ኤርምያስ 52 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 52:1-34

የኤርምያስ ቃል እዚህ ላይ ይፈጸማል።

የኢየሩሳሌም መውደቅ

52፥1-3 ተጓ ምብ – 2ነገ 24፥18-202ዜና 36፥11-16

52፥4-16 ተጓ ምብ – ኤር 39፥1-10

52፥4-21 ተጓ ምብ – 2ነገ 25፥1-212ዜና 36፥17-20

1ሴዴቅያስ ሲነግሥ ዕድሜው ሃያ አንድ ዓመት ነበረ፤ በኢየሩሳሌም ዐሥራ አንድ ዓመት ነገሠ፤ የእናቱም ስም አሚጣል ሲሆን፣ እርሷም የሊብና ሰው የኤርምያስ ልጅ ነበረች። 2ሴዴቅያስም ኢዮአቄም እንዳደረገው ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ነገር አደረገ። 3እግዚአብሔር በኢየሩሳሌምና በይሁዳ ላይ ይህን ሁሉ ያደረሰውንና በመጨረሻም ከፊቱ ያስወገዳቸው ከቍጣው የተነሣ ነበር።

ሴዴቅያስም በባቢሎን ንጉሥ ላይ ዐመፀ። 4ስለዚህ ሴዴቅያስ በነገሠ በዘጠነኛው ዓመት በዐሥረኛው ወር፣ ከወሩም በዐሥረኛው ቀን፣ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ሰራዊቱን ሁሉ አስከትቶ በኢየሩሳሌም ላይ ዘመተ፤ ከተማዪቱንም ከበቧት፤ በዙሪያውም የዐፈር ድልድል ሠሩ። 5ከተማዪቱም እስከ ንጉሡ እስከ ሴዴቅያስ ዐሥራ አንደኛ ዘመነ መንግሥት ተከብባ ነበር።

6በአራተኛው ወር በዘጠነኛው ቀን በከተማዪቱ ራብ ጸንቶ ስለ ነበር ሕዝቡ የሚበላውን ዐጣ፤ 7የከተማዪቱም ቅጥር ተነደለ፤ ሰራዊቱም ሁሉ ኰብልሎ ሄደ። ባቢሎናውያን52፥7 ወይም ከለዳውያን፤ 17 ይመ። በከተማዪቱ ዙሪያ ቢኖሩም፣ በንጉሡ የአትክልት ስፍራ አጠገብ በሁለት ቅጥሮች መካከል ባለው በር በሌሊት ከተማዪቱን ጥለው ሸሹ፤ ወደ ዓረባም52፥7 ወይም ዮርዳኖስ ሸለቆ አመሩ። 8የባቢሎናውያንም52፥8 ወይም ከለዳውያን፤ 14 ይመ። ሰራዊት ንጉሥ ሴዴቅያስን ተከታትሎ በማሳደድ በኢያሪኮ ሜዳ ደረሱበት፤ ወታደሮቹም ሁሉ ከእርሱ ተለይተው ተበታትነው ሳለ፣ ንጉሡን ያዙት።

9እርሱም በሐማት ምድር በሪብላ ወደ ነበረው ወደ ባቢሎንም ንጉሥ ተወሰደ፤ የባቢሎን ንጉሥ በዚያ ፈረደበት። 10በሪብላም የባቢሎን ንጉሥ፣ የሴዴቅያስን ወንዶች ልጆች በአባታቸው ፊት ዐረዳቸው፤ የይሁዳንም ባለሥልጣኖች ሁሉ ገደላቸው፤ 11የሴዴቅያስንም ዐይኖች አወጣ፤ በናስ ሰንሰለትም አስሮ ወደ ባቢሎን ወሰደው፤ በዚያም እስከ ዕለተ ሞቱ በእስር ቤት አቈየው።

12የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በነገሠ በዐሥራ ዘጠነኛው ዓመት በአምስተኛው ወር፤ ከወሩም በዐሥረኛው ቀን፣ የባቢሎን ንጉሥ ባለሟል የክብር ዘበኞች አዛዥ የነበረው ናቡዘረዳን ወደ ኢየሩሳሌም መጣ። 13የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስና የንጉሡን ቤተ መንግሥት እንዲሁም በኢየሩሳሌም የነበሩትን ቤቶች ሁሉ በእሳት አቃጠለ፤ ሌሎች ትልልቅ ሕንጻዎችንም በእሳት አወደመ። 14በክብር ዘበኞቹ አዛዥ ሥር የነበሩት የባቢሎናውያን ሰራዊት ሁሉ በኢየሩሳሌም ዙሪያ ያለውን ቅጥር በሙሉ አፈረሱ። 15የዘቦቹ አዛዥ ናቡዘረዳን አንዳንድ ድኾችንና በከተማዪቱ የቀረውን ሕዝብ፣ የእጅ ጥበብ ያላቸውንና52፥15 ወይም ተራው ሕዝብ ሸሽተው ወደ ባቢሎን ንጉሥ የተጠጉትን አፈለሳቸው። 16ነገር ግን የክብር ዘበኞቹ አዛዥ ናቡዘረዳን ሌሎች የምድሪቱን ድኾች ወይን ተካዮችና ዐራሾች እንዲሆኑ አስቀራቸው።

17ባቢሎናውያን በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የነበሩትን የናስ ዐምዶች፣ ተንቀሳቃሽ ማስቀመጫዎችንና ከናስ የተሠራውን የውሃ ገንዳ ሰባበሩ፤ ናሱንም ሁሉ ወደ ባቢሎን ይዘው ሄዱ። 18ከእነዚህም ሌላ ምንቸቶቹን፣ መጫሪያዎቹን፣ መኰስተሪያዎቹን፣ ወጭቶቹን፣ ጭልፋዎቹንና ለቤተ መቅደስ አገልግሎት የሚውሉትን የናስ ዕቃዎች በሙሉ ወሰዱ። 19የክብር ዘበኞቹ አዛዥ ከንጹሕ ወርቅና ከንጹሕ ብር የተሠሩትን ዕቃዎች ሁሉ ጐድጓዳ ሳሕኖችን ጥናዎችን፣ ወጭቶችን፣ ምንቸቶችን፣ መቅረዞችን፣ ጭልፋዎችንና ለመጠጥ ቍርባን ማቅረቢያ የሚሆኑ ወጭቶችን ይዞ ሄደ።

20ንጉሥ ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ከናስ ያሠራቸው፦ ሁለቱ ዐምዶች፣ ትልቁ የውሃ ገንዳ፣ ከሥሩ ያሉት ዐሥራ ሁለት ወይፈኖችና ተንቀሳቃሽ ማስቀመጫዎች ክብደታቸው ሚዛን ከሚችለው በላይ ነበር። 21እያንዳንዱም ዐምድ ከፍታው ዐሥራ ስምንት ክንድ ዙሪያ ክቡም52፥21 ከፍታው 27 ጫማ (8.1 ሜትር) እና ዙሪያ ክቡ 18 ጫማ (5.4 ሜትር) ገደማ ነው። ዐሥራ ሁለት ክንድ ነበረ፤ ውስጡ ክፍት ስለሆነ የእያንዳንዱ ከንፈር ውፍረት አራት ጣት ነበረ። 22በአንዱ ዐምድ ዐናት ላይ ያለው የናስ ጕልላት ቁመት አምስት ክንድ52፥22 7½ ጫማ (2.3 ሜትር) ገደማ ነው። ሲሆን፣ ዙሪያውንም ሁሉ የሮማን ቅርጽ ባላቸው የናስ ጌጣጌጦች የተዋበ ነበር፤ ሌላውም ዐምድ የሮማኑን ጌጣጌጥ ጨምሮ ከዚሁ ጋር አንድ ዐይነት ነበር። 23ዘጠና ስድስቱ ሮማኖች ከጐን በቀላሉ የሚታዩ ሲሆኑ፣ በአጠቃላይ በዙሪያው ካለው ጌጥ በላይ ያለው የሮማኖች ቍጥር አንድ መቶ ነበር።

24የክብር ዘበኞቹ አዛዥ የካህናት አለቃ የነበረውን ሠራያን፣ ምክትሉንም ካህን ሶፎንያስንና ሦስቱን በር ጠባቂዎች አስሮ ወሰዳቸው፤ 25በከተማው ውስጥ ከቀሩትም ሕዝብ፣ የተዋጊዎቹ ኀላፊ የነበረውን መኰንን፣ ሰባቱን የንጉሡን አማካሪዎች ከአገሬው ሕዝብ ወታደር የሚመለምለውን መኰንን ጸሓፊና በከተማው ውስጥ የተገኙትን ሌሎች ስድሳ ሰዎች ወሰደ። 26የክብር ዘበኞቹ አዛዥ ናቡዘረዳን እነዚህን ሁሉ ይዞ የባቢሎን ንጉሥ ወደ ነበረበት ወደ ሪብላ አመጣቸው። 27ንጉሡም በሐማት ምድር በነበረችው በሪብላ ፈጃቸው።

ይሁዳም በዚህ ሁኔታ ከምድሯ በምርኮ ተወሰደች። 28ናቡከደነፆር ማርኮ የወሰደው ሕዝብ ቍጥር እንደሚከተለው ነው፦

በነገሠ በሰባተኛው ዓመት፣

ሦስት ሺሕ ሃያ ሦስት አይሁድ፤

29ናቡከደነፆር በነገሠ በዐሥራ ስምንተኛው ዓመት፣

ስምንት መቶ ሠላሳ ሁለት ሰዎች ከኢየሩሳሌም፤

30ናቡከደነፆር በነገሠ በሃያ ሦስተኛው ዓመት፣

የክብር ዘበኞች አዛዥ ናቡዘረዳን፣ ሰባት መቶ አርባ አምስት አይሁድ ማርኮ ወስዷል።

በአጠቃላይ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ሰዎች ነበሩ።

የዮአኪን መፈታት

31የይሁዳ ንጉሥ ዮአኪን በተማረከ በሠላሳ ሰባተኛው ዓመት፣ ዮርማሮዴክ52፥31 እንዲሁም አሜልማርዱክ ተብሎ ይጠራል። በባቢሎን ነገሠ፤ በዚሁ ዓመት፣ በዐሥራ ሁለተኛው ወር ከወሩም በሃያ አምስተኛው ቀን የይሁዳን ንጉሥ ዮአኪንን ዐሰበው፤ ከእስር ቤትም አወጣው፤ 32በመልካምም ቃል አናገረው፤ ከእርሱም ጋር በባቢሎን በምርኮ ከነበሩት ነገሥታት ይልቅ ከፍ ባለ የክብር ቦታ አስቀመጠው። 33ዮአኪንም እስር ቤት ለብሶት የነበረውን ልብሱን አውልቆ ጣለ፤ በቀረውም የሕይወቱ ዘመን ሁሉ ከንጉሡ ማእድ ይበላ ነበር። 34የባቢሎንም ንጉሥ፣ ዮአኪን እስኪሞት ድረስ፣ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ሳያቋርጥ በየዕለቱ ቀለቡን ይሰጠው ነበር።

Swedish Contemporary Bible

Jeremia 52:1-34

Sidkia regerar i Jerusalem

(2 Kung 24:18-20; 2 Krön 36:11-14)

1Sidkia var tjugoett år gammal när han blev kung, och han regerade i elva år i Jerusalem. Hans mor hette Hamutal och var dotter till Jeremia från Livna. 2Han gjorde det som var ont i Herrens ögon, precis som Jojakim hade gjort. 3Herren förkastade till sist i sin vrede både Jerusalem och Juda.

Jerusalems fall, förstörelse och folkets bortförande

(2 Kung 24:20—25:21; 2 Krön 36:15-20; Jer 39:1-10)

Men Sidkia gjorde uppror mot kungen i Babylonien. 4I Sidkias nionde regeringsår, på den tionde dagen i tionde månaden, kom Nebukadnessar, kungen av Babylonien, tågande med hela sin armé mot Jerusalem och belägrade det. De byggde en belägringsvall omkring staden. 5Belägringen varade ända till kung Sidkias elfte regeringsår. 6På nionde dagen i fjärde månaden var hungersnöden i staden så svår att folket inte längre hade någon mat i landet. 7Då stormades staden, och alla trupper flydde på natten genom en port som fanns mellan de båda murarna i närheten av den kungliga trädgården, medan de kaldeiska trupperna omringade staden. De flydde mot Jordandalen.

8Men den kaldeiska armén förföljde kungen och tog honom till fånga på Jerikoslätten. Alla hans män lämnade honom och skingrades. 9Kaldéerna grep honom och förde honom till den babyloniske kungen i Rivla i Hamat, där denne dömde honom. 10Den babyloniske kungen lät avrätta Sidkias söner inför hans ögon, och likaså lät han i Rivla avrätta alla de förnämsta männen i Juda. 11Sedan lät han sticka ut ögonen på Sidkia. Den babyloniske kungen band honom med kopparkedjor och förde honom till Babylon och satte honom i fängelse, och där fick han sitta ända tills han dog.

12På tionde dagen i femte månaden av den babyloniske kungen Nebukadnessars nittonde regeringsår kom Nebusaradan, befälhavaren för livgardet och en av den babyloniske kungens närmaste män, till Jerusalem. 13Han brände ner Herrens hus, kungapalatset, och även alla andra byggnader av värde i Jerusalem. 14De kaldeiska trupperna som han var befälhavare för rev ner alla Jerusalems murar. 15Nebusaradan, befälhavaren för livgardet, förde bort till exilen några av de fattigaste som var kvar i staden, tillsammans med de desertörer som hade gått över till den babyloniske kungen och de hantverkare som var kvar, 16men några av de fattigaste i landet lämnade befälhavaren Nebusaradan kvar för att sköta om vingårdar och åkrar.

17Kaldéerna högg ner kopparpelarna i Herrens hus, ställningen och kopparhavet som fanns där och tog med sig all koppar till Babylonien. 18De tog också kärlen, skovlarna, knivarna, skålarna, fyrfaten och alla kopparföremål som användes i gudstjänsten. 19Befälhavaren för livgardet tog också faten, fyrfaten, offerskålarna, grytorna, lampställen, skålarna och bägarna, allt som var av rent guld och rent silver.

20Pelarna, kopparhavet, de tolv koppartjurarna under det och ställningarna, som Salomo låtit göra till Herrens hus, bestod sammantaget av så mycket koppar att det inte gick att väga. 21Pelarna var 9 meter höga, 6 meter i omkrets och ihåliga med väggar tjocka som fyra fingrars bredd.52:21 Uppgifterna om pelarna, liksom en del andra detaljer i templet, varierar något, jfr 1 Kung 7 och 2 Krön 3-5 (spec. 3:15). Tjockleken på pelarna/pelarväggarna kan tolkas olika, men det troligaste är att pelarväggarna (även om ordet inte finns i grundtexten här) var fyra fingerbredder, dvs. ca 10 cm. 22På var och en av dem fanns ett pelarhuvud av koppar, som var 2,5 meter högt och hade ornament i form av granatäpplen som dekoration runt pelarhuvudet. Allt var gjort av koppar. 23Det fanns nittiosex granatäpplen på utsidan och sammanlagt etthundra granatäpplen i ett flätverk runtom.

24Befälhavaren för livgardet tog till fånga översteprästen Seraja och prästen närmast honom, Sefanja, samt tre av dörrvakterna. 25Från staden tog han en hovman som var befälhavare i armén, sju av kungens närmaste män i staden, och sekreteraren åt den överbefälhavare som skrev ut folket till krigstjänst, samt ytterligare sextio män i staden. 26Nebusaradan, befälhavaren för livgardet, tog dem och förde dem till den babyloniske kungen i Rivla. 27Den babyloniske kungen lät avrätta dem i Rivla i Hamat. Så fördes Juda bort från sitt land.

28Detta är de som Nebukadnessar förde bort:

under det sjunde året 3 023 judar,

29under Nebukadnessars artonde regeringsår 832 personer från Jerusalem,

30och under Nebukadnessars tjugotredje regeringsår 745 personer,

som Nebusaradan, befälhavaren för livgardet, förde bort,

sammanlagt 4 600 personer.

Jojakins benådning

(2 Kung 25:27-30)

31Under det trettiosjunde året som Judas kung Jojakin var i fångenskap, den tjugofemte dagen i tolfte månaden, samma år som Evil Merodak blev kung i Babylonien, benådade denne Jojakin, Juda kung, och släppte ut honom ur fängelset. 32Han talade vänligt till honom och gav honom den främsta platsen bland de kungar som var hos honom i Babylon. 33Jojakin fick lägga av sig fångdräkten och alltid äta vid kungens bord under resten av sitt liv. 34Så länge han levde gav den babyloniske kungen honom också ett dagligt underhåll.