ኤርምያስ 35 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 35:1-19

የሬካባውያን ታማኝነት

1በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ፣ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንዲህ የሚል ቃል ወደ ኤርምያስ መጣ፤ 2“ወደ ሬካባውያን ሄደህ ወደ እግዚአብሔር ቤት አምጣቸው፤ ወደ አንዱም ክፍል አስገብተህ የሚጠጡትን ወይን ጠጅ ስጣቸው።”

3ስለዚህ የካባስን ልጅ የኤርምያስን ልጅ ያእዛንያን፣ ወንድሞቹንና ወንዶች ልጆቹን ሁሉ፣ የሬካባውያንን ወገን በአጠቃላይ ሄጄ ጠራኋቸው፤ 4ወደ እግዚአብሔር ቤት አመጣኋቸው፤ ወደ ሐናን ልጆች ክፍልም አስገባኋቸው፤ የሐናን አባት ጌዴልያም የእግዚአብሔር ሰው ነበረ። ክፍሉም በመኳንንቱ ክፍል አጠገብ፣ ከመዕሤያ ክፍል በላይ ነበር፤ መዕሤያም የበር ጠባቂው የሰሎም ልጅ ነበረ፤ 5በሬካባውያንም ሰዎች ፊት በወይን ጠጅ የተሞሉ ማድጋዎችን አቀረብሁ፤ ዋንጫዎችንም ሰጥቻቸው፣ “በሉ፤ የወይን ጠጅ ጠጡ” አልኋቸው።

6እነርሱ ግን እንዲህ አሉ፤ “የወይን ጠጅ አንጠጣም፤ አባታችን የሬካብ ልጅ ኢዮናዳብ እንዲህ ብሎ አዝዞናል፤ ‘እናንተና ዘራችሁ ከቶ የወይን ጠጅ አትጠጡ፤ 7ቤት አትሥሩ፤ ዘር አትዝሩ፤ ወይን አትትከሉ፤ ሁልጊዜ በድንኳን ኑሩ እንጂ ከእነዚህ ነገሮች አንዱም አይኑራችሁ፤ ይህም ሲሆን እንደ መጻተኛ በሆናችሁበት ምድር ረዥም ዘመን ትኖራላችሁ።’ 8እኛም አባታችን የሬካብ ልጅ ኢዮናዳብ ያዘዘንን ሁሉ ፈጽመናል፤ እኛና ሚስቶቻችን፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችንም የወይን ጠጅ ጠጥተን አናውቅም፤ 9የምንቀመጥበትም ቤት አልሠራንም፤ የወይን ቦታ፣ የዕርሻ ስፍራ ወይም የእህል ዘር የለንም። 10በድንኳን ኖረናል፤ አባታችን ኢዮናዳብ ያዘዘንንም ሁሉ ጠብቀናል። 11ነገር ግን የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ይህችን ምድር በወረረ ጊዜ፣ ‘ኑ፤ ከባቢሎን35፥11 ወይም ከለዳውያን ሰራዊትና ከሶርያ ሰራዊት ሸሽተን ወደ ኢየሩሳሌም እንሂድ’ ተባባልን፤ ስለዚህም በኢየሩሳሌም ተቀመጥን።” 12የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 13“የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ሂድ፤ ለይሁዳ ሰዎችና ለኢየሩሳሌም ሕዝብ እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘ቃሌን ትጠብቁ ዘንድ ከዚህ አትማሩምን?’ ይላል እግዚአብሔር14‘የሬካብ ልጅ ኢዮናዳብ ልጆቹ የወይን ጠጅ እንዳይጠጡ አዘዛቸው፤ ይህም ትእዛዝ ተጠብቋል፤ የአባታቸውን ትእዛዝ ስለ ጠበቁ እስከ ዛሬ ድረስ የወይን ጠጅ አይጠጡም፤ እናንተ ግን እኔ ደጋግሜ ብናገራችሁም፤ አልታዘዛችሁኝም። 15አገልጋዮቼን ነቢያትን ሁሉ ደጋግሜ ወደ እናንተ ላክሁ፤ እነርሱም፣ “እያንዳንዳችሁ ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ፤ ምግባራችሁን አስተካክሉ፤ ለእናንተና ለአባቶቻችሁ በሰጠኋቸው ምድር ትኖሩ ዘንድ ሌሎቹን አማልክት ለማገልገል አትከተሉ” አልኋችሁ። እናንተ ግን ጆሯችሁን ወደ እኔ አላዘነበላችሁም፤ አልሰማችሁኝምም። 16የሬካብ ልጅ የኢዮናዳብ ዘሮች አባታቸው የሰጣቸውን ትእዛዝ ጠብቀዋል፤ ይህ ሕዝብ ግን አልታዘዘኝም።’

17“ስለዚህ የእስራኤል አምላክ፤ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እነሆ፤ በይሁዳና በኢየሩሳሌም በሚኖሩት ሁሉ ላይ አደርሳለሁ ያልሁትን ጥፋት ሁሉ አመጣባቸዋለሁ፤ በተናገርኋቸው ጊዜ፣ አልሰሙኝምና በጠራኋቸውም ጊዜ አልመለሱልኝም።’ ”

18ኤርምያስም ሬካባውያንን እንዲህ አላቸው፤ “የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የአባታችሁን የኢዮናዳብን ትእዛዝ ስለ ጠበቃችሁ፤ መመሪያውን ስለ ተከተላችሁ፤ ያዘዛችሁንም ሁሉ ስለ ፈጸማችሁ’ 19የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ከሬካብ ልጅ ከኢዮናዳብ ወገን የሚያገለግለኝ ሰው ለዘላለም አይታጣም።’ ”

Swedish Contemporary Bible

Jeremia 35:1-19

Rekaviternas föredömliga lydnad

1Detta är det ord som kom till Jeremia från Herren, när Jojakim, Josias son, var kung över Juda: 2”Gå till rekaviterna och tala med dem, ta med dem till Herrens hus, till ett av de inre rummen och bjud dem på vin att dricka.” 3Då tog jag med mig Jaasanja, Jeremias son och Havassinjas sonson, och hans bröder och söner och hela rekaviternas släkt. 4Jag förde dem till Herrens hus, in i det rum som tillhörde sönerna till gudsmannen Hanan, Jigdaljas son, och som låg alldeles intill furstarnas, ovanför det som tillhörde dörrvaktaren Maaseja, Shallums son.

5Jag satte fram tillbringare fyllda med vin och vinbägare och bjöd dem att dricka, 6men de svarade: ”Vi dricker inte vin. Vår förfader Jonadav, Rekavs son, befallde oss: ’Ingen av er ska någonsin dricka vin, varken ni eller era barn. 7Ni ska varken bygga hus, så säd eller plantera vingårdar och inte heller äga sådana. Ni ska alltid bo i tält, hela ert liv. Då får ni leva länge på den mark där ni lever som främlingar.’ 8Vi har i allting lytt vad vår far Jonadav, Rekavs son, befallde oss. Varken vi, våra hustrur eller våra söner och döttrar har någonsin druckit vin. 9Vi har inte byggt hus att bo i, inte ägt vingårdar eller åkrar eller säd. 10Vi har bott i tält och lydigt följt allt som vår far Jonadav befallt oss. 11Men när Nebukadnessar, kungen av Babylonien, invaderade landet, sa vi: ’Kom, låt oss flytta till Jerusalem, undan kaldéernas och araméernas arméer.’ Så bosatte vi oss i Jerusalem.”

12Herrens ord kom till Jeremia: 13”Så säger härskarornas Herre, Israels Gud: Gå och säg till männen i Juda och Jerusalems invånare: ’Ska ni inte ta varning och lyda vad jag sagt? säger Herren. 14Den befallning som Jonadav, Rekavs son, gav sina efterkommande att inte dricka vin har de hållit. Än idag dricker de inte vin, för de lyder sin förfaders befallning. Men jag har talat till er gång på gång, och ni har inte lyssnat till mig. 15Gång på gång har jag sänt till er alla mina tjänare profeterna för att säga: ”Vänd om var och en från sin onda väg och gör bättring! Följ inte andra gudar för att tjäna dem. Då ska ni få bo på den mark som jag gav er och era förfäder.” Men ni ville varken lyssna till mig eller lyda mig. 16Jonadavs, Rekavs sons, efterkommande har följt sin fars befallning, men detta folk har inte lyssnat på mig.’

17Därför säger härskarornas Herre, Israels Gud så: ’Se, jag ska låta allt det onda som jag har talat om komma över Juda och alla som bor i Jerusalem. För jag talade till dem, men de lyssnade inte. Jag kallade på dem, men de svarade inte.’ ”

18Till rekaviterna sa Jeremia: ”Så säger härskarornas Herre, Israels Gud: ’Eftersom ni har lytt er förfader Jonadavs befallning, följt allt vad han befallt och ålagt er, 19säger härskarornas Herre, Israels Gud, så: Jonadav, Rekavs son, ska alltid ha en ättling som gör tjänst inför mig.’ ”