ኤርምያስ 46 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 46:1-28

ስለ ግብፅ የተነገረ መልእክት

1ስለ ሕዝቦች ወደ ነቢዩ ወደ ኤርምያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

2ስለ ግብፅ፤ በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት በአራተኛው ዓመት በኤፍራጥስ ወንዝ በከርከሚሽ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ባሸነፈው በግብፅ ንጉሥ በፈርዖን ኒካዑ ሰራዊት ላይ የተነገረ መልእክት ይህ ነው፤

3“ትልቁንና ትንሹን ጋሻ አዘጋጁ፤

ለውጊያም ውጡ!

4ፈረሶችን ጫኑ፤

በላያቸውም ተቀመጡ!

የራስ ቍር ደፍታችሁ፣

በየቦታችሁ ቁሙ፤

ጦራችሁን ወልውሉ፤

ጥሩራችሁን ልበሱ!

5ነገር ግን ይህ የማየው ምንድን ነው?

እጅግ ፈርተዋል፤

ወደ ኋላ እያፈገፈጉ ነው፤

ብርቱ ጦረኞቻቸው ተሸንፈዋል፤

ዘወር ብለውም ሳያዩ፣

በፍጥነት እየሸሹ ነው፤

በየቦታውም ሽብር አለ፣”

ይላል እግዚአብሔር

6“ፈጣኑ መሸሽ አይችልም፤

ብርቱውም አያመልጥም፤

በሰሜን በኤፍራጥስ ወንዝ አጠገብ፣

ተሰናክለው ወደቁ።

7“ይህ እንደ አባይ ወንዝ ሙላት የሚዘልለው፣

እንደ ደራሽ ወንዝ የሚፈስሰው ማነው?

8ግብፅ እንደ አባይ ወንዝ ሙላት ይዘልላል፤

እንደ ደራሽ ወንዝ ይወረወራል፤

‘እወጣለሁ፤ ምድርንም እሸፍናለሁ፤

ከተሞችንና ነዋሪዎቻቸውን አጠፋለሁ’ ይላል።

9ፈረሶች ሆይ ዘልላችሁ ውጡ፤ ሠረገሎችም ሸምጥጡ፤

ጋሻ ያነገባችሁ የኢትዮጵያና46፥9 የላይኛው አባይ አካባቢ ነው የፉጥ ሰዎች፣

ቀስት የገተራችሁ የሉድ ጀግኖች፣

እናንተ ብርቱ ጦረኞች ተነሥታችሁ ዝመቱ።

10ያ ቀን ግን የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔር ቀን ነው፤

ጠላቶቹን የሚበቀልበት የበቀል ቀን።

ሰይፍ እስኪጠግብ ድረስ ይበላል፤

ጥማቱም እስኪረካ ድረስ ደም ይጠጣል።

በሰሜን ምድር በኤፍራጥስ ወንዝ አጠገብ፣

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር መሥዋዕት አዘጋጅቷልና።

11“ድንግሊቱ የግብፅ ሴት ልጅ ሆይ፤

ወደ ገለዓድ ውጪ፤ የሚቀባ መድኀኒትም አምጪ፤

ነገር ግን መድኀኒት የምታበዢው በከንቱ ነው፤

ፈውስ አታገኚም።

12ሕዝቦች ኀፍረትሽን ይሰማሉ፤

ልቅሶሽም ምድርን ይሞላል።

ጦረኛ በጦረኛው ይደናቀፋል፤

ሁለቱም ተያይዘው ይወድቃሉ።”

13የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር መጥቶ ግብፅን እንደሚወጋ፣ እግዚአብሔር ለነቢዩ ለኤርምያስ የተናገረው መልእክት ይህ ነው፤

14“ይህን በግብፅ ተናገር፤ በሚግዶልም አሰማ፤

በሜምፎስና46፥14 ዕብራይስጡ ኖፍ ይላል፤ 19 ይመ። በጣፍናስም እንዲህ ብለህ ዐውጅ፤

‘በቦታችሁ ቁሙ፤ ተዘጋጁም፤

በዙሪያችሁ ያሉትን ሰይፍ ይበላቸዋልና።’

15ጦረኞችህ ለምን ተዘረሩ?

እግዚአብሔር ገፍትሮ ስለሚጥላቸው መቆም አይችሉም።

16ደጋግመው ይሰናከላሉ፣

አንዱም በሌላው ላይ ይወድቃል፤

‘ተነሡ እንሂድ፤

ወደ ሕዝባችንና ወደ ትውልድ አገራችን እንመለስ፤

ከጠላትም ሰይፍ እናምልጥ’ ይላሉ።

17በዚያም የግብፅን ንጉሥ ፈርዖንን፣

‘በተሰጠው ዕድል ያልተጠቀመ፣

አለሁ አለሁ ባይ ደንፊ!’ ብለው ይጠሩታል።”

18ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የሆነው ንጉሡ እንዲህ ይላል፤

“በሕያውነቴ እምላለሁ”።

በተራሮች መካከል ያለውን የታቦር ተራራ የሚመስል፣

ባሕርም አጠገብ ያለውን የቀርሜሎስ ተራራ የሚመስል አንድ የሚመጣ አለ።

19እናንተ በግብፅ የምትኖሩ ሆይ፤

በምርኮ ለመወሰድ ጓዛችሁን አሰናዱ፤

ሜምፎስ ፈራርሳ፣

ሰው የማይኖርባት ባድማ ትሆናለችና።

20“ግብፅ ያማረች ጊደር ናት፤

ነገር ግን ተናዳፊ ዝንብ

ከሰሜን ይመጣባታል።

21ቅጥረኞች ወታደሮቿም

እንደ ሠቡ ወይፈኖች ናቸው፤

የሚቀጡበት ጊዜ ስለ ደረሰ፣

ጥፋታቸው ስለ ተቃረበ፣

እነርሱም ወደ ኋላ ተመልሰው በአንድነት ይሸሻሉ፤

በቦታቸውም ጸንተው ሊቋቋሙ አይችሉም።

22ጠላት ገፍቶ ሲመጣባት፣

ግብፅ እንደሚሸሽ እባብ ታፏጫለች፤

ዛፍ እንደሚቈርጡ ሰዎች፣

መጥረቢያ ይዘው ይመጡባታል።

23ጥቅጥቅ ጫካ ቢሆንም፣ ደኗን ይመነጥራሉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

“ብዛታቸው እንደ አንበጣ ነው፤

ሊቈጠሩም አይችሉም።

24የግብፅ ሴት ልጅ ለኀፍረት ትጋለጣለች፤

ለሰሜን ሕዝብም ዐልፋ ትሰጣለች።”

25የእስራኤል አምላክ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በቴብስ46፥25 ወይም ኖእ አምላክ በአሞን ላይ፣ በፈርዖን ላይ፣ በግብፅና በአማልክቷ ላይ፣ በነገሥታቷም ላይ፣ እንዲሁም በፈርዖን በሚታመኑት ላይ ቅጣት አመጣለሁ፤ 26ነፍሳቸውን ለሚሹት ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆርና ለጦር መኰንኖቹ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ፤ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ግብፅ እንደ ቀድሞው ዘመን የሰው መኖሪያ ትሆናለች” ይላል እግዚአብሔር

27“አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፤ አትፍራ፤

እስራኤል ሆይ፤ አትሸበር፤

አንተን ከሩቅ ስፍራ፣

ዘርህንም ተማርኮ ከሄደበት ምድር አድናለሁ።

ያዕቆብም ተመልሶ በሰላምና በርጋታ ይቀመጣል፤

የሚያስፈራውም አይኖርም።

28አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፤ አትፍራ፤

እኔ ከአንተ ጋር ነኝና” ይላል እግዚአብሔር

“አንተን የበተንሁበትን ሕዝብ ሁሉ፣

ፈጽሜ ባጠፋም እንኳ፣

አንተን ግን ፈጽሜ አላጠፋህም።

ተገቢውን ቅጣት እሰጥሃለሁ እንጂ፣

ያለ ቅጣት አልተውህም።”

Het Boek

Jeremia 46:1-28

Gods boodschap aan de volken

1Hier volgt wat de Here aan Jeremia doorgaf met betrekking tot andere volken.

2De Egyptenaren

Dit is wat de Here doorgaf over Egypte, na de slag bij Karkemis, waar het leger van farao Necho bij de Eufraat werd verslagen door koning Nebukadnezar van Babel. Dat gebeurde in het vierde regeringsjaar van koning Jojakim van Juda, de zoon van Josia: 3‘Neem al uw schilden en trek ten strijde, Egyptenaren! 4Maak uw paarden klaar en stijg op. Neem uw posities in, zet uw helmen op, slijp uw speren en doe uw wapenrusting aan. 5Maar kijk! Het Egyptische leger slaat in paniek op de vlucht, verslagen rennen de dapperste soldaten weg zonder achterom te kijken. Ja, ze zullen verlamd zijn van angst,’ zegt de Here. 6‘Zelfs de snelsten kunnen niet ontsnappen, evenmin als de sterksten. In het noorden, langs de Eufraat, zullen zij struikelen en vallen. 7Wat is dat voor een machtig leger, oprijzend als de Nijl, die bij vloed al het land overstroomt? 8Het is het Egyptische leger dat brult dat het de aarde zal overstromen als een stormvloed, de steden zal verwoesten en elke tegenstander vernietigen. 9Kom dan maar, paarden, strijdwagens en dappere soldaten van Egypte! Kom op, mannen uit Kus en Put, die het schild hanteren en de boog spannen! 10Want dit is de dag van de Here, de God van de hemelse legers, een dag van wraak op zijn vijanden. Het zwaard zal verslinden tot het doordrenkt, ja, dronken is van uw bloed, want de Here, de God van de hemelse legers, zal vandaag slachtoffers maken in het noordelijke land aan de oevers van de Eufraat! 11Ga naar Gilead om zalf te halen, volk van Egypte! Maar al gebruikt u nog zoveel geneesmiddelen, voor u bestaat geen genezing. 12De volken hebben gehoord over uw schande. De aarde is gevuld met uw kreten van vertwijfeling en verslagenheid, uw beste soldaten zullen over elkaar struikelen en samen vallen.’

13Toen gaf de Here Jeremia de volgende boodschap over de komst van koning Nebukadnezar van Babel om Egypte aan te vallen: 14‘Roep het om in Egypte, maak het bekend in de steden Migdol, Memfis en Tachpanhes! Maak u klaar voor de strijd, want het vernietigende zwaard zal iedereen verslinden. 15Waarom zijn uw machtige soldaten gevallen en niet weer opgestaan? Omdat de Here hen neersloeg. 16Velen zijn gestruikeld en vallen over elkaar heen. Dan zal de rest van dat leger zeggen: “Laten wij teruggaan naar ons vaderland, weg van deze slachtpartij!” 17Thuisgekomen roepen ze: “De farao is een opschepper, hij heeft zijn kans niet gegrepen.” 18Zo waar Ik leef,’ zegt de koning, de Here van de hemelse legers, ‘zo zeker als de berg Tabor uitsteekt boven andere bergen en zo zeker als de berg Karmel aan de kust ligt, zo zeker wordt Egypte overweldigd! 19Pak uw bezittingen bij elkaar, maak u klaar om in ballingschap te gaan, inwoners van Egypte, want de stad Memfis zal totaal worden verwoest en zonder overlevenden worden achtergelaten. 20-21 Egypte lijkt op een mooie jonge koe, maar een horzel uit het noorden komt op haar af! Zelfs haar befaamde huurlingen lijken nu op vetgemeste kalveren. Zij draaien zich om en zetten het op een lopen, want dit is een rampzalige dag voor Egypte, de tijd voor de straf. 22-23 Sissend als een wegglijdende slang vlucht Egypte, het aanvallende leger marcheert binnen. Talloze soldaten slaan uw mensen neer als houthakkers die een bos omkappen. 24Het volk van Egypte is verslagen, in de handen gevallen van het volk uit het noorden.’ 25De Here van de hemelse legers, de God van Israël, zegt: ‘Ik zal Amon, de god van Thebe, en alle andere Egyptische goden straffen. Ook de farao zal Ik straffen, evenals allen die op hem vertrouwen. 26Ik zal hen in handen geven van degenen die hen naar het leven staan, in handen van koning Nebukadnezar van Babel en zijn leger. Pas lang daarna zal het land zich weer herstellen van de door de oorlog aangerichte verwoestingen.

27Maar u hoeft niet bang te zijn, volk van Mij dat terugkeert naar uw eigen land. Wees niet angstig, want Ik zal u uit dat verre land bevrijden en uw kinderen uit de gevangenschap terugbrengen. Ja, Israël zal terugkeren en rust krijgen. Niets zal haar nog bang maken. 28Wees niet bang, mijn dienaar Jakob,’ zegt de Here, ‘want Ik ben bij u. De volken waarheen Ik u in ballingschap gestuurd heb, zal Ik vernietigen, maar u verwoest Ik niet volledig. Ik zal u straffen, maar niet meer dan nodig is om u op het rechte pad te houden.’