ኤርምያስ 48 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 48:1-47

ስለ ሞዓብ የተነገረ መልክት

48፥29-36 ተጓ ምብ – ኢሳ 16፥6-12

1ስለ ሞዓብ፤

የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ናባው ትጠፋለችና ወዮላት፤

ቂርያታይም ትዋረዳለች፤ ትያዛለችም፤

ምሽጎች48፥1 ወይም ሚሥጋብ ይደፈራሉ፤ ይፈራርሳሉም።

2ከእንግዲህ ሞዓብ አትከበርም፤

ሰዎች በሐሴቦን48፥2 ሐሴቦን የሚለው የዕብራይስጡ ቃል አነባበብ መዶለት ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል ጋር ተመሳሳይ ነው። ተቀምጠው፣

‘ኑ ያቺን አገር እናጥፋት’ ብለው ይዶልቱባታል።

መድሜን48፥2 መድሜን የሚለው የሞዓባውያን ከተማ ስም አነባበብ ጸጥ ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል ጋር ተመሳሳይ ነው። ሆይ፤ አንቺም ደግሞ ጸጥ ትደረጊያለሽ፤

ሰይፍም ያሳድድሻል።

3ከሖሮናይም የሚወጣውን ጩኸት፣

የመውደምና የታላቅ ጥፋት ድምፅ ስሙ!

4ሞዓብ ትሰበራለች፤

ልጆቿም ጩኸት ያሰማሉ።48፥4 የዕብራይስጡና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ለዞአር ያውጃሉ ይላሉ።

5ክፉኛ እያለቀሱ፣

ወደ ሉሒት ሽቅብ ይወጣሉ፤

ስለ ደረሰባቸውም ጥፋት መራራ ጩኸት እያሰሙ፣

ወደ ሖርናይም ቍልቍል ይወርዳሉ።

6ሽሹ፤ ሕይወታችሁንም አትርፉ!

በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ48፥6 ወይም እንደ አሮኤር ሁኑ።

7በድርጊታችሁና በብልጽግናችሁ ስለምትታመኑ፣

እናንተም ትማረካላችሁ፤

ካሞሽም ከካህናቱና ከመኳንንቱ ጋር፣

በምርኮ ይወሰዳል።

8በእያንዳንዱ ከተማ ላይ አጥፊ ይመጣል፤

አንድም ከተማ አያመልጥም።

እግዚአብሔር ተናግሯልና፣

ሸለቆው ይጠፋል፤

ዐምባውም ይፈርሳል።

9በርራ እንድታመልጥ፣

ለሞዓብ ክንፍ ስጧት፤

ከተሞቿም ምንም እስከማይኖርባቸው ድረስ፣

ባድማ48፥9 ወይም የተተወች ምድር እንድትሆን/በሞዓብ ላይ ጨው ነስንሱባት ይሆናሉ።

10የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያከናውን ርጉም ይሁን፤

ሰይፉን ደም ከማፍሰስ የሚከላከል የተረገመ ይሁን፤

11“ሞዓብ በአንቡላው ላይ እንዳረፈ የወይን ጠጅ፣

ከልጅነት ጀምሮ የተረጋጋ ነበረ፤

ከዕቃ ወደ ዕቃ አልተገላበጠም፤

በምርኮም አልተወሰደም፤

ቃናው እንዳለ ነው፤

መዐዛውም አልተለወጠም።

12ስለዚህ ዕቃውን የሚገለብጡ ሰዎችን

የምልክበት ጊዜ ይመጣል፤”

ይላል እግዚአብሔር

“እነርሱም ይደፉታል፤

ዕቃውን ባዶ ያስቀራሉ፤

ማንቈርቈሪያዎቹንም ይሰባብራሉ።

13የእስራኤል ቤት፤

በቤቴል ታምኖ እንዳፈረ ሁሉ፣

ሞዓብም በካሞሽ ያፍራል።

14“እናንተ፣ ‘እኛ ተዋጊዎች ነን፤

በጦርነትም ብርቱ ነን’ ልትሉ እንዴት ቻላችሁ?

15ሞዓብ ትጠፋለች፤ ከተሞቿም ይወረራሉ፤

ምርጥ ወጣቶቿም ወደ መታረድ ይወርዳሉ፤”

ይላል ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የሆነው ንጉሥ፤

16“የሞዓብ ውድቀት ተቃርቧል፤

ጥፋቱም ፈጥኖ ይመጣበታል።

17በዙሪያው የምትኖሩ ሁሉ፤

ዝናውን የምታውቁ ሁሉ አልቅሱለት፤

‘ብርቱው ከዘራ፣

የከበረው በትር እንዴት ሊሰበር ቻለ’ በሉ።

18“ሞዓብን የሚያጠፋ፣

በአንቺ ላይ ይመጣልና፤

የተመሸጉ ከተሞችሽንም ያጠፋልና፤

አንቺ የዲቦን ሴት ልጅ ሆይ፤

ከክብርሽ ውረጂ፤

በደረቅም መሬት ተቀመጪ።

19አንቺ በአሮዔር የምትኖሪ ሆይ፤

በመንገድ አጠገብ ቆመሽ ተመልከቺ፤

የሚሸሸውን ወንድ፣ የምታመልጠውንም ሴት፣

‘ምን ተፈጠረ?’ ብለሽ ጠይቂ።

20ሞዓብ በመፍረሱ ተዋርዷል፤

ዋይ በሉ፤ ጩኹ፤

የሞዓብን መደምሰስ፣

በአርኖን አጠገብ አስታውቁ።

21ፍርድ በዐምባው ምድር፦

በሖሎን፣ በያሳና በሜፍዓት ላይ፣

22በዲቦን፣ በናባውና በቤት ዲብላታይም ላይ፣

23በቂርያታይም፣ በቤት ጋሙልና በቤትምዖን ላይ፣

24በቂርዮትና በባሶራ ላይ፤

በሩቅና በቅርብ ባሉት በሞዓብ ከተሞች ሁሉ ላይ መጥቷል።

25የሞዓብ ቀንድ48፥25 ቀንድ እዚህ ቦታ ኀይልን በትእምርትነት ይመለከታል። ተቈርጧል፤

እጁም ተሰባብሯል፤”

ይላል እግዚአብሔር

26እግዚአብሔርን ንቋልና፣

ሞዓብን በመጠጥ አስክሩት።

ሞዓብ በትፋቱ ላይ ይንከባለል፤

ለመዘባበቻም ይሁን።

27በእስራኤል ላይ ስታላግጥ አልነበረምን?

ስለ እርሷ በተናገርህ ቍጥር፣

እያቃለልሃት ራስህን የምትነቀንቀውስ፣

ከሌቦች ጋር ስትሰርቅ ተይዛለችን?

28እናንተ በሞዓብ የምትኖሩ ሆይ፤

ከከተማ ወጥታችሁ በዐለት መካከል ኑሩ፤

በገደል አፋፍ ላይ ጐጆዋን እንደምትሠራ፣

እንደ ርግብ ሁኑ።

29“ስለ ሞዓብ ትዕቢት፣

ስለ እብሪቱና ስለ ኵራቱ፣

ስለ ትምክሕቱና ስለ መጓደዱ፣

ስለ ልቡም ማበጥ ሰምተናል።

30መዳፉን ዐውቃለሁ፤ ነገር ግን ከንቱ ነው፤”

ይላል እግዚአብሔር

“ጕራውም ፋይዳ አይኖረውም።

31ስለዚህ ለሞዓብ አለቅሳለሁ፤

ለሞዓብ ምድር ሁሉ ዋይ እላለሁ፤

ለቂርሔሬስ ሰዎችም የልቅሶ ድምፅ አሰማለሁ።

32የሴባማ ወይን ሆይ፤

ለኢያዜር ካለቀስሁት እንኳ ይልቅ አለቅስልሻለሁ፤

ቅርንጫፎችሽ እስከ ባሕሩ ተዘርግተዋል፤

እስከ ኢያዜርም ደርሰዋል፤

ለመከር በደረሰው ፍሬሽና በወይንሽ ላይ፣

አጥፊው መጥቷል።

33ከሞዓብ የአትክልት ቦታና ዕርሻ፣

ሐሤትና ደስታ ርቋል፤

የወይን ጠጅ ከመጭመቂያው እንዳይወርድ አድርቄዋለሁ፤

በእልልታ የሚጨምቀውም አይገኝም፤

በዚያ ድምፅ ቢሰማም፣

የእልልታ ድምፅ አይደለም።

34“ከሐሴቦን እስከ ኤልያሊና እስከ ያሀጽ፣

ከዞዓር እስከ ሖሮናይም፣ እስከ ዔግላት ሺሊሺያ ድረስ፣

ጩኸታቸው ከፍ ብሎ ይሰማል፤

የኔሞሬም ውሃ እንኳ ደርቋልና።

35በመስገጃ ኰረብቶች ላይ የሚሠዉትን፣

ለአማልክታቸው የሚያጥኑትን፣

ከሞዓብ አጠፋለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

36“ስለዚህ ልቤ ለሞዓብ እንደ ዋሽንት ያንጐራጕራል፤

ለቂርሔሬስ ሰዎችም እንደ ዋሽንት ያንጐራጕራል።

ያከማቹት ንብረት ጠፍቷልና።

37የእያንዳንዱ ሰው ራስ፣

ጢምም ሁሉ ተላጭቷል፤

እጅ ሁሉ ተቸፍችፏል፤

ወገብም ሁሉ ማቅ ታጥቋል።

38በሞዓብ ቤቶች ጣራ ሁሉ ላይ፣

በሕዝብም አደባባዮች፣

ሐዘን እንጂ ሌላ የለም፤

እንደማይፈለግ እንስራ፣

ሞዓብን ሰብሬአለሁና፤”

ይላል እግዚአብሔር

39“እንዴት ተንኰታኰተ! ምንኛስ አለቀሱ!

ሞዓብ እንዴት ዐፍሮ ጀርባውን አዞረ!

ሞዓብ የመሰደቢያ፣

በዙሪያው ላሉትም ሁሉ የሽብር ምልክት ሆነ።”

40እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ እንደ ንስር ተወርውሮ ይወርድበታል፤

ክንፎቹንም በሞዓብ ላይ ይዘረጋል።

41ከተሞቹ48፥41 ወይም ቂርያት ይወረራሉ፤

ምሽጎቹም ይያዛሉ፤

በዚያን ቀን የሞዓብ ጦረኞች ልብ፣

በምጥ እንደ ተያዘች ሴት ልብ ይሆናል።

42ሞዓብ እግዚአብሔርን አቃልሏልና ይጠፋል፤

መንግሥትነቱም ይቀራል።

43የሞዓብ ሕዝብ ሆይ፤

ሽብርና ጕድጓድ፣ ወጥመድም ይጠብቅሃል፤”

ይላል እግዚአብሔር

44“ከሽብር የሚሸሽ ሁሉ፣

ጕድጓድ ውስጥ ይገባል፤

ከጕድጓዱም የሚወጣ፣

በወጥመድ ይያዛል፤

በሞዓብ ላይ፣

የቅጣቱን ዓመት አመጣለሁና፣”

ይላል እግዚአብሔር

45“የሞዓብን ግንባር፣

የደንፊዎችን ዐናት የሚያቃጥል፣

እሳት ከሐሴቦን፣

ነበልባል ከሴዎን ቤት ወጥቷልና፤

ኰብላዮች በሐሴቦን ጥላ ሥር፣

ተስፋ ቈርጠው ቆመዋል።

46ሞዓብ ሆይ፤ ወዮልህ!

የካሞሽ ሕዝብ ተደምስሷል፤

ወንዶች ልጆችህ በምርኮ ተወስደዋል፤

ሴቶች ልጆችህም ተግዘዋል።

47“ነገር ግን የኋላ ኋላ፣

የሞዓብን ምርኮ እመልሳለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

በሞዓብ ላይ የተወሰነው ፍርድ ይኸው ነው።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

耶利米书 48:1-47

关于摩押的预言

1论到摩押以色列的上帝——万军之耶和华说:

尼波大祸临头了!

它必被毁灭;

基列亭必蒙羞沦陷,

堡垒必蒙羞被毁。

2摩押不再受称赞,

敌人在希实本图谋害她,说,

‘来吧!我们铲除这个国家。’

玛得缅啊,你也将被敌人追杀,

变得死寂无声。

3“从何罗念传来呼喊声,

‘荒凉了!毁灭了!’

4摩押灭亡了,

她的孩童放声哀哭。

5摩押人痛哭着走上鲁希坡

他们在何罗念的山坡下听见悲惨的哀号。

6逃命吧!藏到旷野去吧!

7摩押啊,你要被攻占,

因为你倚仗自己的成就和财富。

你的神明基抹及供奉它的祭司和官长都要被掳去。

8所有的城邑必被毁灭,

无一幸免;

山谷遭践踏,

平原被蹂躏。

这是耶和华说的。

9“给摩押翅膀让她飞走吧48:9 给摩押翅膀让她飞走吧,”或译作“给摩押竖起墓碑吧,因为她将被毁灭”或“在摩押撒盐吧,因为她将被毁灭”。

因为她的城邑将沦为废墟,

杳无人迹。

10不殷勤地为耶和华做工,

不挥刀斩杀摩押人的必受咒诅。

11摩押自幼常享安逸,

从未被掳到别处,

好像沉淀的酒没有被从这缸倒到那缸,

味道依旧,香气未变。

12“不过,看啊,时候将到,我要派倒酒的人去把她倒出来,倒空酒缸,把缸打碎。这是耶和华说的。 13摩押人必因他们的神明基抹而羞愧,就像以色列人因信靠伯特利的神像而羞愧一样。

14摩押人啊,

你们怎能自称为骁勇善战的英雄呢?

15摩押要灭亡了,

她的城邑要被摧毁,

她最勇敢的青年将被杀戮。

这是名叫万军之耶和华的君王说的。

16摩押快要被毁灭了,

灾难就要来临。

17她的近邻和知道她名望的人啊,

你们都要为她哀悼,

‘那强大、辉煌的权势竟然崩溃了!’

18底本的居民啊,

你们要从荣耀的位子上下来,

坐在干旱的地上,

因为毁灭摩押的要来攻击你们,

摧毁你们的堡垒。

19亚罗珥的居民啊!

你们要站在路旁观望,

询问逃难的男女究竟发生了什么事。

20你们会得知摩押沦陷了,

她羞愧难当。

你们哀伤痛哭吧!

你们要在亚嫩河边宣告,

摩押灭亡了!’

21“审判降临在平原上的何伦雅杂米法押22底本尼波伯·低比拉太音23基列亭伯·迦末伯·米恩24加略波斯拉摩押各地的城邑。 25摩押的权势被粉碎了,她的力量被摧毁了。这是耶和华说的。

26“你们要灌醉她,因为她藐视耶和华。她必在自己的呕吐物中打滚,被人耻笑。 27摩押啊,你不是曾经嘲笑以色列吗?以色列难道是强盗吗?你每次谈到她总是不屑地摇头。

28摩押人啊,

你们要离开城邑,住到岩洞里,

像鸽子在岩缝里筑巢一样。

29我们听说摩押人傲气冲天,

他们狂妄自大、心中高傲。

30我知道狂傲的摩押不过是外强中干,

她的夸耀不过是虚张声势。

这是耶和华说的。

31因此,我要为她哀号,

摩押人痛哭,

吉珥·哈列设人悲伤。

32西比玛的葡萄树啊,

我为你们比为雅谢人哭得更悲痛!

你们的枝条虽然延伸到大海,

一直到雅谢

但毁灭者已在蹂躏你们夏日的果子了!

33摩押的沃土上再没有欢喜快乐的声音。

我使榨酒池不出酒,

再没有踩踏葡萄的欢呼声,

欢呼被呐喊取代。

34“哀哭声从希实本传到以利亚利雅杂,又从琐珥传到何罗念伊基拉·施利施亚,因为连宁林的水也干涸了。” 35耶和华说:“我要灭绝摩押那些在丘坛献祭和向假神烧香的人。 36我的心为摩押悲鸣,好像凄凉的箫声;我的心为吉珥·哈列设人悲鸣,他们的一切财富都消失了。 37他们都悲哀地剃去发须,割伤双手,腰束麻布。 38摩押境内的屋顶和街头巷尾,哀声处处可闻,因为我已把摩押打得粉碎,好像打碎没人要的器皿。这是耶和华说的。 39摩押破碎不堪!她嚎啕痛哭,羞愧难当,令四围的人嗤笑、惊惧。”

40耶和华说:

“看啊,敌人必像展翅疾飞的大鹰一样来攻击摩押

41他们要攻取城池,占领堡垒。

那时,摩押的勇士像临盆的妇人一样心惊胆战。

42摩押必被摧毁,彻底灭亡,

因为她藐视耶和华。

43摩押人啊!

你们要充满恐惧,

陷入深坑和网罗。

这是耶和华说的。

44逃过惊恐的必落入深坑,

爬出深坑的必陷入网罗,

因为我惩罚摩押的时候到了。

这是耶和华说的。

45“逃难的人来到希实本

无助地站着,

因为希实本烈焰熊熊,

西宏的城火光冲天,

烧毁了摩押和其中的叛逆之人。

46基抹神明的摩押人啊,

你们有祸了!

你们灭亡了!

你们的儿女都被掳去了。

47但将来,我要使你们重整家园。

这是耶和华说的。”

摩押的审判到此为止。