ኤርምያስ 42 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 42:1-22

1የቃሬያን ልጅ ዮሐናንና የሆሻያን ልጅ ያእዛንያን42፥1 የዕብራይስጡና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (43፥2 ይመ) አዛርያ ይላሉ። ጨምሮ፣ የጦር መኰንኖች ሁሉ እንዲሁም ሕዝቡ ሁሉ ከትንሹ እስከ ትልቁ ቀርበው፣ 2ነቢዩ ኤርምያስን እንዲህ አሉት፤ “ቀድሞ ብዙዎች ነበርን አሁን እንደምታየን ግን የቀረነው ጥቂት ነን፤ ስለዚህ እባክህ ልመናችንን ስማ፤ ለዚህ ለተረፈው ሕዝብ ሁሉ ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ። 3አምላክህ እግዚአብሔር ወዴት መሄድ እንዳለብንና ምን ማድረግ እንደሚገባን እንዲነግረን ጸልይልን።”

4ነቢዩ ኤርምያስም፣ “ሰምቻችኋለሁ፤ እንዳላችሁት ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር በርግጥ እጸልያለሁ፤ እግዚአብሔር ያለኝን ሁሉ አንዳች ሳላስቀር እነግራችኋለሁ” አላቸው።

5እነርሱም ኤርምያስን እንዲህ አሉት፤ “እግዚአብሔር አምላክህ በአንተ በኩል የሚለውን ነገር ሁሉ ባናደርግ፣ እግዚአብሔር ራሱ በእኛ ላይ እውነተኛና ታማኝ ምስክር ይሁን። 6አምላካችንን እግዚአብሔርን በመታዘዝ መልካም ይሆንልን ዘንድ ነገሩ ቢስማማንም ባይስማማንም፣ አንተን ወደ እርሱ የምንልክህን አምላካችንን እግዚአብሔርን እንታዘዛለን።”

7ከዐሥር ቀን በኋላ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ መጣ። 8ስለዚህ የቃሬያን ልጅ ዮሐናንንና፣ ከእርሱም ጋር የነበሩትን የጦር መኰንኖች ሁሉ እንዲሁም ሕዝቡን ሁሉ ከትንሽ እስከ ትልቅ ጠርቶ፤ 9እንዲህ አላቸው፤ “ልመናችሁን በፊቱ እንዳቀርብ ወደ እርሱ የላካችሁኝ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ 10‘ባመጣሁባችሁ ጥፋት ዐዝኛለሁና፣ በዚህች ምድር ብትቀመጡ እሠራችኋለሁ እንጂ አላፈርሳችሁም፤ እተክላችኋለሁ እንጂ አልነቅላችሁም። 11አሁን የሚያስፈራችሁን የባቢሎንን ንጉሥ አትፍሩ፤ አድናችሁ ዘንድ ከእጁም አስጥላችሁ ዘንድ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና አትፍሩ ይላል እግዚአብሔር12እርሱ እንዲምራችሁና ወደ አገራችሁ እንዲመልሳችሁ እኔ እምራችኋለሁ።’

13“እናንተ ግን፤ ‘በዚህች ምድር አንቀመጥም’ ብትሉና አምላካችሁን እግዚአብሔርን ባትታዘዙ፣ 14ደግሞም፣ ‘ጦርነት ወደማናይበት፣ የመለከት ድምፅ ወደማንሰማበትና ወደማንራብበት ወደ ግብፅ ምድር ሄደን በዚያ እንኖራለን’ ብትሉ፣ 15እንግዲህ የይሁዳ ቅሬታ ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ወደ ግብፅ ለመሄድ ወስናችሁ እዚያ ለመቀመጥ ብትሄዱ፣ 16የፈራችሁት ሰይፍ በዚያ ያገኛችኋል፤ የሠጋችሁበት ራብ እስከ ግብፅ ድረስ ተከትሏችሁ ይመጣል፤ በዚያም ትሞታላችሁ። 17በዚያም ለመኖር ወደ ግብፅ ለመሄድ የወሰኑ ሁሉ በሰይፍ፣ በራብና በቸነፈር በርግጥ ይሞታሉ፤ ከማመጣባቸውም ጥፋት አንድ እንኳ የሚተርፍ ወይም የሚያመልጥ አይገኝም።’ 18የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፣ ‘ቍጣዬና መዓቴ በኢየሩሳሌም በሚኖሩት ሁሉ ላይ እንደ ፈሰሰ፣ እንዲሁ ወደ ግብፅ በገባችሁ ጊዜ መዓቴ በእናንተ ላይ ይፈስሳል፤ እናንተም የመነቀፊያና የድንጋጤ፣ የመረገሚያና የመዘባበቻ ምልክት ትሆናላችሁ፤ ይህንም ስፍራ ዳግመኛ አታዩም።’

19“እናንተ የይሁዳ ቅሬታ ሆይ፤ እግዚአብሔር፤ ‘ወደ ግብፅ አትሂዱ’ ብሏችኋል፤ እኔም ዛሬ እንዳስጠነቀቅኋችሁ በርግጥ ዕወቁ፤ 20‘ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ጸልይልን፤ እርሱ ያለህን ሁሉ ንገረን፤ እኛም እንታዘዛለን’ ብላችሁ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር በላካችሁኝ ጊዜ ሕይወታችሁን የሚያጠፋ ስሕተት42፥20 ወይም በልባችሁ ስሕተት ሠራችሁ ፈጸማችሁ። 21እነሆ፤ ዛሬ በግልጥ ነገርኋችሁ፤ እናንተ ግን እግዚአብሔር አምላካችሁ ልኮኝ የነገርኋችሁን ሁሉ አሁንም አልታዘዛችሁም፤ 22እንግዲህ ሄዳችሁ ልትኖሩበት በፈለጋችሁት ስፍራ በሰይፍ፣ በራብና በቸነፈር እንደምትሞቱ በርግጥ ዕወቁ።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

耶利米書 42:1-22

耶利米警告猶大人勿去埃及

1加利亞的兒子約哈難何沙雅的兒子耶撒尼亞和其他將領及各階層的民眾前來, 2耶利米先知說:「求你答應我們的懇求,為我們這些餘民向我們的上帝耶和華祈求。你也看見了,我們本來人數眾多,現在卻寥寥無幾。 3願你的上帝耶和華指示我們該去哪裡,該做什麼。」 4耶利米先知說:「好。我必照你們說的向你們的上帝耶和華祈求,並把祂的話毫不隱瞞地告訴你們。」 5他們說:「倘若我們不照你的上帝耶和華說的去做,願誠實可靠的耶和華作證指控我們! 6不論我們的上帝耶和華說什麼,我們都願意聽從。我們若聽祂的話,就必亨通。」

7十天之後,耶和華的話傳給了耶利米8耶利米便召集加利亞的兒子約哈難和眾將領及各階層的民眾, 9對他們說:「你們讓我向以色列的上帝耶和華祈求,耶和華這樣說, 10『如果你們留在這地方,我必扶持你們,決不毀滅你們;我必栽培你們,決不剷除你們。因為我為降在你們身上的災禍而難過。 11不要懼怕巴比倫王,不要怕他,因為我必與你們同在,拯救你們脫離他的權勢。這是耶和華說的。 12我必憐憫你們,也要讓他憐憫你們,使你們重歸故土。』 13然而,如果你們不聽你們的上帝耶和華的話,不留在這地方, 14非要去埃及住,以為那裡沒有戰爭,聽不見號角聲,也不會忍饑挨餓, 15那麼,你們這些猶大的餘民就要聽聽耶和華的話。以色列的上帝——萬軍之耶和華說,『如果你們決意去埃及住, 16你們所害怕的戰爭和饑荒必緊緊地跟著你們。你們必死在埃及17凡決意去埃及住的人必要死於戰爭、饑荒和瘟疫,無人能逃脫我降的災禍。』

18以色列的上帝——萬軍之耶和華說,『我曾把烈怒傾倒在耶路撒冷人身上,如果你們去埃及,我也要把我的怒氣傾倒在你們身上。你們的下場將很可怕,被人責罵、咒詛和羞辱,再也見不到故土。』 19猶大的餘民啊,耶和華已告訴你們不要去埃及。別忘了我今日給你們的警告, 20你們是在自欺,因為原是你們請我去向我們的上帝耶和華祈求,讓我毫不隱瞞地把祂的話告訴你們,你們也答應遵行。 21今日,我把你們上帝耶和華的話告訴了你們,你們卻不聽從。 22因此,你們要清楚知道,你們如果決意去埃及住,必死於戰爭、饑荒和瘟疫。」