ኤርምያስ 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 4:1-31

1“እስራኤል ሆይ፤ ብትመለስ፣

ወደ እኔ ብትመለስ”

ይላል እግዚአብሔር

“አስጸያፊ ነገሮችህን ከፊቴ ብታስወግድ፣

ባትናወጥ ብትቆምም፣

2በእውነት፣ በቅንነትና በጽድቅ፣

‘ሕያው እግዚአብሔርን!’ ብለህ ብትምል፣

አሕዛብ በእርሱ ይባረካሉ፤

በእርሱም ይከበራሉ።”

3እግዚአብሔር ለይሁዳና ለኢየሩሳሌም ሰዎች እንዲህ ይላል፤

“ዕዳሪውን መሬት ዕረሱ፤

በእሾኽም መካከል አትዝሩ።

4እናንተ የይሁዳ ሰዎች፣ የኢየሩሳሌምም ነዋሪዎች፤

ለእግዚአብሔር ተገረዙ፤

የልባችሁንም ሸለፈት አስወግዱ፤

አለዚያ ስለ ሠራችሁት ክፋት፣

ቍጣዬ እንደ እሳት ይንበለበላል፤

ሊገታውም የሚችል የለም።

ጥፋት ከሰሜን መምጣቱ

5“ ‘በምድሪቱ ሁሉ መለከትን ንፉ’ ብላችሁ፤

በይሁዳ ተናገሩ፣ በኢየሩሳሌም ዐውጁ፤

ጩኹ፤ እንዲህም በሉ፤

‘በአንድነት ተሰብሰቡ፤

ወደ ተመሸጉት ከተሞች እንሽሽ!’

6ወደ ጽዮን ለመግባት ሰንደቅ ዐላማ አንሡ፤

ቶሎ ሸሽታችሁ አምልጡ፤

ከሰሜን መቅሠፍትን፣

ታላቅ ጥፋትን አመጣለሁና።”

7አንበሳ ከደኑ ወጥቷል፤

ሕዝብንም የሚያጠፋ ተሰማርቷል፤

ምድርሽን ባዶ ሊያደርግ፣

ከስፍራው ወጥቷል።

ከተሞችሽ ፈራርሰው ይወድቃሉ፤

ያለ ነዋሪም ይቀራሉ።

8ስለዚህ ማቅ ልበሱ፤

ዕዘኑ፤ ዋይ በሉ፤

የእግዚአብሔር አስፈሪ ቍጣ፣

ከእኛ አልተመለሰምና።

9“በዚያ ቀን” ይላል እግዚአብሔር

“ንጉሡና ሹማምቱ ወኔ ይከዳቸዋል፤

ካህናቱ ድንጋጤ ይውጣቸዋል፤

ነቢያቱም ብርክ ይይዛቸዋል።”

10እኔም፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰይፍ ዐንገታቸው ላይ ተቃጥቶ ሳለ፣ ‘ሰላም ይሆንላችኋል’ ብለህ ይህን ሕዝብና ኢየሩሳሌምን ለምን እጅግ አታለልህ?” አልሁ።

11በዚያን ጊዜ፣ ለእዚህ ሕዝብና ለኢየሩሳሌም እንዲህ ተብሎ ይነገራል፤ “ለማበጠር ወይም ለማጥራት ሳይሆን፣ ከዚያ የበረታ የሚጠብስ ደረቅ ነፋስ በምድረ በዳ ካሉት ባድማ ኰረብቶች ወደ ወገኔ ሴት ልጅ 12በእኔ ትእዛዝ ይነፍሳል፤4፥12 ወይም በእኔ ትእዛዝ የሚመጣው እንግዲህ ፍርዴን በእነርሱ ላይ እናገራለሁ።”

13እነሆ፤ እንደ ደመና ይንሰራፋል፤

ሠረገሎቹ እንደ ዐውሎ ነፋስ ይመጣሉ፤

ፈረሶቹም ከንስር ይፈጥናሉ፤

መጥፋታችን ነውና ወዮልን!

14ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እንድትድኚ ከልብሽ ክፋት ታጠቢ፤

እስከ መቼ ክፉ ሐሳብ በውስጥሽ ይኖራል?

15ድምፅ ከዳን ይሰማልና፤

ከኤፍሬም ተራሮችም ጥፋትን ያውጃል።

16“ይህን ለሕዝቦች አሳውቁ፤

ለኢየሩሳሌምም እንዲህ ብላችሁ በይፋ ንገሩ፤

‘ከብበው የሚያስጨንቁ ከሩቅ አገር ይመጣሉ፤

በይሁዳ ከተሞችም ላይ ይደነፋሉ፤

17ሰብል እንደሚጠብቁ ሰዎች ይከቧታል፤

በእኔ ላይ ዐምፃለችና፤’ ”

ይላል እግዚአብሔር

18“የገዛ መንገድሽና ተግባርሽ፣

ይህን አምጥቶብሻል፤

ይህም ቅጣትሽ ነው፤

ምንኛ ይመርራል!

እንዴትስ ልብ ይሰብራል!”

19ወይ አበሳዬ! ወይ አበሳዬ!

ሥቃይ በሥቃይ ላይ ሆነብኝ፤

አወይ፣ የልቤ ጭንቀት!

ልቤ ክፉኛ ይመታል፤

ዝም ማለት አልችልም፤

የመለከትን ድምፅ፣

የጦርነትንም ውካታ ሰምቻለሁና።

20ጥፋት በጥፋት ላይ ይመጣል፤

ምድሪቱም በሞላ ባድማ ትሆናለች፤

ድንኳኔ በድንገት፣

መጠለያዬም በቅጽበት ጠፋ።

21እስከ መቼ የጦርነት ዐርማ እመለከታለሁ?

እስከ መቼስ የመለከት ድምፅ እሰማለሁ?

22“ሕዝቤ ተላሎች ናቸው፤

እኔን አያውቁኝም።

ማስተዋል የጐደላቸው፣

መረዳትም የማይችሉ ልጆች ናቸው።

ክፋትን ለማድረግ ጥበበኞች፣

መልካም መሥራት ግን የማያውቁ።”

23ምድርን ተመለከትሁ፤

እነሆ ቅርጽ የለሽና ባዶ ነበረች፤

ሰማያትንም አየሁ፣

ብርሃናቸው ጠፍቷል።

24ተራሮችን ተመለከትሁ፣

እነሆ ይንቀጠቀጡ ነበር፤

ኰረብቶችም ሁሉ ተናጡ።

25አየሁ፤ ሰው አልነበረም፤

የሰማይ ወፎች ሁሉ በረው ጠፍተዋል።

26ተመለከትሁ፤ እነሆም፣ ፍሬያማው ምድር በረሓ ሆነ፤

ከተሞቹ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት፣

ከብርቱ ቍጣው የተነሣ ፈራረሱ።

27እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ምድር ሁሉ ባድማ ትሆናለች፤

ነገር ግን ፈጽሜ አላጠፋትም።

28ስለዚህ ምድር ታለቅሳለች፤

ሰማያትም በላይ ይጨልማሉ፤

ተናግሬአለሁ፤ ሐሳቤን አልለውጥም፤

ወስኛለሁ፤ ወደ ኋላም አልልም።”

29ከፈረሰኞችና ከቀስተኞች ጩኸት የተነሣ፣

ከተማ ሁሉ ይሸሻል፤

አንዳንዶች ደን ውስጥ ይገባሉ፤

ሌሎችም ቋጥኝ ላይ ይወጣሉ፤

ከተሞች ሁሉ ባዶ ቀርተዋል፤

የሚኖርባቸውም የለም።

30አንቺ ለጥፋት የተዳረግሽ ሆይ፤ ምን መሆንሽ ነው?

ቀይ ቀሚስ የለበስሽው ለምንድን ነው?

ለምን በወርቅ አጌጥሽ?

ዐይኖችሽንስ ለምን ተኳልሽ?

እንዲያው በከንቱ ተሽሞንሙነሻል፤

የተወዳጀሻቸው ንቀውሻልና፤

ነፍስሽንም ሊያጠፉ ይፈልጋሉ።

31የበኵር ልጇን ለመውለድ እንደምታምጥ፣

በወሊድ እንደምትጨነቅ ሴት ድምፅ ሰማሁ፤

የጽዮን ሴት ልጅ ትንፋሽ ዐጥሯት ስትጮኽ፣

እጇን ዘርግታ፣

“ወዮልኝ! ተዝለፈለፍሁ፣

በነፍሰ ገዳዮች እጅ ወደቅሁ!” ስትል ሰማሁ።

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 4:1-31

1องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า

“อิสราเอลเอ๋ย หากเจ้าจะหันกลับมา

หากเจ้าจะกลับมาหาเรา

หากเจ้ากำจัดเทวรูปอันน่าชิงชังออกไปให้พ้นหน้าเรา

และไม่หลงเตลิดอีกต่อไป

2และหากเจ้าจะปฏิญาณโดยกล่าวอ้างว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด’

ด้วยความจริง ความยุติธรรม และความชอบธรรม

ประชาชาติทั้งหลายก็จะได้รับพรจากเรา

และพวกเขาจะสรรเสริญเทิดทูนเรา”

3องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับชาวยูดาห์และชาวเยรูซาเล็มว่า

“จงไถพรวนดินแข็งแห่งจิตใจของเจ้า

และอย่าหว่านเมล็ดพืชลงกลางดงหนาม

4ชนยูดาห์ ชาวเยรูซาเล็มเอ๋ย

จงทำสุหนัตให้ตัวเองถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า

จงทำสุหนัตที่ใจของพวกเจ้า

มิฉะนั้นโทสะของเราจะระเบิดออกและแผดเผาดั่งไฟ

เผาผลาญโดยไม่มีใครดับได้

เนื่องจากความชั่วร้ายที่พวกเจ้าได้ทำ

ภัยพิบัติจากทิศเหนือ

5“จงป่าวประกาศในยูดาห์และป่าวร้องในเยรูซาเล็มว่า

‘จงเป่าแตรทั่วแผ่นดิน!’

จงป่าวร้องเสียงดังว่า

‘มารวมตัวกัน!

ให้เราหนีไปยังเมืองป้อมปราการต่างๆ โดยเร็ว!’

6จงส่งสัญญาณให้ไปศิโยน!

อย่าชักช้า! จงรีบหนีเอาชีวิตรอด

เพราะเรากำลังนำภัยพิบัติมาจากทางเหนือ

เป็นหายนะร้ายแรง”

7ราชสีห์ตัวหนึ่งได้ออกมาจากถ้ำ

ผู้ที่จะทำลายบรรดาประชาชาติได้ออกมาแล้ว

เขาออกมาจากที่พักของตน

เพื่อทำให้แผ่นดินของเจ้าถูกทิ้งร้าง

เมืองต่างๆ ของเจ้าจะกลายเป็นซากปรักหักพัง

ปราศจากผู้อยู่อาศัย

8ฉะนั้นจงสวมเสื้อผ้ากระสอบ

จงร้องไห้คร่ำครวญ

เพราะพระพิโรธอันรุนแรงขององค์พระผู้เป็นเจ้า

ยังไม่หันเหจากเรา

9องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า “ในวันนั้น

กษัตริย์และบรรดาข้าราชการจะเสียขวัญกำลังใจ

ปุโรหิตจะตกใจกลัว

และผู้เผยพระวจนะจะขนลุก”

10แล้วข้าพเจ้ากราบทูลว่า “ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต พระองค์ทรงหลอกลวงเยรูซาเล็มและชนชาตินี้แน่แล้ว ก็ไหนพระองค์ตรัสว่า ‘เจ้าจะมีสันติสุข’ แต่นี่ดาบจ่อที่คอหอยข้าพระองค์ทั้งหลายแล้ว”

11เมื่อถึงเวลานั้นจะมีผู้บอกชนชาตินี้และชาวเยรูซาเล็มว่า “ลมร้อนจากที่สูงอันเวิ้งว้างในทะเลทรายพัดมายังประชากรของเรา แต่ไม่ใช่เพื่อฝัดร่อนหรือชะล้าง 12เราเป็นผู้ส่งลมกล้านั้นมา4:12 หรือเราเป็นผู้สั่งให้ลมกล้านั้นมา บัดนี้เราประกาศคำพิพากษาลงโทษพวกเขา”

13ดูสิ! บุคคลผู้นั้นบุกมาเหมือนเมฆ

รถม้าศึกของเขามาเหมือนพายุหมุน

ม้าศึกของเขาไวยิ่งกว่านกอินทรี

วิบัติแก่เรา! เราพินาศวอดวายแล้ว!

14เยรูซาเล็มเอ๋ย จงชำระความชั่วร้ายออกจากจิตใจเพื่อจะได้รับความรอด

เจ้าจะบ่มความคิดชั่วไว้นานสักเท่าใด?

15เสียงหนึ่งป่าวร้องออกมาจากดาน

ประกาศภัยพิบัติจากบรรดาเนินเขาของเอฟราอิม

16“จงบอกเรื่องนี้แก่บรรดาประชาชาติ

ประกาศเรื่องนี้แก่เยรูซาเล็มว่า

‘กองทัพที่ล้อมเมืองกำลังมาจากแดนไกล

โห่ร้องออกศึกสู้กับเมืองต่างๆ ของยูดาห์

17พวกเขาโอบล้อมเยรูซาเล็มเหมือนคนเฝ้านา

เพราะเยรูซาเล็มกบฏต่อเรา’ ”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

18“การกระทำและความประพฤติของเจ้าเอง

ได้ชักนำให้เหตุการณ์นี้เกิดแก่เจ้า

นี่คือโทษทัณฑ์ของเจ้า

มันช่างขมขื่นยิ่งนัก!

มันช่างเสียดแทงใจเสียจริง!”

19โอย ทุกข์เหลือเกิน ทรมานเหลือเกิน!

ข้าพเจ้าทุรนทุรายด้วยความเจ็บปวด

โอย หัวใจของข้าพเจ้าร้าวราน!

หัวใจของข้าพเจ้าสะทกสะท้านอยู่ภายใน

ข้าพเจ้าไม่อาจสงบนิ่ง

เพราะข้าพเจ้าได้ยินเสียงแตร

ได้ยินเสียงโห่ร้องคะนองศึก

20หายนะกระหน่ำเข้ามาติดๆ กัน

ทั้งแผ่นดินตกอยู่ในสภาพปรักหักพัง

เต็นท์ทั้งหลายของข้าพเจ้าถูกทำลายไปในชั่วพริบตา

เพียงแวบเดียว ที่พักพิงของข้าพเจ้าก็ย่อยยับไป

21ข้าพเจ้าจะต้องทนดูธงรบ

และฟังเสียงแตรไปนานสักเท่าใดหนอ?

22“ประชากรของเราโง่เขลา

พวกเขาไม่รู้จักเรา

พวกเขาเป็นเด็กเหลวไหล

ไม่มีความเข้าใจ

พวกเขาช่ำชองในการทำชั่ว

ทำดีไม่เป็นเลย”

23ข้าพเจ้ามองดูที่แผ่นดินโลก

มันไม่มีรูปทรงและว่างเปล่า

มองดูที่ฟ้าสวรรค์

แสงสว่างลับไปเสียแล้ว

24ข้าพเจ้ามองดูภูเขาทั้งหลาย

เห็นมันสั่นสะท้าน

เนินเขาทั้งหลายก็โคลงเคลง

25ข้าพเจ้ามองดู ไม่มีผู้คนเลย

นกในท้องฟ้าบินลับหายไปหมด

26ข้าพเจ้ามองดูและเห็นแผ่นดินอันอุดมสมบูรณ์กลายเป็นถิ่นกันดาร

เมืองทั้งหลายอยู่ในสภาพปรักหักพัง

ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าและต่อพระพิโรธอันรุนแรงของพระองค์

27องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า

“ทั้งแผ่นดินจะย่อยยับ

แม้เราจะไม่ทำลายจนหมดสิ้น

28ฉะนั้นโลกจะคร่ำครวญ

และฟ้าสวรรค์เบื้องบนจะหม่นหมอง

เพราะเราได้ลั่นวาจาไว้ และจะไม่มีการผ่อนผัน

เราได้ตัดสินใจไว้แล้ว และจะไม่เปลี่ยนแปลง”

29เมื่อได้ยินเสียงพลม้าและพลธนู

ชาวเมืองทุกแห่งหนีกระเจิดกระเจิง

บางคนเข้าไปในพุ่มไม้

บางคนปีนป่ายขึ้นไปตามหินผา

เมืองทุกเมืองถูกทิ้งร้าง

ไม่มีใครอยู่อาศัย

30เจ้าผู้ถูกทำลาย เจ้ากำลังทำอะไรอยู่นั่น?

ทำไมจึงสวมเสื้อผ้าสีแดงเข้ม

และสวมเครื่องเพชรเครื่องทอง?

เจ้าแต่งแต้มทาตาไปทำไม?

ถึงแต่งตัวสวยก็เปล่าประโยชน์

คนรักของเจ้าเหยียดหยามเจ้า

พวกเขาหมายจะเอาชีวิตเจ้า

31ข้าพเจ้าได้ยินเสียงร้องเหมือนเสียงผู้หญิงกำลังคลอดลูก

เหมือนเสียงครวญครางของผู้หญิงที่คลอดลูกท้องแรก

เป็นเสียงร้องของธิดาแห่งศิโยน4:31 คือ ชาวเยรูซาเล็มหอบหายใจเป็นห้วงๆ

เธอเหยียดแขนออกและพูดว่า

“อนิจจา ฉันจะเป็นลมแล้ว

ชีวิตฉันถูกมอบไว้ในมือของเหล่าฆาตกร”