ኤርምያስ 31 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 31:1-40

1“በዚያ ዘመን” ይላል እግዚአብሔር፤ “ለእስራኤል ነገድ ሁሉ አምላካቸው እሆናለሁ፤ እነርሱም ሕዝቤ ይሆናሉ።”

2እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ከሰይፍ የተረፈው ሕዝብ፣

በምድረ በዳ ሞገስን ያገኛል፤

እኔም ለእስራኤል ዕረፍት ለመስጠት እመጣለሁ።”

3እግዚአብሔር ከሩቅ31፥3 ወይም እግዚአብሔር ከጥንት ወይም ከቀድሞ ተገለጠልን ተገለጠልን፤ እንዲህም አለን፤

“በዘላለማዊ ፍቅር ወድጄሻለሁ፤

ስለዚህም በርኅራኄ ሳብሁሽ።

4የእስራኤል ድንግል ሆይ፤ እንደ ገና ዐንጽሻለሁ፤

አንቺም ትታነጺአለሽ፤

ከበሮችሽንም እንደ ገና አንሥተሽ፣

ከሚፈነጥዙት ጋር ትፈነድቂአለሽ።

5እንደ ገናም በሰማርያ ኰረብቶች ላይ፣

ወይን ትተክያለሽ፤

አትክልተኞች ይተክሏቸዋል፤

በፍሬውም ደስ ይላቸዋል።

6ጠባቂዎች፣ በኤፍሬም ኰረብቶች ላይ፣

‘ኑ፤ ወደ ጽዮን፣

ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር እንውጣ!’

ብለው የሚጮኹበት ቀን ይመጣል።”

7እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ያዕቆብ በደስታ ዘምሩ፤

ስለ ሕዝቦች አለቃ እልል በሉ፤

ምስጋናችሁን አሰሙ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ የእስራኤልን ቅሬታ፣

ሕዝብህን አድን’ በሉ።

8እነሆ፤ ከሰሜን ምድር አመጣቸዋለሁ፤

ከምድርም ዳርቻ እሰበስባቸዋለሁ፤

በመካከላቸውም ዕውሮችና ዐንካሶች፣

ነፍሰ ጡርና በምጥ ላይ ያሉ ሴቶች ይገኛሉ፤

ታላቅም ሕዝብ ሆነው ይመለሳሉ።

9እያለቀሱ ይመጣሉ፤

እያጽናናሁ አመጣቸዋለሁ፤

እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፣

ኤፍሬም በኵር ልጄ ነውና፣

በውሃ ምንጭ ዳር፣

በማይሰናከሉበት ቀና መንገድ እመራቸዋለሁ።

10“ሕዝቦች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤

ሩቅ ባሉ የባሕር ጠረፎችም፣

‘እስራኤልን የበተነ እርሱ ይሰበስበዋል፤

መንጋውንም እንደ እረኛ ይጠብቃል’ ብላችሁ ዐውጁ።

11እግዚአብሔር ያዕቆብን ይዋጀዋልና፤

ከእርሱም ከሚበረቱት እጅ ይታደገዋልና።

12መጥተውም በጽዮን ተራራ ላይ በደስታ ይዘምራሉ፤

በእግዚአብሔርም ልግስና፣

በእህሉ፣ በወይን ጭማቂውና በዘይቱ፣

በፍየልና በበግ ጠቦት፣ በወይፈንና በጊደር ደስ ይሰኛሉ፤

ውሃ እንደማይቋረጥባት የአትክልት ስፍራ ይሆናሉ፤

ከእንግዲህም አያዝኑም።

13ኰረዶች ይዘፍናሉ፤ ደስም ይላቸዋል፤

ጐረምሶችና ሽማግሌዎችም ይፈነጥዛሉ፤

ልቅሷቸውን ወደ ደስታ እለውጣለሁ፤

ከሐዘናቸውም አጽናናቸዋለሁ፤ ደስታንም እሰጣቸዋለሁ።

14ካህናቱን አትረፍርፌ እባርካለሁ፤

ሕዝቤም በልግስናዬ ይጠግባል፤”

ይላል እግዚአብሔር

15እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ዋይታና መራራ ልቅሶ

ከራማ ተሰማ፤

ልጆቿ የሉምና፣

ራሔል አለቀሰች፤

መጽናናትም እንቢ አለች።”

16እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ድምፅሽን ከልቅሶ፣

ዐይኖችሽንም ከእንባ ከልክይ፤

ድካምሽ ያለ ዋጋ አይቀርምና፤”

ይላል እግዚአብሔር

“ከጠላት ምድር ይመለሳሉ፤

17ስለዚህ ወደ ፊት ተስፋ አለሽ”

ይላል እግዚአብሔር

“ልጆችሽ ወደ ገዛ ምድራቸው ይመለሳሉ።

18“የኤፍሬምን የሲቃ እንጕርጕሮ በርግጥ ሰምቻለሁ፤

‘እንዳልተገራ ወይፈን ቀጣኸኝ፤

እኔም ተቀጣሁ።

አንተ እግዚአብሔር አምላኬ ነህና፣

መልሰኝ፤ እኔም እመለሳለሁ።

19ከአንተ ከራቅሁ በኋላ፣

ተመልሼ ተጸጸትሁ፤

ባስተዋልሁም ጊዜ፣

ጭኔን መታሁ፤

የወጣትነት ውርደቴን ተሸክሜአለሁና

ዐፈርሁ፤ ቀለልሁም።’

20ኤፍሬም የምወድደው፣

ደስም የምሰኝበት ልጄ አይደለምን?

ብዙ ጊዜ ተቃውሜው ብናገርም፣

መልሼ ስለ እርሱ ዐስባለሁ፤

አንጀቴ ይላወሳል፤

በታላቅ ርኅራኄም እራራለታለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

21“የጐዳና ምልክት አቁሚ፤

መንገድ አመልካች ትከዪ፤

የምትሄጂበትን መንገድ፣

አውራ ጐዳናውን አስተውዪ፤

ድንግሊቱ እስራኤል ሆይ፤ ተመለሺ፤

ወደ ከተሞችሽም ግቢ።

22አንቺ ከዳተኛ ልጅ ሆይ፤

እስከ መቼ ትቅበዘበዣለሽ?

እግዚአብሔር በምድር ላይ አዲስ ነገር ይፈጥራል፤

ሴት በወንድ ላይ ከበባ ታደርጋለች።31፥22 ወይም መፈለግ ትጀምራለች ወይም መጠበቅ ትጀምራለች

23የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ምርኳቸውን በመለስሁላቸው ጊዜ፣31፥23 ወይም ዕድል ፈንታቸውን በመለስሁላቸው እነርሱ በይሁዳ ምድርና በከተሞቿ፣ ‘አንተ የጽድቅ ማደሪያ ቅዱስ ተራራ ሆይ፤ እግዚአብሔር ይባርክህ!’ የሚል አነጋገር እንደ ገና ይጠቀማሉ። 24ገበሬዎችና ዘላን ከብት አርቢዎች በይሁዳና በከተሞቿ በአንድነት ይኖራሉ። 25የዛለችውን ነፍስ ዐድሳለሁ፤ የደከመችውንም አበረታለሁ።”

26በዚህ ጊዜ ከእንቅልፌ ነቅቼ ዙሪያዬን ተመለከትሁ፤ እንቅልፌም ጣፋጭ ሆኖልኝ ነበር።

27“እነሆ፤ የእስራኤልን ቤትና የይሁዳን ቤት” ይላል እግዚአብሔር፤ “በሰውና በእንስሳት ዘር የምሞላበት ጊዜ ይመጣል፤ 28ልነቅላቸውና ላፈርሳቸው፣ ልገለብጣቸውና ላጠፋቸው፣ መከራም ላመጣባቸው እንደ ተጋሁ ሁሉ፣ ላንጻቸውና ልተክላቸው ደግሞ እተጋለሁ” ይላል እግዚአብሔር29“በዚያ ዘመን ሰዎች ዳግመኛ፣

“ ‘አባቶች በበሉት ጐምዛዛ የወይን ፍሬ፣

የልጆች ጥርስ ጠረሰ’

የሚለውን ምሳሌ አይናገሩም። 30ነገር ግን፣ እያንዳንዱ በገዛ ኀጢአቱ ይሞታል፤ ጐምዛዛ የወይን ፍሬ የሚበላ ሁሉ የራሱን ጥርስ ይጠርሳል።

31“ከእስራኤል ቤትና፣

ከይሁዳ ቤት ጋር” ይላል እግዚአብሔር

“አዲስ ቃል ኪዳን የምገባበት፣

ጊዜ ይመጣል።

32ከግብፅ አወጣቸው ዘንድ፣

እጃቸውን ይዤ በመራኋቸው ጊዜ፣

ከአባቶቻቸው ጋር እንደገባሁት ኪዳን

አይደለም፤31፥32 የዕብራይስጡ፣ የሰብዓ ሊቃናትና የሱርሰት ትርጕሞች እኔም ዘወር አልሁባቸው ይላሉ።

የእነርሱ ባል31፥32 31፥32 ወይም የእነርሱ ጌታ ሆኜ ሳለሁ፣

ቃል ኪዳኔን አፍርሰዋልና።”

ይላል እግዚአብሔር

33“ነገር ግን ከዚያ ጊዜ በኋላ፣

ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው” ይላል እግዚአብሔር

“ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ፤

በልባቸውም እጽፈዋለሁ።

እኔ አምላክ እሆናቸዋለሁ፤

እነርሱም ሕዝቤ ይሆናሉ።

34ከእንግዲህ ማንም ሰው ባልንጀራውን፣

ወይም ወንድሙን፣ ‘እግዚአብሔርን ዕወቅ’ ብሎ አያስተምርም፤

ከትንሹ ጀምሮ እስከ ትልቁ፣

ሁሉም እኔን ያውቁኛልና፤”

ይላል እግዚአብሔር

“በደላቸውን ይቅር እላለሁ፤

ኀጢአታቸውንም መልሼ አላስብም።”

35በቀን እንድታበራ፣

ፀሓይን የመደበ፣

በሌሊት እንዲያበሩ፣

ጨረቃንና ከዋክብትን ያዘዛቸው፣

የሞገዱ ድምፅ እንዲተምም፣

ባሕሩን የሚያናውጥ፣

ስሙ የሰራዊት ጌታ የሆነ፣

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

36“ይህ ሥርዐት በፊቴ ከተሻረ፣”

ይላል እግዚአብሔር

“በዚያ ጊዜ የእስራኤልም ዘር በፊቴ፣

መንግሥት መሆኑ ለዘላለም ይቀራል።”

37እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በላይ ያሉትን ሰማያትን መለካት፣

በታችም ያሉትን የምድር መሠረቶች መመርመር ከተቻለ፣

በዚያ ጊዜ የእስራኤልን ዘር ሁሉ፣

ስላደረጉት ነገር ሁሉ እጥላቸዋለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

38“እነሆ ከሐናንኤል ግንብ ጀምሮ እስከ ማእዘኑ በር ድረስ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ይህች ከተማ ለእግዚአብሔር የምትሠራበት ጊዜ ይመጣል፤ 39መለኪያ ገመዱም ከዚያ ጀምሮ በቀጥታ ወደ ጋሬብ ኰረብታ፣ ዐልፎም ወደ ጎዓ ይዘረጋል። 40ሬሳና ዐመድ የሚጣልበት ሸለቆ በሙሉ፣ በምሥራቅ በኩል የቄድሮንን ሸለቆ ይዞ እስከ ፈረስ በር የሚደርሰው ደልዳላ ቦታ ሁሉ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ይሆናል፤ ከእንግዲህም ከተማዪቱ አትነቀልም፤ አትፈርስምም።”

Korean Living Bible

예레미야 31:1-40

1여호와께서 말씀하신다. “그 때에 내가 이스라엘 모든 가족의 하나님이 되고 그들은 내 백성이 될 것이다.

2이스라엘 백성이 안식을 찾아갈 때에 광야에서 칼날을 피한 자들이 은혜를 얻었다.

3그때 나 여호와는 이스라엘 백성에게 나타나 ‘내가 영원한 사랑으로 너희를 사랑하였으므로 한결같은 사랑으로 너희를 인도하였다’ 하고 말하였다.

4이스라엘 백성아, 내가 다시 너희를 일으켜 세우겠다. 너희가 소고를 들고 즐겁게 춤출 것이다.

5너희가 다시 사마리아 산에 포도나무를 심을 것이며 그것을 심은 자가 그 과일을 먹을 것이다.

6에브라임 산에서 파수꾼들이 ‘자, 시온으로 올라가서 우리 하나님 여호와께 나아가자!’ 하고 외칠 날이 올 것이다.”

7여호와께서 다시 말씀하신다. “너희는 이스라엘을 위해 기쁨으로 노래하라. 세계에서 가장 위대한 나라를 위해 외쳐라. 너희는 이렇게 선포하며 찬양하라. ‘여호와께서 자기 백성을 구원하시고 남은 자를 다 구출하셨다.’

8보라, 내가 그들을 북쪽 땅에서 인도해 내고 그들을 땅 끝에서부터 모을 것이니 소경과 절뚝발이와 임신부와 해산할 여인들과 함께 그들이 큰 민족이 되어 돌아올 것이다.

9그들은 돌아올 때 기쁨의 눈물을 흘리며 기도할 것이요 나는 그들이 넘어지지 않도록 그들을 평탄한 시냇가의 길로 인도할 것이다. 이것은 내가 이스라엘의 아버지이며 에브라임은 나의 장남이기 때문이다.

10“모든 민족들아, 너희는 나 여호와의 말을 듣고 먼 해안 지역에 전파하라. ‘이스라엘 백성을 흩으신 자가 그들을 모으시고 목자가 자기 양떼를 지키듯이 그들을 지키실 것이다.’

11나 여호와가 이스라엘을 해방시키고 그들을 강한 자의 손에서 구할 것이다.

12그들은 돌아와 시온산에서 기쁨으로 노래할 것이며 나의 선물인 곡식과 새 포도주와 기름과 양떼와 소떼를 보고 기뻐할 것이다. 그들은 물을 댄 동산 같아서 다시는 걱정할 일이 없을 것이다.

13그때 처녀들이 춤을 추고 기뻐할 것이며 청년들과 노인들이 함께 즐거워할 것이다. 나는 그들의 슬픔이 변하여 기쁨이 되게 하고 그들을 위로하여 근심 대신 기쁨을 주겠다.

14내가 제사장들에게 풍성한 것으로 채우며 내 백성들을 나의 좋은 것으로 만족하게 할 것이다. 이것은 나 여호와의 말이다.”

15여호와께서 말씀하신다. “라마에서 한 소리가 들리니 슬퍼하고 통곡하는 소리이다. 라헬이 자식을 잃고 슬퍼하며 위로 받기를 거절하는구나.”

16여호와께서 다시 말씀하신다. “너는 울음을 그치고 눈물을 거두어라. 네 일이 보상받을 것이며 네 자식들이 원수의 땅에서 돌아올 것이다.

17너의 미래에 희망이 있을 것이니 그들이 고향 땅으로 돌아올 것이다. 이것은 나 여호와의 말이다.

18“나는 에브라임이 이렇게 탄식하는 소리를 들었다. ‘주께서 나를 징계하시므로 내가 길들지 않은 송아지처럼 징계를 받았습니다. 주는 나의 하나님 여호와이십니다. 나를 회복시키소서. 그러면 내가 돌아가겠습니다.

19나는 주를 떠난 후에 곧 뉘우쳤고 깨달은 후에는 가슴을 치며 슬퍼했습니다. 나는 젊었을 때 지은 죄로 창피해서 견딜 수 없었습니다.’

20“에브라임은 나의 사랑하는 아들이요 기뻐하는 자식이 아니냐? 내가 가끔 그를 꾸짖긴 하지만 나는 여전히 그를 기억하고 있다. 그러므로 내 마음이 그를 그리워하게 되니 내가 그를 불쌍히 여길 것이다. 이것은 나 여호와의 말이다.

21“처녀 이스라엘아, 너를 위해 도로 표지판을 세우고 안내판을 세워라. 그래서 네가 가는 길을 눈여겨 보았다가 돌아오너라. 네 성으로 돌아오너라.

22신실치 못한 딸아, 네가 언제까지 방황하겠느냐? 나 여호와가 이 땅에 새로운 일이 일어나게 할 것이니 31:22 또는 ‘여자가 남자를 안으리라’여자가 남자를 둘러싸고 보호하는 것과 같은 아주 색다른 일이다.”

23전능하신 여호와 이스라엘의 하나님이 말씀하신다. “내가 포로들을 다시 그들의 땅으로 돌아오게 할 때에 그들이 유다 땅과 그 모든 성에서 다시 이런 말을 쓸 것이다. ‘의의 처소여, 거룩한 산이여, 여호와께서 너를 축복하시기 원하노라.’

24“그리고 백성들이 유다와 그 모든 성에 함께 살 것이며 거기는 농부들과 양떼를 인도하는 목자들도 있을 것이다.

25내가 피곤한 자를 상쾌하게 하고 지쳐 있는 자를 만족하게 하겠다.”

26이때 나는 깨어나 단잠을 자고 난 것을 알게 되었다.

27여호와께서 말씀하신다. “보라, 내가 이스라엘과 유다 땅에 사람과 짐승의 수를 헤아릴 수 없이 많게 할 날이 올 것이다.

28내가 그들을 철저하게 뽑고 파괴하며 허물고 엎어 버리며 멸망시키고 재앙으로 쳤던 것처럼 앞으로는 철저하게 그들을 세우고 심을 것이다.

29그때 백성들은 ‘아버지가 신 포도를 먹었는데 아들의 이가 시다’ 는 말을 더 이상 하지 않을 것이다.

30그러므로 신 포도를 먹는 그 사람만 이가 시게 되는 것처럼 모든 사람은 자기 자신의 죄에 대해서만 책임을 지고 죽게 될 것이다.”

31여호와께서 말씀하신다. “내가 이스라엘 및 유다 백성과 새로운 계약을 맺을 날이 올 것이다.

32이 계약은 내가 그들의 조상들을 이집트에서 인도해 내던 때에 맺은 계약과 같지 않을 것이다. 나는 그들에게 남편처럼 되었으나 그들은 나와 맺은 계약을 어겼다.

33그러나 그 후에 내가 이스라엘 백성과 맺을 새로운 계약은 이렇다: 내가 나의 법을 그들 속에 새기고 그들의 마음에 기록할 것이다. 그리고 나는 그들의 하나님이 되고 그들은 내 백성이 될 것이다.

34그 때에는 아무도 자기 형제나 이웃에게 나를 알도록 가르칠 필요가 없을 것이다. 이것은 모든 사람이 다 나를 알게 될 것이기 때문이다. 내가 그들의 잘못을 용서하고 다시는 그들의 죄를 기억하지 않을 것이다. 이것은 나 여호와의 말이다.”

35낮에 빛을 내는 해를 주시고 달과 별들의 질서를 정하셔서 밤을 비추게 하시며 바다를 휘저어 성난 파도를 일으키시는 여호와, 그의 이름은 전능하신 여호와이시다.

36여호와께서 말씀하신다. “이런 자연 질서가 지속되는 한 이스라엘도 언제까지나 나라로서 존속할 것이다.

37하늘이 측량되고 땅의 기초가 탐지된다면 몰라도 그런 일이 있기 전에는 이스라엘 백성이 죄를 지었다는 이유로 내가 그들을 버리지 않을 것이다.”

38여호와께서 말씀하신다. “예루살렘은 북동쪽의 하나넬 망대에서부터 북서쪽의 모퉁이문까지 나 여호와의 성으로 건설될 것이다.

39그 경계선은 다시 모퉁이문에서부터 서쪽으로 가렙산에 곧게 이어지고 거기서 고아를 돌 것이다.

40그리고 죽은 사람의 시체나 재를 버리는 골짜기와 기드론 시내와 동쪽으로 말문에 이르는 모든 밭이 다 나 여호와의 성지가 되고 다시는 허물어지거나 파괴되는 일이 없을 것이다.”