ኤርምያስ 50 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 50:1-46

ስለ ባቢሎን የተነገረ መልእክት

51፥15-19 ተጓ ምብ – ኤር 10፥12-16

1እግዚአብሔር ስለ ባቢሎንና ስለ ባቢሎናውያን50፥1 ወይም ከለዳውያን፤ በ8፡25፡35 እና 45 ይመ። ምድር፣ በነቢዩ ኤርምያስ በኩል የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2“በሕዝቦች መካከል ተናገሩ፤ አስታውቁም፤

ሰንደቅ ዐላማ አንሡ፤ ዐውጁ፤

አንዳች ሳታስቀሩ፣ እንዲህ በሉ፤

‘ባቢሎን ትያዛለች፤

ቤል ይዋረዳል፤

ሜሮዳክ በሽብር ይሞላል፤

ጣዖቶቿ ይዋረዳሉ፤

አማልክቷም ይሸበራሉ።’

3ከሰሜን አንድ መንግሥት መጥቶ ይወጋታል፤

ምድሯንም ባድማ ያደርጋል፤

የሚኖርባትም አይገኝም፤

ሰዎችና እንስሳትም ሸሽተው ይሄዳሉ።

4“በዚያ ዘመን፣ በዚያ ጊዜም፤”

ይላል እግዚአብሔር

“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ በአንድነት ይመጣሉ፤

አምላካቸውንም እግዚአብሔርን በመፈለግ እያለቀሱ ይመጣሉ።

5ወደ ጽዮን የሚወስደውን መንገድ ይጠይቃሉ፤

ፊታቸውንም ወደዚያ ያቀናሉ።

መጥተውም ከቶ በማይረሳ፣

በዘላለም ቃል ኪዳን፣

ከእግዚአብሔር ጋር ይጣበቃሉ።

6“ሕዝቤ የጠፉ በጎች ሆነዋል፤

እረኞቻቸው አሳቷቸው፤

በተራሮችም ላይ እንዲቅበዘበዙ አደረጓቸው፤

በተራራና በኰረብታ ላይ ተንከራተቱ፤

ማደሪያቸውንም ረሱ።

7ያገኛቸው ሁሉ ይውጣቸዋል፤

ጠላቶቻቸውም፣ ‘እኛ በደለኞች አይደለንም፤

እነርሱ የአባቶቻቸውን ተስፋ እግዚአብሔርን፣

እውነተኛ ማደሪያቸው የሆነውን እግዚአብሔርን በድለዋል’ አሉ።

8“ከባቢሎን ሽሹ፤

የባቢሎናውያንን ምድር ልቀቁ፤

መንጋ እንደሚመራ የፍየል አውራ ሁኑ።

9የታላላቅ መንግሥታትን ማኅበር፣

ከሰሜን በባቢሎን ላይ አስነሣለሁ፤

እነርሱም በእርሷ ላይ ይሰለፋሉ፤

መጥተውም ይይዟታል።

ቀስቶቻቸው ባዶ እጃቸውን እንደማይመለሱ፣

እንደ ሥልጡን ተዋጊዎች ናቸው።

10የባቢሎን ምድር50፥10 ወይም ከላውዴዎን ትዘረፋለች፤

የሚዘርፏትም ሁሉ እስኪበቃቸው ይመዘብሯታል፤”

ይላል እግዚአብሔር

11“እናንተ ርስቴን የበዘበዛችሁ ሆይ፤

ደስ ስላላችሁና ሐሤትም ስላደረጋችሁ፣

በመስክ እንዳለች ጊደር ስለ ፈነጫችሁ፤

እንደ ድንጉላ ፈረስ ስለ አሽካካችሁ፤

12እናታችሁ እጅግ ታፍራለች፤

የወለደቻችሁም ትዋረዳለች።

እርሷም ምድረ በዳ፣ ደረቅ ምድርና በረሓ፣

ከመንግሥታትም ሁሉ ያነሰች ትሆናለች።

13ከእግዚአብሔር ቍጣ የተነሣ ባድማ ትሆናለች እንጂ፣

የሚኖርባት አይገኝም፤

በቍስሎቿም ሁሉ ምክንያት፣

በባቢሎን የሚያልፍ ሁሉ ይገረማል፤ ያፌዝባታልም።

14“እናንተ ቀስት የምትገትሩ ሁሉ፣

በባቢሎን ዙሪያ ተሰለፉ፤

አንዳች ሳታስቀሩ ፍላጾችን ስደዱባት፤

በእግዚአብሔር ላይ ኀጢአት ሠርታለችና።

15ከየአቅጣጫው ጩኹባት፤

እጇን ትሰጣለች፤ ምሽጓም ይወድቃል፤

ቅጥሮቿ ይፈርሳሉ።

ይህ የእግዚአብሔር በቀል ነውና፣

እርሷን ተበቀሏት፤

በሌሎቹ ላይ እንዳደረገችውም አድርጉባት።

16ከባቢሎን ዘር የሚዘራውን፣

በመከር ጊዜ ማጭድ የጨበጠውንም ዐጫጅ አጥፉት፤

ከአጥፊው ሰይፍ የተነሣ፣

እያንዳንዱ ወደ ገዛ ሕዝቡ ይመለስ፤

ወደ ገዛ ምድሩም ይሽሽ።

17“እስራኤል አንበሶች ያሳደዱት፣

የተበተነ መንጋ ነው፤

መጀመሪያ የአሦር ንጉሥ፣

ቦጫጭቆ በላው፤

በኋላም የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር፣

ዐጥንቱን ቈረጣጠመው።”

18ስለዚህ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“የአሦርን ንጉሥ እንደ ቀጣሁት ሁሉ፣

የባቢሎንን ንጉሥና ምድሩን እቀጣለሁ።

19እስራኤልንም ወደ መሰማሪያው እመልሰዋለሁ፤

በቀርሜሎስና በባሳን ላይ ይሰማራል፤

በኤፍሬም ተራሮችና በገለዓድም ላይ፣

እስኪጠግብ ይመገባል።

20በእነዚያ ጊዜያት፣ በዚያ ዘመን፣”

ይላል እግዚአብሔር

“የእስራኤል በደል ይፈለጋል፤

አንዳችም አይገኝም፤

የይሁዳም ኀጢአት ይፈለጋል፤

ከቶም የለም፤

እንዲተርፉ ያደረግኋቸውን ቅሬታዎች እምራለሁና።

21“የምራታይምን ምድር፣

የፋቁድ ነዋሪዎችንም፣

አሳድዷቸው፤ ግደሏቸው፤ ፈጽማችሁም አጥፏቸው፤”50፥21 አጥፏቸው ለሚለው የሚተካው የዕብራይስጡ ቃል የሚያመለክተው ነገሮችን ወይም ሰዎችን ዳግም ላይመለሱ ለእግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ መስጠትን ነው፤ 26 ይመ።

ይላል እግዚአብሔር

“ያዘዝኋችሁንም ሁሉ አድርጉ።

22በምድሪቱ የጦርነት ውካታ፣

የታላቅ ጥፋት ድምፅ ተሰማ።

23የምድር ሁሉ መዶሻ፣

እንዴት ተሰበረ! እንዴትስ ደቀቀ!

በሕዝቦች መካከል፣

ባቢሎን እንዴት ባድማ ሆነች!

24ባቢሎን ሆይ፤ ወጥመድ ዘርግቼልሻለሁ፤

አንቺም ሳታውቂ ተይዘሻል፤

እግዚአብሔርን ተገዳድረሻልና፣

ተገኘሽ፤ ተያዝሽም።

25እግዚአብሔር የመሣሪያ ግምጃ ቤቱን ከፍቷል፤

የቍጣውን የጦር ዕቃ አውጥቷል፤

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በባቢሎናውያን ምድር ሥራ አለውና።

26ከሩቅ መጥታችሁ በእርሷ ላይ ውጡ፤

ጐተራዎቿን አፈራርሱ፤

እንደ እህል ክምር ከምሯት፤

ፈጽማችሁ አጥፏት፤

ምኗም አይቅር።

27ወይፈኖቿን ሁሉ ዕረዱ፤

ወደ መታረጃም ይውረዱ!

የሚቀጡበት ጊዜ፣

ቀናቸው ደርሷልና ወዮላቸው!

28እግዚአብሔር አምላካችን የተበቀለውን፣

ስለ ቤተ መቅደሱ የተበቀለውን በቀል፣

ከባቢሎን የመጡ ኰብላዮችና ስደተኞች፣

በጽዮን የሚናገሩትን ስሟቸው።

29“ቀስት የሚገትሩትን፣

ቀስተኞችን ሁሉ በባቢሎን ላይ ጥሩ፤

አንድም ሰው እንዳያመልጥ፣

ዙሪያውን ሁሉ መሽጉ፤

የእስራኤልን ቅዱስ፣

እግዚአብሔርን አቃልላለችና፣

እንደ ሥራዋ መጠን መልሱላት፤

በሌሎች ላይ እንዳደረገችውም አድርጉባት።

30ስለዚህ ወንዶች ወጣቶቿ በየአደባባዩ ይረግፋሉ፤

በዚያ ቀን ወታደሮቿ ሁሉ ይወድቃሉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

31“አንተ ትዕቢተኛ፤ እነሆ፤ በአንተ ላይ ተነሥቻለሁ፤”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

“የምትቀጣበት ጊዜ፣

ቀንህ ደርሷልና።

32ትዕቢተኛው ይሰናከላል፤ ይወድቃልም፤

የሚያነሣውም የለም፤

በዙሪያው ያሉትን ሁሉ የሚበላ እሳት፣

በከተሞቹ ውስጥ አስነሣለሁ።”

33የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ፣

በአንድነት ተጨቍነዋል፤

የማረኳቸውም ሁሉ አጥብቀው ይዘዋቸዋል፤

ይለቅቋቸውም ዘንድ እንቢ ብለዋል።

34ነገር ግን ቤዛቸው ብርቱ ነው፤

ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤

ለምድራቸው ዕረፍትን ለመስጠት፤

ተግቶ ይሟገትላቸዋል፤

በባቢሎን የሚኖሩትን ግን ዕረፍት ይነሣቸዋል።

35“ሰይፍ በባቢሎናውያን ላይ መጣ!”

ይላል እግዚአብሔር

“በባቢሎን ነዋሪዎች ላይ፤

በባለሥልጣኖቿና በጥበበኞቿም ላይ ተመዘዘ!

36ሰይፍ በሐሰተኞች ነቢያቷ ላይ መጣ!

እነርሱም ሞኞች ይሆናሉ፤

ሰይፍ በጦረኞቿ ላይ ተመዘዘ፤

እነርሱም ይሸበራሉ።

37ሰይፍ በፈረሰኞቿና በሠረገሎቿ ላይ፣

በመካከሏ ባሉት ባዕዳን ወታደሮች ሁሉ ላይ መጣ!

እነርሱም እንደ ሴቶች ይሆናሉ፤

ሰይፍ በሀብት ንብረቷ ላይ መጣ!

ለዝርፊያም ይሆናሉ።

38ድርቅ50፥38 ወይም ሰይፍ በውሆቿ ላይ መጣ!

እነሆ፤ ይደርቃሉ፤

ምድሪቱ በፍርሀት በሚሸበሩ አማልክት፣

በጣዖትም ብዛት ተሞልታለችና።

39“ስለዚህ የምድረ በዳ አራዊትና የጅብ መኖሪያ፣

የጕጕትም ማደሪያ ትሆናለች፤

ከእንግዲህ ወዲህ ማንም አይኖርባትም፤

ከትውልድ እስከ ትውልድም የሚቀመጥባት አይገኝም።

40እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን፣

በዙሪያቸውም የነበሩትን ከተሞች ያለ ነዋሪ እንዳስቀራቸው”

ይላል እግዚአብሔር

“እንዲሁ ማንም በዚያ አይኖርም፤

የሚቀመጥባትም አይገኝም።

41“እነሆ፤ ሰራዊት ከሰሜን ይመጣል፤

አንድ ኀያል መንግሥትና ብዙ ነገሥታት፣

ከምድር ዳርቻ ተነሣሥተዋል።

42ቀስትና ጦር ይዘዋል፤

ጨካኞች ናቸው፤ ምሕረትም አያደርጉም፤

በፈረሳቸው እየጋለቡ ሲመጡ፣

ድምፃቸው እንደ ባሕር ሞገድ ይተምማል፤ ያስገመግማል።

አንቺ የባቢሎን ሴት ልጅ ሆይ፤

ለጦርነት እንደ ተዘጋጁ ተዋጊዎች ይመጡብሻል።

43የባቢሎን ንጉሥ ስለ እነርሱ ሰማ፤

እጆቹም በድን ሆኑ፤

ጭንቀት ይዞታል፤

ምጥ እንደ ያዛት ሴት ታምሟል።

44አንበሳ ከዮርዳኖስ ደኖች ድንገት ወጥቶ፣

ወደ ግጦሽ ሜዳ ብቅ እንደሚል፣

እኔም ባቢሎንን ሳይታሰብ ከምድሯ አባርራታለሁ፤

የመረጥሁትንም በእርሷ ላይ እሾማለሁ፤

እንደ እኔ ያለ ማን ነው? ማንስ ሊገዳደረኝ ይችላል?

የትኛውስ እረኛ ሊቋቋመኝ ይችላል?”

45ስለዚህ እግዚአብሔር በባቢሎን ላይ ያቀደውን፣

በባቢሎናውያንም ምድር ላይ ያሰበውን ስሙ፤

ከመንጋው ታናናሹ ተጐትቶ ይወሰዳል፤

በእነርሱም ምክንያት መሰማሪያቸውን ፈጽሞ ያጠፋል።

46በባቢሎን ውድቀት ድምፅ ትናወጣለች፤

ጩኸቷም በሕዝቦች መካከል ያስተጋባል።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

耶利米书 50:1-46

审判巴比伦的预言

1论到迦勒底人居住的巴比伦,耶和华对耶利米先知说:

2“你要向列国宣告,

你要竖起旗帜毫不隐瞒地宣告,

巴比伦要沦陷了!

它的神明彼勒必蒙羞,

米罗达必惊慌;

巴比伦的神像都蒙羞,

偶像都必惊慌。

3因为有一个来自北方的国家要攻击它,

使它荒凉、人畜绝迹。’”

4耶和华说:“那时,以色列人要与犹大人一同哭着来寻求他们的上帝耶和华。 5他们必打听前往锡安的路,朝锡安走去。他们必凭不会被遗忘的永恒之约归附耶和华。 6我的子民成了一群迷路的羊,他们的牧人使他们步入歧途,在高山丘陵间流浪,忘了自己的安歇之处。 7敌人遇见他们,就吞噬他们,还说,‘我们没有错!这是因为他们冒犯了他们真正的安歇之处——耶和华,他们祖先的盼望——耶和华。’ 8我的子民啊,你们要逃离巴比伦,离开迦勒底人的土地,要像带领羊群的公山羊一样离开。 9看啊,我要使来自北方的列强联合起来攻打巴比伦,他们要列阵攻占它,他们的勇士箭术高超,百发百中。 10他们要在迦勒底肆意掳掠,直到心满意足。这是耶和华说的。

11“抢夺我产业的巴比伦人啊,

你们欢喜快乐,

像草场上欢跳的母牛犊,

又像嘶鸣的公马。

12生养你们的母亲巴比伦将羞愧难当,

蒙受耻辱,

排在列国之末,

沦为干旱的荒漠。

13由于耶和华的愤怒,

巴比伦必无人居住,

荒凉不堪。

她满目疮痍,

令路人惊惧、嗤笑。

14弓箭手啊,你们要列阵围攻巴比伦

向她猛射,

不要吝啬箭枝,

因为她得罪了耶和华。

15你们要从四面向她吶喊,

她必投降,

她的堡垒将倾倒,

城墙将坍塌,

因为耶和华要报应她。

你们要向她复仇,

她怎样对待别人,

你们也要怎样对待她。

16你们要铲除在巴比伦撒种的和收割的。

为躲避敌人的刀剑,

人们各自逃到故土亲族那里。

17以色列人是一群被狮子驱散的羊,先被亚述王吞噬,后被巴比伦尼布甲尼撒咬碎骨头。” 18以色列的上帝——万军之耶和华说:“看啊,我要像惩罚亚述王一样惩罚巴比伦王和他的国家。 19我要带领以色列人返回他们的草场,让他们在迦密巴珊吃草,在以法莲基列的山上吃得饱足。 20那时,在以色列必找不到过犯,在犹大必找不到罪恶,因为我必赦免我保留下来的余民。这是耶和华说的。

21“你们要去攻打米拉大翁比割的居民,

照我的命令彻底消灭他们。

这是耶和华说的。

22巴比伦境内传来战争和大毁灭的声音。

23威震天下的锤子巴比伦怎么被砍断、打碎了!

它的下场令列国震惊。

24巴比伦啊,我给你设下了陷阱,

你在懵然不知中被捉住,

因为你与耶和华为敌。

25耶和华已打开祂的军库,

取出倾泻祂愤怒的兵器。

因为主——万军之耶和华要惩罚迦勒底人。

26你们要从远方前来攻打巴比伦

打开她的粮仓,

使她沦为一堆废墟,

彻底毁灭她,不留一物。

27你们要杀掉她所有的士兵,

把他们全部屠杀。

他们大祸临头了,

惩罚他们的日子到了。

28“从巴比伦逃出来的人在锡安述说我们的上帝耶和华如何报仇,为祂的圣殿报仇。

29“要召集所有的弓箭手来攻打巴比伦,在她四围扎营,不让一人漏网。要照她的所作所为报应她;她怎样对待别人,也要怎样对待她,因为她藐视耶和华——以色列的圣者。 30她的青年要倒毙街头,那时她所有的战士都要灭亡。”这是耶和华说的。

31“主——万军之耶和华说,

‘狂傲的人啊,我要与你为敌,

我惩罚你的时候到了。

32狂傲的人要踉踉跄跄,

跌倒在地,无人扶起。

我要焚烧她的城邑,

使她周围的一切化为灰烬。’”

33万军之耶和华说:“以色列人和犹大人要一同受压迫,掳走他们的人必控制他们,不肯释放他们。 34但他们的救赎主——万军之耶和华有伟大的能力,祂必为他们申冤,使他们的家园安宁,使巴比伦的居民不得安宁。”

35耶和华说:

“敌人要攻击巴比伦的居民及其首领和谋士;

36敌人要攻击巴比伦的假先知,

使他们显出愚昧;

敌人要攻击巴比伦的勇士,

使他们充满恐惧;

37敌人要攻击巴比伦人的战车战马和他们的盟军,

使他们柔弱得像妇女;

敌人要攻打他们的库房,

肆意抢夺他们的财宝。

38旱灾必临到巴比伦

使那里的河流干涸,

因为那里偶像遍地,

人们都沉迷于祭拜神像。

39“因此,巴比伦必杳无人烟,永远荒凉,成为豺狼等野兽出没之地、鸵鸟的栖身之所。 40上帝要毁灭巴比伦,像毁灭所多玛蛾摩拉及其周围的城邑一样,使那里人烟绝迹。这是耶和华说的。

41“看啊,大军要从北方而来,

一个强国及其盟军要从地极而来。

42巴比伦人啊,他们残忍无道,

手持弓箭和矛枪,

骑着战马,

列阵攻击你们,

声势如翻腾的大海。

43巴比伦王闻风丧胆,

四肢发软,

像分娩的妇人一样痛苦不堪。

44“看啊,我必在瞬间把巴比伦人赶离家园,如约旦河边丛林中跳出的狮子赶散草场的羊群。我要派我拣选的人统治这地方。谁能与我相比?谁能与我较量?哪位首领能抵抗我?”

45因此,你们要听听耶和华攻击巴比伦的策略,听听祂攻击迦勒底人的计划。他们的孩子要被拖走,他们的家园要被毁灭。 46巴比伦被毁灭的消息震动天下,呼喊声传到列国。