ኤፌሶን 3 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ኤፌሶን 3:1-21

ለአሕዛብ ሐዋርያ የሆነው ጳውሎስ

1በዚህም ምክንያት እኔ ጳውሎስ ለእናንተ ለአሕዛብ የክርስቶስ ኢየሱስ እስረኛ ሆኛለሁ።

2ለእናንተ ጥቅም ሲባል ስለ ተሰጠኝ የእግዚአብሔር ጸጋ መጋቢነት በርግጥ ሰምታችኋል፤ 3ቀደም ሲል በዐጭሩ እንደ ጻፍሁት፣ በመገለጥ እንዳውቀው የተደረገው ምስጢር ይህ ነው። 4እንግዲህ ይህን ስታነብቡ፣ የክርስቶስን ምስጢር እንዴት እንደማስተውል ለመረዳት ትችላላችሁ። 5ይህም ምስጢር አሁን ለቅዱሳኑ ሐዋርያትና ነቢያት የተገለጠውን ያህል ባለፉት ዘመናት ለነበሩ ሰዎች አልተገለጠም ነበር። 6ይህም ምስጢር አሕዛብ በወንጌል አማካይነት ከእስራኤል ጋር አብረው ወራሾች፣ አብረው የአንዱ አካል ብልቶች እንዲሁም በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነው ተስፋ አብረው ተካፋይ መሆናቸው ነው።

7እኔም በኀይሉ አሠራር በተሰጠኝ በእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ የዚህ ወንጌል አገልጋይ ሆኛለሁ። 8ምንም እንኳ ከቅዱሳን ሁሉ ያነስሁ ብሆንም፣ የማይመረመረውን የክርስቶስን ባለጠግነት ለአሕዛብ እሰብክ ዘንድ ይህ ጸጋ ለእኔ ተሰጠኝ። 9እንዲሁም ሁሉን በፈጠረ በእግዚአብሔር ላለፉት ዘመናት የተሰወረውን የዚህን ምስጢር አሠራር ለሁሉም እገልጥ ዘንድ ተሰጠኝ። 10ሐሳቡም በአሁኑ ዘመን በቤተ ክርስቲያን አማካይነት ብዙ ገጽታ ያለው የእግዚአብሔር ጥበብ በሰማያዊ ስፍራ ላሉት አለቆችና ባለሥልጣናት ይታወቅ ዘንድ ነው፤ 11ይህም በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን በፈጸመው ዘላለማዊ ዕቅዱ መሠረት ነው። 12በእርሱና በእርሱ ላይ ባለን እምነት አማካይነት፣ በነጻነትና በልበ ሙሉነት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንችላለን። 13ስለዚህ ክብራችሁ በሆነው ስለ እናንተ በደረሰብኝ መከራ ተስፋ እንዳትቈርጡ ዐደራ እላችኋለሁ።

ለኤፌሶን ክርስቲያኖች የተደረገ ጸሎት

14በዚህም ምክንያት በአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ 15ከእርሱም በሰማይና በምድር ያለ ቤተ ሰብ ሁሉ ስያሜ3፥15 ወይም አባትነት ሁሉ ያገኛል። 16በውስጥ ሰውነታችሁ እንድትጠነክሩ፣ ከክብሩ ባለጠግነት በመንፈሱ በኩል ኀይል እንዲሰጣችሁ እጸልያለሁ፤ 17ይኸውም በእምነት ክርስቶስ በልባችሁ እንዲያድር ነው። ደግሞም ሥር ሰድዳችሁ፣ በፍቅር ታንጻችሁ፣ 18የክርስቶስ ፍቅር ስፋቱ፣ ርዝመቱ፣ ከፍታውና ጥልቀቱ ምን ያህል እንደ ሆነ፣ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር የመገንዘብ ኀይልን እንድታገኙ ነው። 19እስከ እግዚአብሔር ሙላት ሁሉ ልክ ደርሳችሁ እንድትሞሉ፣ ከመታወቅ በላይ የሆነውን የክርስቶስን ፍቅር ታውቁም ዘንድ ነው።

20እንግዲህ በእኛ ውስጥ እንደሚሠራው እንደ ኀይሉ መጠን፣ ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ በላይ እጅግ አብልጦ ማድረግ ለሚቻለው፣ 21በቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በክርስቶስ ኢየሱስ፣ በዘመናት ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ክብር ይሁን፤ አሜን።

Knijga O Kristu

Efežanima 3:1-21

Otkrivenje Božjega tajnog plana

1Ja, Pavao, utamničen sam za Isusa Krista zbog vas pogana. 2Kao što zacijelo znate, Bog mi je dao osobitu službu da vam naviještam njegovu milost. 3Kao što sam već ukratko opisao, Bog mi je objavio svoj tajni naum. 4Čitajući to, shvatit ćete da razumijem Otajstvo—Krista. 5Bog ga nije objavio prijašnjim naraštajima, ali sada ga je po Svetom Duhu objavio svojim svetim apostolima i prorocima.

6A tajna je u tome da će pogani, prema evanđelju, skupa sa Židovima biti subaštinicima, udovima istog Tijela i dionicima obećanja u Kristu Isusu. 7Bog mi je svojom milošću podario da tome evanđelju služim djelotvornošću njegove sile.

8Pomislite samo! Iako to nisam ničim zaslužio, iako sam najmanji među svim svetima, ipak sam izabran da drugim narodima prenesem Radosnu vijest o neiscrpnom bogatstvu koje imaju u Kristu; 9da svakome objasnim tajnu da je Bog Spasitelj i drugih naroda, onaj koji je sve stvorio i u tajnosti sve naumio još odavno, od samoga početka.

10Božja je svrha toga bila da pokaže svim Vrhovništvima i Vlastima na nebesima sve bogatstvo i raznolikost svoje mudrosti, koja će se očitovati u njegovoj Crkvi. 11Taj je svoj vječni naum ostvario u našemu Gospodinu Kristu Isusu.

12U njemu možemo s pouzdanjem, kroz vjeru, slobodno pristupiti Bogu. 13Nemojte zato, molim vas, klonuti zbog nevolja koje zaradi vas podnosim. Ponosite se njima!

Pavlova molitva za duhovnu silu

14Prigibam zato koljena pred Ocem, 15Stvoriteljem svega što je na nebesima i na zemlji.3:15 U grčkome: po kome svako očinstvo u nebesima i na zemlji ima ime. 16Molim se da vam iz svojega slavnog bogatstva dade da kroz Svetoga Duha ojačate svoje nutarnje biće, 17da Krist prebiva u vašim srcima po vjeri, da budete ukorijenjeni i utemeljeni u ljubavi, 18da možete potpuno razumjeti, kao i sva Božja djeca, duljinu, širinu, dubinu i visinu njegove ljubavi, 19da spoznate Kristovu ljubav, tako veliku da ju nikada nećete moći potpuno shvatiti. Tada ćete biti ispunjeni Božjom puninom.

20Neka je slava Bogu! Svojom silom koja djeluje u nama on može učiniti puno više nego što ga mi uopće možemo moliti ili zamisliti. 21Neka mu je slava u Crkvi i u Kristu Isusu kroz sve naraštaje i u vijeke vjekova!