ኤርምያስ 9 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 9:1-26

1ስለ ታረዱት ወገኖቼ፣

ቀንና ሌሊት አለቅስ ዘንድ፣

ምነው፣ ራሴ የውሃ ምንጭ በሆነ!

ምነው ዐይኖቼ የእንባ መጕረፊያ በሆኑልኝ!

2ሕዝቤን ትቼ፣ ርቄ እንድሄድ፣

በምድረ በዳ የእንግዶች ማደሪያ ማን በሰጠኝ!

ሁሉም አመንዝሮች፣

የአታላዮች መንጋ ሆነዋላ!

3“ሐሰትን ለመናገር፣

ምላሳቸውን እንደ ቀስት ገተሩ፤

በእውነት ሳይሆን፣

በሐሰት በምድሪቱ ገነኑ፤

ከክፋት ወደ ክፋት ሄዱ፤

እኔንም አላወቁኝም፤”

ይላል እግዚአብሔር

4“እያንዳንዱ ወንድም አታላይ፣9፥4 ወይም አታላይ ያዕቆብ

ባልንጀራም ሁሉ ሐሜተኛ ስለሆነ፣

ወንድም ከወንድሙ ይጠንቀቅ፤

ባልንጀራም በጓደኛው አይታመን።

5ባልንጀራ ባልንጀራውን ያታልላል፤

እውነትን የሚናገር የለም፤

ሐሰትን ይናገሩ ዘንድ ምላሳቸውን አሠልጥነዋል፤

ኀጢአትንም በማድረግ ራሳቸውን አድክመዋል።

6መኖሪያህ9፥6 ኤርምያስን ያመለክታል (በዕብራይስጡ በነጠላ ቍጥር ተጽፏል) በሽንገላ መካከል ነው፤

ከሽንገላቸውም የተነሣ ሊያውቁኝ አልፈቀዱም፤”

ይላል እግዚአብሔር

7ስለዚህ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ እንደ ብረት አነጥራቸዋለሁ፤ እፈትናቸዋለሁም፤

ስለ ሕዝቤ ኀጢአት፣

ከዚህ የተለየ ምን ማድረግ እችላለሁ?

8ምላሳቸው የሚገድል ቀስት ነው፤

በሽንገላ ይናገራል፤

ሁሉም ከባልንጀራው ጋር በፍቅር ይናገራል፤

በልቡ ግን ያደባበታል።

9ታዲያ ስለ እነዚህ ነገሮች ልቀጣቸው አይገባኝምን?”

ይላል እግዚአብሔር

“እንደዚህ ዐይነቱንስ ሕዝብ፣

አልበቀልምን?”

10ስለ ተራሮች አለቅሳለሁ፤ ዋይ ዋይ እላለሁ፤

በምድረ በዳ ስላሉትም መሰማሪያዎች ዐዝናለሁ።

ሰው የማያልፍባቸው ባድማ ሆነዋል፤

የከብቶች ጩኸት አይሰማም፤

የሰማይ ወፎች ሸሽተዋል፤

የዱር አራዊትም ጠፍተዋል።

11“ኢየሩሳሌምን የፍርስራሽ ክምር፣

የቀበሮም ጐሬ አደርጋታለሁ፤

የይሁዳንም ከተሞች፣

ሰው የማይኖርባቸው ባድማ አደርጋቸዋለሁ።”

12ይህን መረዳት የሚችል ጥበበኛ ሰው ማን ነው? እግዚአብሔር ገልጾለት ይህንስ ማስረዳት የሚችል ማን ነው? ምድሪቱስ ሰው እንደማያልፍበት በረሓ ለምን ጠፋች? ለምን ወና ሆነች?

13እግዚአብሔርም እንዲህ አለ፤ “ይህ የሆነው የሰጠኋቸውን ሕጌን ትተው ስላልታዘዙኝና ሥርዐቴን ስላልተከተሉ ነው። 14በዚህ ፈንታ፣ በልባቸው እልኸኝነት በመሄድ አባቶቻቸው ያስተማሯቸውን በኣሊምን ተከተሉ።” 15ስለዚህ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣ እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ ይህን ሕዝብ መራራ ምግብ አበላዋለሁ፤ የተመረዘንም ውሃ አጠጣዋለሁ። 16እነርሱንም ሆነ አባቶቻቸውን በማያውቋቸው ሕዝቦች መካከል እበትናቸዋለሁ፤ እስካጠፋቸውም ድረስ በሰይፍ አሳድዳቸዋለሁ።”

17የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እንግዲህ፤ አልቃሽ ሴቶች ጥሩ፤

ሥልጡን ሙሾ አውራጆች አስመጡ፤

18እነርሱ ፈጥነው ይምጡ፤

ዐይኖቻችን እንባ እስኪያጐርፉ፣

ሽፋሽፍቶቻችንም ውሃ እስኪያመነጩ፣

ስለ እኛ ሙሾ ያውርዱልን።

19እነሆ የዋይታ ድምፅ ከጽዮን ተሰምቷል፤ እንዲህም ይላል፤

‘ምንኛ ወደቅን!

ውርደታችንስ እንዴት ታላቅ ነው!

ቤቶቻችን ፈራርሰዋልና፤

አገራችንን ጥለን እንሂድ።’ ”

20እናንት ሴቶች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤

ጆሮቻችሁን ከአንደበቱ ለሚወጡት ቃላት ክፈቱ፤

ሴቶች ልጆቻችሁን ዋይታ፣

አንዳችሁም ሌላውን ሙሾ አስተምሩ።

21ሞት በመስኮቶቻችን ገብቷል፤

ወደ ምሽጎቻችንም ዘልቋል፤

ሕፃናትን ከየመንገዱ፣

ወጣቶችን ከየአደባባዩ ጠራርጎ ወስዷል።

22እንዲህ በሉ፤ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘የሰዎች ሬሳ፣

በሜዳ እንደ ተጣለ ጕድፍ፣

ማንም እንደማይሰበስበው፣

ከዐጫጅ ኋላ እንደ ተተወ ቃርሚያ ይወድቃል።’ ”

23እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ጥበበኛ በጥበቡ አይታበይ፤

ኀያልም በኀይሉ አይመካ፤

ሀብታምም በሀብቱ አይኵራራ፤

24የሚመካ ግን፣

እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ በማወቁና፣

በምድር ላይ ምሕረትን፣ ፍትሕንና ጽድቅን የማደርግ መሆኔን በመረዳቱ፣

በዚህ ይመካ፤ እኔ በእነዚህ ነገሮች፣

እደሰታለሁና፤”

ይላል እግዚአብሔር

25እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ሥጋቸውን ብቻ የተገረዙትን ሁሉ የምቀጣበት ጊዜ ይመጣል፤ 26እነርሱም ግብፅ፣ ይሁዳ፣ ኤዶም፣ አሞን፣ ሞዓብና ጠጕራቸው ዙሪያውን የሚከረከም የበረሓ9፥26 ወይም በበረሓ በተራራቁ ስፍራዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች ሁሉ ናቸው፤ እነዚህ ሕዝቦች ሁሉ በርግጥ የተገረዙ አይደሉምና፤ የእስራኤልም ቤት ሁሉ ልባቸው አልተገረዘም።”

Japanese Contemporary Bible

エレミヤ書 9:1-26

9

1ああ、私の目が涙の泉であったら、

殺された同胞のために、

昼となく夜となく、永久にすすり泣くことだろう。

2ああ、どこか遠くへ行って何もかも忘れ、

荒野の小屋に住めたら、どんなに気が楽だろう。

彼らはみな姦淫の罪を犯し、

裏切り者になり下がってしまった。

3「彼らは舌を弓のように曲げ、不真実という矢を射る。

正しいことには縁もゆかりもない者で、

悪から悪へと進み、わたしのことなど

いっこう心に留めない」と、主は言います。

4隣人や兄弟に気をつけなさい。

だれもかれも人を利用しようと、

中傷し合うからです。

5彼らは、よく訓練された舌で互いにだまし合い、

罪を犯し続けて、弱り果てます。

6「彼らは悪に悪を、偽りに偽りを積み重ね、

絶対にわたしのところへ来ようとしない」と、

主は言います。

7そのため、天の軍勢の主は、さらにこうつけ加えます。

「わたしは彼らを悩みの炉に入れてとかす。

彼らを精錬し、金属のように試す。

これ以外にどんなことができよう。

8彼らの舌は毒矢のようなうそを射る。

口先では穏やかに語るが、

心の中では相手を殺そうと企む。

9この事実に目をつぶり、

罰せずに放っておけるだろうか。

このような国に復讐しないでいられようか。」

10私は泣きながら、山や牧場を指さします。

そこには住む者もなく、

すっかり荒れ果てているのです。

家畜の鳴き声は絶え、鳥や獣も姿を消しました。

11「わたしはエルサレムを、瓦礫の山にする。

そこを住みかとするのは山犬だけだ。

ユダの町々は、誰ひとり住む者のない廃墟になる。」

12このことを悟る知恵者は、どこにいるでしょう。

このことを説明してくれる主の使者は、

どこにいるのでしょうか。

どうしてこの国は荒れ地となり、

通行人さえいなくなったのでしょうか。

13「それは、わたしの民がわたしの戒めを捨て、おきてに従わなかったからだ。 14それどころか、好き勝手なことばかりして、先祖が伝えたバアルを拝んだ。 15そこで、イスラエルの神であるわたしは言う。彼らに苦い物を食べさせ、毒を飲ませる。 16彼らを世界中に散らし、遠くの国々に追い払う。どこへ行っても、剣に追い回され、ついに根絶やしにされる。

17-18わたしは言う。

大急ぎで泣き女を呼んで来て、泣かせなさい。

涙を滝のように流させるのだ。

19エルサレムが絶望しきって泣いているのを聞け。

『町はすっかり荒れ果てた。悲劇が私たちを襲った。

こうなったら、国も家も見捨てるよりほかない。』」

20大声を上げて泣く女たちよ、

神のことばに耳を傾けなさい。

娘と隣人に、泣き方を教えなさい。

21死が窓から家に忍び込み、

若いいのちをもぎ取ったからです。

道ばたで遊ぶ子どもの姿はなく、

広場にも若者の姿はありません。

22次のことを話すようにと、主は言います。

死体は肥やしのように、

刈り入れのあとの束のように、

あちこちに散らされたままで、だれも埋めてくれない。

23主は命じます。

「知恵のある者は、知恵をひけらかしてはいけない。

力のある者は力を、金持ちは富を誇ってはいけない。

24誇る者は、わたしをほんとうに知っていることと、

わたしが正義の主であって、

その愛は変わらないと知っていることを誇りなさい。

25-26わたしが、体に割礼(男子が生まれて八日目に

その生殖器の包皮を切り取る儀式)を受けていても、

心に割礼を受けていないエジプト人、エドム人、

アモン人、モアブ人、アラブ人、

そしておまえたちユダの民を

罰する時が近づいている。

異教の国々の民でも体の割礼は受ける。

わたしを愛するしるしに心の割礼を受けなければ、

おまえたちの割礼は、

異教徒の儀式と少しも変わらない。」