ኤርምያስ 9 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 9:1-26

1ስለ ታረዱት ወገኖቼ፣

ቀንና ሌሊት አለቅስ ዘንድ፣

ምነው፣ ራሴ የውሃ ምንጭ በሆነ!

ምነው ዐይኖቼ የእንባ መጕረፊያ በሆኑልኝ!

2ሕዝቤን ትቼ፣ ርቄ እንድሄድ፣

በምድረ በዳ የእንግዶች ማደሪያ ማን በሰጠኝ!

ሁሉም አመንዝሮች፣

የአታላዮች መንጋ ሆነዋላ!

3“ሐሰትን ለመናገር፣

ምላሳቸውን እንደ ቀስት ገተሩ፤

በእውነት ሳይሆን፣

በሐሰት በምድሪቱ ገነኑ፤

ከክፋት ወደ ክፋት ሄዱ፤

እኔንም አላወቁኝም፤”

ይላል እግዚአብሔር

4“እያንዳንዱ ወንድም አታላይ፣9፥4 ወይም አታላይ ያዕቆብ

ባልንጀራም ሁሉ ሐሜተኛ ስለሆነ፣

ወንድም ከወንድሙ ይጠንቀቅ፤

ባልንጀራም በጓደኛው አይታመን።

5ባልንጀራ ባልንጀራውን ያታልላል፤

እውነትን የሚናገር የለም፤

ሐሰትን ይናገሩ ዘንድ ምላሳቸውን አሠልጥነዋል፤

ኀጢአትንም በማድረግ ራሳቸውን አድክመዋል።

6መኖሪያህ9፥6 ኤርምያስን ያመለክታል (በዕብራይስጡ በነጠላ ቍጥር ተጽፏል) በሽንገላ መካከል ነው፤

ከሽንገላቸውም የተነሣ ሊያውቁኝ አልፈቀዱም፤”

ይላል እግዚአብሔር

7ስለዚህ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ እንደ ብረት አነጥራቸዋለሁ፤ እፈትናቸዋለሁም፤

ስለ ሕዝቤ ኀጢአት፣

ከዚህ የተለየ ምን ማድረግ እችላለሁ?

8ምላሳቸው የሚገድል ቀስት ነው፤

በሽንገላ ይናገራል፤

ሁሉም ከባልንጀራው ጋር በፍቅር ይናገራል፤

በልቡ ግን ያደባበታል።

9ታዲያ ስለ እነዚህ ነገሮች ልቀጣቸው አይገባኝምን?”

ይላል እግዚአብሔር

“እንደዚህ ዐይነቱንስ ሕዝብ፣

አልበቀልምን?”

10ስለ ተራሮች አለቅሳለሁ፤ ዋይ ዋይ እላለሁ፤

በምድረ በዳ ስላሉትም መሰማሪያዎች ዐዝናለሁ።

ሰው የማያልፍባቸው ባድማ ሆነዋል፤

የከብቶች ጩኸት አይሰማም፤

የሰማይ ወፎች ሸሽተዋል፤

የዱር አራዊትም ጠፍተዋል።

11“ኢየሩሳሌምን የፍርስራሽ ክምር፣

የቀበሮም ጐሬ አደርጋታለሁ፤

የይሁዳንም ከተሞች፣

ሰው የማይኖርባቸው ባድማ አደርጋቸዋለሁ።”

12ይህን መረዳት የሚችል ጥበበኛ ሰው ማን ነው? እግዚአብሔር ገልጾለት ይህንስ ማስረዳት የሚችል ማን ነው? ምድሪቱስ ሰው እንደማያልፍበት በረሓ ለምን ጠፋች? ለምን ወና ሆነች?

13እግዚአብሔርም እንዲህ አለ፤ “ይህ የሆነው የሰጠኋቸውን ሕጌን ትተው ስላልታዘዙኝና ሥርዐቴን ስላልተከተሉ ነው። 14በዚህ ፈንታ፣ በልባቸው እልኸኝነት በመሄድ አባቶቻቸው ያስተማሯቸውን በኣሊምን ተከተሉ።” 15ስለዚህ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣ እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ ይህን ሕዝብ መራራ ምግብ አበላዋለሁ፤ የተመረዘንም ውሃ አጠጣዋለሁ። 16እነርሱንም ሆነ አባቶቻቸውን በማያውቋቸው ሕዝቦች መካከል እበትናቸዋለሁ፤ እስካጠፋቸውም ድረስ በሰይፍ አሳድዳቸዋለሁ።”

17የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እንግዲህ፤ አልቃሽ ሴቶች ጥሩ፤

ሥልጡን ሙሾ አውራጆች አስመጡ፤

18እነርሱ ፈጥነው ይምጡ፤

ዐይኖቻችን እንባ እስኪያጐርፉ፣

ሽፋሽፍቶቻችንም ውሃ እስኪያመነጩ፣

ስለ እኛ ሙሾ ያውርዱልን።

19እነሆ የዋይታ ድምፅ ከጽዮን ተሰምቷል፤ እንዲህም ይላል፤

‘ምንኛ ወደቅን!

ውርደታችንስ እንዴት ታላቅ ነው!

ቤቶቻችን ፈራርሰዋልና፤

አገራችንን ጥለን እንሂድ።’ ”

20እናንት ሴቶች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤

ጆሮቻችሁን ከአንደበቱ ለሚወጡት ቃላት ክፈቱ፤

ሴቶች ልጆቻችሁን ዋይታ፣

አንዳችሁም ሌላውን ሙሾ አስተምሩ።

21ሞት በመስኮቶቻችን ገብቷል፤

ወደ ምሽጎቻችንም ዘልቋል፤

ሕፃናትን ከየመንገዱ፣

ወጣቶችን ከየአደባባዩ ጠራርጎ ወስዷል።

22እንዲህ በሉ፤ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘የሰዎች ሬሳ፣

በሜዳ እንደ ተጣለ ጕድፍ፣

ማንም እንደማይሰበስበው፣

ከዐጫጅ ኋላ እንደ ተተወ ቃርሚያ ይወድቃል።’ ”

23እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ጥበበኛ በጥበቡ አይታበይ፤

ኀያልም በኀይሉ አይመካ፤

ሀብታምም በሀብቱ አይኵራራ፤

24የሚመካ ግን፣

እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ በማወቁና፣

በምድር ላይ ምሕረትን፣ ፍትሕንና ጽድቅን የማደርግ መሆኔን በመረዳቱ፣

በዚህ ይመካ፤ እኔ በእነዚህ ነገሮች፣

እደሰታለሁና፤”

ይላል እግዚአብሔር

25እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ሥጋቸውን ብቻ የተገረዙትን ሁሉ የምቀጣበት ጊዜ ይመጣል፤ 26እነርሱም ግብፅ፣ ይሁዳ፣ ኤዶም፣ አሞን፣ ሞዓብና ጠጕራቸው ዙሪያውን የሚከረከም የበረሓ9፥26 ወይም በበረሓ በተራራቁ ስፍራዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች ሁሉ ናቸው፤ እነዚህ ሕዝቦች ሁሉ በርግጥ የተገረዙ አይደሉምና፤ የእስራኤልም ቤት ሁሉ ልባቸው አልተገረዘም።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

耶利米書 9:1-26

1真希望我的頭是水泉,

眼是淚泉,

好為我被殺的同胞晝夜哭泣;

2真希望我在曠野有棲身之處,

以便遠離我的同胞,

因為他們是一群不忠不貞之徒。

3耶和華說:

「他們鼓舌如簧,射出謊言,

遍地充滿詭詐,毫無誠實;

他們行惡不斷,

不認我是上帝。

4你們要提防鄰居,

不要信賴弟兄,

因為弟兄詭計多端,

鄰居滿口是非。

5他們彼此欺騙,不說真話;

他們說謊成性,

不知疲倦地肆意犯罪;

6他們充滿詭詐,

不認我是上帝。

這是耶和華說的。」

7因此,萬軍之耶和華說:

「看啊,我要熬煉、試驗這些罪惡的子民,

除此之外,我別無選擇。

8他們舌如毒箭,說話詭詐,

對鄰居口蜜腹劍。

9難道我不該懲罰他們嗎?

難道我不該報應這樣的民族嗎?

這是耶和華說的。」

10我要為眾山悲傷痛哭,

為曠野的草原唱哀歌,

因為那裡一片荒涼,杳無人跡,

聽不見牲畜的叫聲,

飛鳥和走獸也逃去無蹤。

11耶和華說:「我要使耶路撒冷淪為廢墟,

成為豺狼出沒之地;

我要使猶大的城邑荒涼,

不見人煙。」

12誰有智慧明白這事呢?誰曾受過耶和華的指教可以講解這事呢?為什麼這片土地被蹂躪,變得荒涼、杳無人跡? 13耶和華說:「這是因為他們棄絕我賜給他們的律法,不聽從我的話,不遵守我的命令, 14執迷不悟,隨從他們祖先的教導去供奉巴力。」 15因此,以色列的上帝——萬軍之耶和華說:「看啊,我要使這百姓吃苦艾,喝毒藥; 16我要把他們分散到他們及其祖先都不認識的列國;我要使敵人追殺他們,直到滅絕他們。」

17萬軍之耶和華說:

「把陪哭的婦人請來,

把最會哭的婦人帶來,

18叫她們速來為我的子民哀哭,

哭得他們淚盈滿眶,

哭得他們淚如泉湧。

19因為從錫安傳出哀鳴,

『我們滅亡了!

我們受了奇恥大辱!

我們的家園被毀,

我們只好背井離鄉。』」

20婦人啊,你們要聽耶和華的話,

接受祂的教誨;

你們要教導女兒哀哭,

教導鄰居唱輓歌。

21因為死亡從窗戶爬進我們的城堡,

吞滅街上的孩童和廣場上的青年。

22耶和華說:「人們必屍橫遍野,

像散佈在田野上的糞便,

又像收割者身後沒有收集的禾捆。」

23耶和華說:「智者不要誇耀自己的智慧,勇士不要誇耀自己的力量,富人不要誇耀自己的財富。 24若有人誇耀,就讓他誇耀自己認識我是耶和華,知道我喜歡在地上憑慈愛、公平和正義行事。這是耶和華說的。」 25耶和華說:「看啊,時候將到,我要懲罰所有只在身體受過割禮的人, 26就是埃及人、猶大人、以東人、亞捫人、摩押人和所有住在曠野、剃了鬢髮的人,因為這些人,包括以色列人,都沒有受過真正的割禮,沒有受過內心的割禮。」