፣ በፍቅር ታንጻችሁ፣ 18የክርስቶስ ፍቅር ስፋቱ፣ ርዝመቱ፣ ከፍታውና ጥልቀቱ ምን ያህል እንደ ሆነ፣ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር የመገንዘብ ኀይልን እንድታገኙ ነው። 19እስከ እግዚአብሔር ሙላት ሁሉ ልክ ደርሳችሁ እንድትሞሉ፣ ከመታወቅ በላይ የሆነውን የክርስቶስን ፍቅር ታውቁም ዘንድ ነው።

20እንግዲህ በእኛ ውስጥ እንደሚሠራው እንደ ኀይሉ መጠን፣ ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ በላይ እጅግ አብልጦ ማድረግ ለሚቻለው፣ 21በቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በክርስቶስ ኢየሱስ፣ በዘመናት ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ክብር ይሁን፤ አሜን።

New Serbian Translation

Ефесцима 3:1-21

1Ради тога сам ја, Павле, сужањ Исуса Христа за вас многобошце. 2Ви сте, свакако, чули за службу која ми је по Божијој милости поверена за вас. 3Наиме, Бог ми је откривењем обзнанио тајну, као што сам вам укратко написао. 4Читајући то, можете да разумете моје поимање Христове тајне, 5која није била позната ранијим нараштајима, али је сада преко Духа откривена његовим светим апостолима и пророцима. 6Тајна се састоји у томе да су многобошци постали сунаследници, припадници истог тела, те да учествују у обећању које је Бог испунио у Христу Исусу путем Радосне вести. 7Овој Радосној вести ја сам постао слуга по дару Божије милости која ми је поверена дејством његове силе.

8А мени, најмањем од свих светих, указана је ова милост да проповедам многобошцима неистраживо богатство Христово, 9и да свима расветлим остварење ове тајне, коју је Бог, створитељ свега, држао сакривеном у минулим вековима, 10да би сада, посредством Цркве, обзнанио своју многострану мудрост главарствима и властима на небесима. 11Бог је то остварио на основу свог вечног наума, посредством нашег Господа, Исуса Христа. 12У њему имамо слободу да приступимо Богу с поуздањем, вером у њега. 13Зато вас молим да се не обесхрабрите овим мојим невољама које подносим за вас; све је то ради ваше славе.

Павлова молитва

14Зато пригибам своја колена пред Оцем, 15који доводи у постојање сваки род на небу и на земљи, 16да вас он, по својој богатој слави, ојача својим Духом у вашем унутрашњем човеку; 17да се Христос вером настани у вашим срцима, те да у љубави будете укорењени и утемељени; 18да разумете са свим светима, ширину, дужину, висину, и дубину Божије љубави, 19и да упознате ту љубав Христову која надмашује свако знање, да бисте сасвим били испуњени Богом.

20А ономе, што силом којом делује у нама може да учини далеко више од свега што молимо или мислимо, 21њему нека је слава у Цркви и у Христу Исусу у свим поколењима од сад и довека! Амин.