ኤፌሶን 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤፌሶን 2:1-22

በክርስቶስ ሕያው መሆን

1እናንተ በበደላችሁና በኀጢአታችሁ ምክንያት ሙታን ነበራችሁ፤ 2በዚህም፣ የዓለምን ክፉ መንገድ ተከትላችሁ፣ በአየር ላይ ላሉት መንፈሳውያን ኀይላት ገዥ ለሆነውና አሁንም ለእግዚአብሔር በማይታዘዙት ሰዎች ላይ ለሚሠራው መንፈስ እየታዘዛችሁ ትኖሩ ነበር። 3እኛ ሁላችን በአንድ ወቅት የሥጋችንን ምኞት2፥3 ወይም የአሮጌውን ባሕርይ ፈቃድ እያረካን፣ መንገዱንም እየተከተልን በመካከላቸው እንኖር ነበር፤ እንደ ሌሎቹም የቍጣ ልጆች ነበርን። 4ነገር ግን በምሕረቱ ባለጠጋ የሆነ እግዚአብሔር ለእኛ ካለው ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ፣ 5በበደላችን ሙታን ሆነን ሳለ፣ በክርስቶስ ሕያዋን አደረገን፤ የዳናችሁት በጸጋ ነው። 6እግዚአብሔርም ከክርስቶስ ጋር አስነሣን፤ በክርስቶስ ኢየሱስ በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን፤ 7ይኸውም በሚመጣው ዘመን በክርስቶስ ኢየሱስ በቸርነቱ የገለጠልንን ወደር የሌለውን የጸጋውን ባለጠግነት ያሳይ ዘንድ ነው፤ 8በእምነት፣ በጸጋ ድናችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ 9ማንም እንዳይመካ በሥራ አይደለም፤ 10ምክንያቱም፣ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀልንን መልካም ሥራ እንድንሠራ በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጠርን የእግዚአብሔር እጅ ሥራዎች ነን።

በክርስቶስ አንድ መሆን

11ስለዚህ እናንተ ቀድሞ በትውልድ አሕዛብ የሆናችሁ፣ በአካል ላይ በሰው እጅ ከተደረገው የተነሣ፣ ራሳቸውን “ተገርዘናል” በሚሉት፣ “ያልተገረዙ” የተባላችሁ ያን አስታውሱ፤ 12በዚያን ዘመን ከክርስቶስ ተለይታችሁ፣ ከእስራኤል ወገንነት ርቃችሁ፣ ለኪዳኑም ተስፋ ባዕዳን ሆናችሁ፣ በዓለም ላይ ያለ ተስፋና ያለ እግዚአብሔር እንደ ነበራችሁ አስታውሱ። 13አሁን ግን እናንተ ቀድሞ ርቃችሁ የነበራችሁ፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም አማካይነት ቀርባችኋል።

14ሁለቱን አንድ ያደረገ፣ የሚለያየውንም የጥል ግድግዳ ያፈረሰ ሰላማችን እርሱ ራሱ ነውና፤ 15ሕግንም፣ ከትእዛዞቹና ከሥርዐቱ ጋር በሥጋው ሻረ። ዐላማውም ከሁለቱ አንድን አዲስ ሰው በራሱ ፈጥሮ ሰላምን ለማድረግ ነው። 16ጥልን በገደለበት በመስቀሉም ሁለቱን በዚህ በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ። 17መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁት ለእናንተ፣ ቀርበው ለነበሩትም ለእነርሱ ሰላምን ሰበከ፤ 18ሁላችንም በእርሱ አማካይነት በአንዱ መንፈስ ወደ አብ መቅረብ እንችላለንና።

19ከዚህ የተነሣ እናንተ ከቅዱሳን ጋር የአንድ አገር ዜጋ፣ የእግዚአብሔርም ቤተ ሰብ አባል ናችሁ እንጂ፣ ከእንግዲህ ወዲህ መጻተኞችና እንግዶች አይደላችሁም። 20በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፤ የማእዘኑ ራስ ድንጋይም ክርስቶስ ኢየሱስ ራሱ ነው፤ 21በእርሱ ሕንጻ ሁሉ አንድ ላይ ተገጣጥሞ በጌታ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንዲሆን ያድጋል። 22እናንተም ደግሞ እግዚአብሔር በመንፈሱ የሚኖርበት ማደሪያ ትሆኑ ዘንድ አብራችሁ እየተገነባችሁ ነው።

Thai New Contemporary Bible

เอเฟซัส 2:1-22

มีชีวิตในพระคริสต์

1ส่วนท่านทั้งหลายได้ตายแล้วในการล่วงละเมิดและในบาปทั้งหลาย 2ซึ่งท่านเคยทำเมื่อดำเนินชีวิตตามวิถีของโลกนี้ และวิถีของเจ้าแห่งย่านฟ้าอากาศซึ่งเป็นวิญญาณที่บัดนี้ทำการอยู่ในบรรดาผู้ที่ไม่เชื่อฟัง 3ครั้งหนึ่งเราเคยใช้ชีวิตร่วมกับพวกนั้นบำเรอตัณหาแห่งวิสัยบาปของเรา2:3 หรือเนื้อหนังของเรา สนองความอยากกับความคิดของมันตามวิสัย เราจึงควรแก่พระพิโรธเหมือนคนอื่น 4แต่เนื่องด้วยความรักใหญ่หลวงที่ทรงมีต่อเรา พระเจ้าผู้เปี่ยมด้วยพระเมตตาอันอุดม 5จึงทรงให้เรามีชีวิตอยู่กับพระคริสต์แม้เมื่อเราได้ตายแล้วในบาป คือท่านทั้งหลายได้รับความรอดโดยพระคุณ 6และพระองค์ทรงให้เราเป็นขึ้นมากับพระคริสต์ และในพระเยซูคริสต์ พระเจ้าทรงให้เรานั่งในสวรรคสถานกับพระคริสต์ 7เพื่อในยุคต่อๆ ไปพระองค์จะได้ทรงสำแดงความอุดมแห่งพระคุณอันหาใดเปรียบ ซึ่งได้ทรงแสดงด้วยพระกรุณาที่มีต่อเราในพระเยซูคริสต์ 8เพราะว่าท่านทั้งหลายได้รับความรอดโดยพระคุณผ่านทางความเชื่อ ความรอดนี้ไม่ได้มาจากตัวท่านเอง แต่เป็นของประทานจากพระเจ้า 9ไม่ใช่ความรอดโดยการประพฤติ เพื่อจะไม่มีใครอวดได้ 10เพราะเราทั้งหลายเป็นผลงานของพระเจ้าซึ่งทรงสร้างในพระเยซูคริสต์เพื่อให้ทำการดีที่พระเจ้าทรงจัดเตรียมไว้ล่วงหน้าให้เราทำ

หนึ่งเดียวกันในพระคริสต์

11เพราะฉะนั้นจงระลึกว่าแต่ก่อนท่านเป็นคนต่างชาติโดยกำเนิด และบรรดาผู้ที่เรียกตนเองว่า “พวกที่เข้าสุหนัต” (ซึ่งกระทำทางกายด้วยมือมนุษย์) เรียกท่านว่า “พวกไม่เข้าสุหนัต” 12จงระลึกว่าครั้งนั้นท่านแยกจากพระคริสต์ ไม่ได้เป็นพลเมืองอิสราเอลและเป็นคนต่างด้าวอยู่นอกพันธสัญญาที่ทรงสัญญาไว้ ไม่มีความหวังและอยู่ในโลกโดยปราศจากพระเจ้า 13แต่บัดนี้ในพระเยซูคริสต์ท่านทั้งหลายซึ่งเมื่อก่อนอยู่ไกลได้เข้ามาใกล้แล้วโดยพระโลหิตของพระคริสต์

14เพราะพระองค์เองทรงเป็นสันติสุขของเรา ผู้ทรงทำให้สองพวกกลายเป็นหนึ่งเดียวกัน และทรงทำลายสิ่งกีดขวาง คือกำแพงแห่งความเกลียดชังที่กีดกั้นลง 15โดยทรงล้มเลิกบทบัญญัติทั้งหมดของชาวยิวซึ่งประกอบด้วยข้อบังคับและกฎระเบียบต่างๆ ด้วยพระกายของพระองค์ จุดประสงค์ของพระองค์ก็เพื่อยุบสองฝ่ายและสร้างขึ้นใหม่เป็นหนึ่งเดียวในพระองค์ เช่นนี้แหละจึงทรงทำให้มีสันติสุข 16และในกายเดียวนี้ทั้งสองพวกจึงกลับคืนดีกับพระเจ้าโดยไม้กางเขน ซึ่งพระองค์ทรงใช้ทำลายความเป็นศัตรูกันให้หมดสิ้นไป 17พระองค์เสด็จมาประกาศสันติสุขแก่ท่านทั้งหลายที่อยู่ไกลและสันติสุขแก่ผู้ที่อยู่ใกล้ 18เพราะโดยพระองค์เราทั้งสองพวกสามารถเข้าถึงพระบิดาโดยพระวิญญาณองค์เดียวกัน

19ดังนั้นท่านจึงไม่ใช่คนต่างด้าวแปลกถิ่นอีกต่อไป แต่เป็นพลเมืองเดียวกับประชากรของพระเจ้าและเป็นสมาชิกในครอบครัวของพระเจ้า 20ท่านได้รับการสร้างขึ้นบนฐานรากของเหล่าอัครทูตและผู้เผยพระวจนะโดยมีพระเยซูคริสต์เองเป็นศิลามุมเอก 21ในพระองค์ ทุกส่วนของอาคารทั่วทั้งหมดต่อกันสนิท และประกอบกันขึ้นเป็นวิหารอันศักดิ์สิทธิ์ในองค์พระผู้เป็นเจ้า 22และในพระองค์ ท่านก็เช่นกันกำลังรับการทรงสร้างขึ้นด้วยกันให้เป็นที่ประทับซึ่งพระเจ้าสถิตอยู่โดยพระวิญญาณของพระองค์