ኤርምያስ 36 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 36:1-32

ኢዮአቄም የኤርምያስን ብራና አቃጠለ

1የይሁዳ ንጉሥ የኢዮስያስ ልጅ የነበረው ኢዮአቄም በነገሠ በአራተኛው ዓመት እንዲህ የሚል ቃል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ ኤርምያስ መጣ፤ 2“የብራና ጥቅልል ውሰድ፤ ለአንተም መናገር ከጀመርሁበት ከኢዮስያስ ዘመነ መንግሥት አንሥቶ እስካሁን ድረስ ስለ እስራኤል፣ ስለ ይሁዳና ስለ ሌሎች ሕዝቦች ሁሉ የነገርሁህን ቃል ሁሉ ጻፍበት፤ 3ምናልባትም የይሁዳ ሕዝብ ላመጣባቸው ያሰብሁትን ጥፋት ሁሉ ሲሰሙ፣ እያንዳንዳቸው ከክፉ መንገዳቸው ይመለሱ ይሆናል፤ እኔም ክፋታቸውንና ኀጢአታቸውን ይቅር እላለሁ።”

4ኤርምያስም የኔርያን ልጅ ባሮክን ጠራው፤ ባሮክም እግዚአብሔር የተናገረውን ቃል ሁሉ ከኤርምያስ አፍ ተቀብሎ በብራናው ላይ ጻፈ። 5ኤርምያስም ባሮክን እንዲህ አለው፤ “እኔ ተከልክያለሁና ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መግባት አልችልም፤ 6ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሄደህ፣ በቃል እየነገርሁህ በብራናው ላይ የጻፍኸውን የእግዚአብሔርን ቃል በጾም ቀን ለተሰበሰበው ሕዝብ አንብብ፤ ከየከተሞቻቸው ለመጡት ለይሁዳ ሕዝብ ሁሉ አንብብ። 7እግዚአብሔር በዚህ ሕዝብ ላይ የተናገረው ቍጣና መቅሠፍት ታላቅ ስለሆነ፣ ምናልባት ልመናቸውን በእግዚአብሔር ፊት በማቅረብ እያንዳንዳቸው ከክፉ መንገዳቸው ይመለሱ ይሆናል።”

8የኔርያ ልጅ ባሮክ ነቢዩ ኤርምያስ የነገረውን ሁሉ አደረገ፤ በእግዚአብሔርም ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔርን ቃል ከብራናው አነበበ። 9የይሁዳ ንጉሥ የኢዮስያስ ልጅ የሆነው ኢዮአቄም በነገሠ በአምስተኛው ዓመት በዘጠነኛው ወር በኢየሩሳሌም የሚኖረው ሕዝብ ሁሉና ከይሁዳ ከተሞች የመጡት ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት ጾም ዐወጁ። 10ባሮክም በብራና ላይ የተጻፈውን የኤርምያስን ቃል በእግዚአብሔር ቤት በላይኛው አደባባይ፤ “አዲሱ በር” በሚባለው በቤተ መቅደሱ መግቢያ ላይ በሚገኘው በጸሓፊው በሳፋን ልጅ በገማርያ ክፍል ውስጥ ሆኖ ለሕዝቡ ሁሉ አነበበው።

11የሳፋን ልጅ የገማርያ ልጅ ሚክያስ ከብራናው የተነበበውን የእግዚአብሔርን ቃል ሁሉ በሰማ ጊዜ፣ 12በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ወዳለው ወደ ጸሓፊው ክፍል ወረደ፤ በዚያም መኳንንቱ ሁሉ፦ ጸሓፊው ኤሊሳማ፣ የሸማያ ልጅ ድላያ፣ የዓክቦር ልጅ ኤልናታን፣ የሳፋን ልጅ ገማርያ፣ የሐናንያ ልጅ ሴዴቅያስ እንዲሁም ሌሎች መኳንንት ሁሉ ተቀምጠው ነበር። 13ባሮክ ለሕዝቡ ከብራናው ሲያነብ ሚክያስ የሰማውን ሁሉ ከነገራቸው በኋላ፣ 14መኳንንቱ ሁሉ የኩሲን ልጅ የሴሌምያን ልጅ የናታንያን ልጅ ይሁዲን፣ “ለሕዝቡ ያነበብኸውን ብራና ይዘህ እንድትመጣ” ብለው ወደ ባሮክ ላኩ። የኔርያም ልጅ ባሮክ ብራናውን ይዞ ወደ እነርሱ መጣ፤ 15እነርሱም፣ “እስቲ ተቀምጠህ አንብብልን” አሉት። ባሮክም አነበበላቸው፤ 16እነርሱም ቃሉን ሁሉ በሰሙ ጊዜ እርስ በርሳቸው በፍርሀት በመተያየት ባሮክን፣ “ይህን ሁሉ ቃል ለንጉሡ መንገር ይገባናል።” አሉት፤ 17ደግሞም፣ “ይህን ሁሉ እንዴት ልትጽፍ እንደ ቻልህ ንገረን፤ ኤርምያስ በቃል እየነገረህ ነውን?” ብለው ባሮክን ጠየቁት።

18ባሮክም፣ “አዎን ይህን ሁሉ በቃሉ ነገረኝ፤ እኔም በብራናው ላይ በቀለም ጻፍሁ” ብሎ መለሰላቸው።

19መኳንንቱም ባሮክን፣ “እንግዲያውስ አንተና ኤርምያስ ሄዳችሁ ተሸሸጉ፤ የት እንዳላችሁም ማንም አይወቅ” አሉት።

20የብራናውን ጥቅልል በጸሓፊው በኤሊሳማ ክፍል ካስቀመጡት በኋላ፣ ንጉሡ ወዳለበት አደባባይ ሄደው የሆነውን ሁሉ ነገሩት። 21ንጉሡም ብራናውን ያመጣ ዘንድ ይሁዲን ላከው፤ ይሁዲም ከጸሓፊው ከኤሊሳማ ክፍል ብራናውን አምጥቶ፣ ለንጉሡና በንጉሡ አጠገብ ቆመው ለነበሩት መኳንንት ሁሉ አነበበላቸው። 22ዘጠነኛው ወር እንደ መሆኑ፣ ንጉሡ የክረምትን ወራት በሚያሳልፍበት ቤት ተቀምጦ ነበር፤ በምድጃ የሚነድድ እሳትም ፊት ለፊቱ ነበር። 23ይሁዲ ከብራናው ሦስት ወይም አራት ዐምድ ባነበበ ቍጥር ንጉሡ ብራናው ሁሉ እስከሚያልቅ ድረስ በጸሓፊ ቢላዋ እየቈረጠ እንዲቃጠል ወደ እሳቱ ምድጃ ይጥል ነበር። 24ንጉሡም ሆነ ይህን ሁሉ ቃል የሰሙት መኳንንት ሁሉ አንዳች አልፈሩም፤ ልብሳቸውንም አልቀደዱም። 25ኤልናታን፣ ድላያ፣ ገማርያም ንጉሡ ብራናውን እንዳያቃጥል ቢለምኑትም እንኳ አልሰማቸውም፣ 26ይልቁንም ጸሓፊውን ባሮክንና ነቢዩን ኤርምያስን ይዘው ያስሩ ዘንድ የንጉሡን ልጅ ይረምሕኤልን፣ የዓዝርኤልን ልጅ ሠራያንና የአብድኤልን ልጅ ሰሌምያን አዘዘ፤ እግዚአብሔር ግን ሰውሯቸው ነበር።

27ንጉሡ፣ ባሮክ ከኤርምያስ አፍ ተቀብሎ የጻፈው ቃል ያለበትን ብራና ካቃጠለ በኋላ፤ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 28“ሌላ ብራና ወስደህ፣ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአቄም ባቃጠለው በመጀመሪያው ብራና ላይ የነበረውን ቃል ሁሉ ጻፍበት፤ 29ለይሁዳ ንጉሥ ለኢዮአቄም እንዲህ ብለህ ንገረው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የባቢሎን ንጉሥ በርግጥ ይመጣል፤ ይህችን ምድር፣ በእርሷም ላይ የሚኖሩትን ሰዎችንና እንስሳትን ያጠፋል በማለት የጻፍህበት ለምንድን ነው?” ብለህ ብራናውን አቃጥለሃል። 30ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮአቄም እንዲህ ይላል፤ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጥ ከዘሩ አይገኝም፤ ሬሳውም ወደ ውጭ ተጥሎ ለቀን ሐሩርና ለሌሊት ቍር ይጋለጣል። 31እርሱንና ልጆቹን መኳንንቱንም ስለ ክፋታቸው እቀጣለሁ፤ አልሰሙኝምና አመጣባቸዋለሁ ያልሁትን ጥፋት ሁሉ በእነርሱና በኢየሩሳሌም በሚኖሩት፣ በይሁዳም ሕዝብ ላይ አመጣለሁ።’ ”

32ኤርምያስም ሌላ ብራና ወስዶ ለኔርያ ልጅ ለጸሓፊው ለባሮክ ሰጠው፤ ባሮክም የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአቄም በእሳት ባቃጠለው ብራና ላይ የነበረውን ቃል ሁሉ ከኤርምያስ አፍ ተቀብሎ ጻፈበት፤ ብዙ ተመሳሳይ ቃልም ተጨመረበት።

Persian Contemporary Bible

ارميا 36:1-32

طومار ارميا

1در سال چهارم سلطنت يهوياقيم (پسر يوشيا)، پادشاه يهودا، خداوند اين پيغام را به من داد:

2«طوماری تهيه كن و تمام سخنان مرا كه عليه اسرائيل و يهودا و اقوام ديگر گفته‌ام، از نخستين پيغامم در زمان يوشيا تا به امروز، همه را در آن بنويس. 3شايد وقتی مردم يهودا تمام بلاهايی را كه قصد دارم بر سرشان بياورم به صورت نوشته ببينند، توبه كنند و از راههای بد خويش بازگشت نمايند. آنگاه من نيز ايشان را خواهم آمرزيد.»

4باروک (پسر نيريا) را نزد خود خواندم و هر آنچه خداوند فرموده بود، برای او بازگو كردم و او همه را نوشت. 5سپس به او گفتم: «من در اينجا زندانی‌ام و نمی‌توانم به خانه خداوند بروم. 6بنابراين تو در روزی كه مردم روزه می‌گيرند، به خانه خداوند برو و اين طومار را با صدای بلند بخوان، چون در آن روز، مردم از سراسر يهودا در آنجا گرد خواهند آمد. 7شايد از راههای بد خود بازگردند و پيش از آنكه دير شود، از خداوند طلب بخشش كنند، زيرا بلايی كه خداوند عليه اين قوم اعلام فرموده، بسيار سخت است.»

8باروک به گفتهٔ من عمل كرد و كلام خدا را تماماً در خانهٔ خداوند برای مردم خواند. 9اين امر، در ماه نهم از سال پنجم سلطنت يهوياقيم (پسر يوشيا) روی داد. در آن روز مردم از سراسر يهودا به خانهٔ خداوند آمده بودند تا در مراسم روزه شركت نمايند. 10وقتی همه آماده شنيدن شدند، باروک به اتاق جمريا (پسر شافان) کاتب دربار رفت و از آنجا طومار را برای مردم خواند. (اين اتاق در حياط بالايی خانهٔ خداوند و نزديک «دروازهٔ جديد» واقع شده بود.)

11هنگامی كه ميكايا (پسر جمريا، نوهٔ شافان) پيغام خداوند را از آن طومار شنيد، 12بی‌درنگ به اتاق منشيان دربار رفت كه در آنجا بزرگان قوم دور هم جمع بودند، از جمله اليشاماع کاتب، دلايا (پسر شمعيا)، الناتان (پسر عكبور)، جمريا (پسر شافان)، صدقيا (پسر حننيا). 13ميكايا پيغامی را كه باروک برای قوم خوانده بود، برای ايشان بازگو كرد؛ 14‏-15آنگاه بزرگان قوم، شخصی به نام يهودی (پسر نتنيا، نوهٔ شلميا، نبيرهٔ كوشی) را نزد باروک فرستادند تا از او بخواهد كه بيايد و آن طومار را برای ايشان نيز بخواند. باروک هم مطابق خواهش ايشان عمل كرد.

16وقتی طومار خوانده شد، ايشان با ترس به يكديگر نگاه كردند و به باروک گفتند: «ما بايد اين موضوع را به عرض پادشاه برسانيم. 17ولی اول بگو كه اين مطالب را چگونه نوشتی؟ آيا آنها را ارميا گفته است؟» 18باروک جواب داد: «ارميا آنها را كلمه به كلمه گفت و من با مركب روی اين طومار نوشتم.» 19ايشان به باروک گفتند: «تو و ارميا خود را پنهان كنيد و به هيچكس نگوييد كجا هستيد!» 20بعد طومار را در اتاق اليشاماع، کاتب دربار، گذاشتند و به حضور پادشاه رفتند تا قضيه را به اطلاع او برسانند.

21پادشاه «يهودی» را فرستاد تا طومار را بياورد. او نيز آن را از اتاق اليشاماع کاتب آورد و برای پادشاه و تمام مقامات دربار كه حضور داشتند، خواند. 22زمستان بود و پادشاه در كاخ زمستانی مقابل آتش نشسته بود. 23وقتی «يهودی» چند ستون از آن را خواند، پادشاه آن قسمت را با چاقو بريد و در آتش انداخت، و به تدریج كه طومار خوانده می‌شد همين كار را ادامه داد تا تمام طومار را سوزاند. 24او و اطرافيانش از شنيدن كلام خدا نترسيدند و غمگين نشدند، 25و با اينكه الناتان، دلايا و جمريا به پادشاه التماس كردند كه طومار را نسوزاند، ولی او توجهی ننمود.

26آنگاه پادشاه به شاهزاده يرحمی‌ئيل و سرايا (پسر عزرئيل) و شلميا (پسر عبدئيل) دستور داد كه مرا و باروک را بازداشت كنند، ولی خداوند ما را پنهان كرده بود.

27پس از آنكه پادشاه طومار را سوزاند، خداوند به من فرمود كه 28طوماری ديگر تهيه كنم و همهٔ سخنانی را كه در طومار قبلی نوشته بودم، بر روی آن بنويسم، 29و به پادشاه بگويم كه خداوند چنين می‌فرمايد: «تو آن طومار را سوزاندی، زيرا در آن نوشته شده بود كه پادشاه بابل اين مملكت را ويران خواهد كرد و هر چه را كه در آن است از انسان و حيوان از بين خواهد برد. 30بنابراين ای يهوياقيم، پادشاه يهودا، از نسل تو كسی بر تخت پادشاهی داوود تكيه نخواهد زد. جنازهٔ تو بيرون انداخته خواهد شد تا روز، زير آفتاب سوزان و شب، در سرما باقی بماند. 31تو را و خاندانت را و بزرگان مملكتت را به خاطر گناهانتان مجازات خواهم نمود، و تمام بلاهايی را كه گفته‌ام، بر سر تو و بر سر تمام مردم يهودا و اورشليم خواهم آورد، چون به هشدارهای من توجهی نمی‌كنيد.»

32پس من طوماری ديگر گرفتم و آنچه كه قبلاً گفته بودم، بار ديگر به باروک بازگو كردم تا بنويسد؛ ولی اين بار خداوند مطالب بسياری نيز به آن افزود!