ኤርምያስ 30 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 30:1-24

የእስራኤል ሕዝብ መመለስ

1ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ ኤርምያስ የመጣው ቃል ይህ ነው፤ 2“የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የነገርሁህን ቃል ሁሉ በመጽሐፍ ጻፈው። 3እነሆ፣ ሕዝቤን እስራኤልንና ይሁዳን’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘ለአባቶቻቸው ወደ ሰጠኋት ምድር የምመልስበት ጊዜ ተቃርቧል፤30፥3 ወይም የሕዝቤን የእስራኤልንና የይሁዳን ዕድል ፈንታ እመልሳለሁ እነርሱም ይወርሷታል’ ይላል እግዚአብሔር።”

4እግዚአብሔር ስለ እስራኤልና ስለ ይሁዳ የተናገረው ቃል ይህ ነው፤ 5እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘የፍርሀትና የሽብር ጩኸት ተሰምቷል፤

ሰላምም የለም።

6እስቲ ጠይቁ፤ ተመልከቱም፤

ወንድ መውለድ ይችላል?

ታዲያ ወንድ ሁሉ ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

እጁን በሆዱ ላይ አድርጎ፣

የሰውስ ሁሉ ፊት ጠቍሮ የማየው ለምንድን ነው?

7ያ ቀን ምንኛ አስጨናቂ ይሆናል!

እንደዚያም ያለ አይኖርም፤

ለያዕቆብ የመከራ ጊዜ ነው፤

ነገር ግን ይተርፋል።

8“ ‘በዚያን ቀን’ ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

‘በጫንቃቸው ላይ ያለውን ቀንበር እሰብራለሁ፤

እስራታቸውንም እበጥሳለሁ፤

ከእንግዲህ ባዕዳን አይገዟቸውም።

9ነገር ግን ለአምላካቸው ለእግዚአብሔር

ለማስነሣላቸውም ለንጉሣቸው፣

ለዳዊት ይገዛሉ።

10“ ‘ስለዚህ፤ አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፤ አትፍራ፤

እስራኤል ሆይ፤ አትደንግጥ፤’

ይላል እግዚአብሔር

‘አንተን ከሩቅ አገር፣

ዘርህንም ከተማረኩበት ምድር እታደጋለሁ፤

ያዕቆብ ተመልሶ በሰላምና በርጋታ ይቀመጣል፤

የሚያስፈራውም አይኖርም።

11እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፤ አድንሃለሁም’

ይላል እግዚአብሔር

‘በአሕዛብ መካከል በትኜሃለሁ፤

እነዚህን አሕዛብ ሁሉ ፈጽሜ አጠፋለሁ፤

አንተን ግን ሙሉ በሙሉ አላጠፋህም፤

በመጠኑ እቀጣሃለሁ እንጂ፣

ያለ ቅጣት አልተውህም።’

12እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ስብራትህ የማይጠገን፣

ቍስልህም የማይድን ነው።

13የሚሟገትልህ ሰው የለም፤

ለቍስልህ መድኃኒት አይኖርም፤

ፈውስም አታገኝም።

14ወዳጆችህ ሁሉ ረስተውሃል፤

ስለ አንተም ግድ የላቸውም።

ጠላት እንደሚመታ መታሁህ፤

እንደ ጨካኝም ቀጣሁህ፤

በደልህ ታላቅ፣

ኀጢአትህም ብዙ ነውና።

15ፈውስ ለማይገኝለት ሕመምህ፣

ስለ ቍስልህ ለምን ትጮኻለህ?

በደልህ ታላቅ፣ ኀጢአትህም ብዙ ስለሆነ፣

እነዚህን ሁሉ አድርጌብሃለሁና።

16“ ‘ነገር ግን አሟጥጠው የበሉህ ሁሉ እንደዚያው ይበላሉ፤

ጠላቶችህ ሁሉ ለምርኮ ዐልፈው ይሰጣሉ፤

የሚዘርፉህ ይዘረፋሉ፤

የሚበዘብዙህም ሁሉ ይበዘበዛሉ።

17አንተን ግን መልሼ ጤነኛ አደርግሃለሁ፤

ቍስልህንም እፈውሳለሁ፤’

ይላል እግዚአብሔር

‘የተናቀች፣

ማንም የማይፈልጋት ጽዮን’ ብለውሃልና።

18እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘እነሆ የያዕቆብን ድንኳን ምርኮ እመልሳለሁ፤

ለማደሪያውም እራራለሁ፤

ከተማዪቱ በፍርስራሿ ጕብታ ላይ ትሠራለች፤

ቤተ መንግሥቱም በቀድሞ ቦታው ይቆማል።

19ከእነርሱም የምስጋና መዝሙር፣

የእልልታ ድምፅ ይሰማል።

እኔ አበዛቸዋለሁ፤

ቍጥራቸውም አይቀንስም፣

አከብራቸዋለሁ፤

የተናቁም አይሆኑም።

20ልጆቻቸው እንደ ቀድሞው ይሆናሉ፤

ማኅበረ ሰቡም በፊቴ የጸና ይሆናል፤

የሚጨቍኗቸውን ሁሉ እቀጣለሁ።

21መሪያቸው ከራሳቸው ወገን ይሆናል፤

ገዣቸውም ከመካከላቸው ይነሣል፤

ወደ እኔ አቀርበዋለሁ፤ እርሱም ይቀርበኛል፤

አለዚያማ ደፍሮ፣

ወደ እኔ የሚቀርብ ማን ነው?’ ይላል እግዚአብሔር

22‘ስለዚህ እናንተ ሕዝብ ትሆኑኛላችሁ፤

እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ።’ ”

23እነሆ፤ የእግዚአብሔር ማዕበል፣

በቍጣ ይነሣል፤

የሚገለባብጥም ዐውሎ ነፋስ፣

በክፉዎች ዐናት ላይ ይወርዳል።

24የልቡን ሐሳብ ሳይፈጽም፣

የእግዚአብሔር ቍጣ፣

እንዲሁ አይመለስም፤

በሚመጡትም ዘመናት፣

ይህን ታስተውላላችሁ።

New International Version – UK

Jeremiah 30:1-24

Restoration of Israel

1This is the word that came to Jeremiah from the Lord: 2‘This is what the Lord, the God of Israel, says: “Write in a book all the words I have spoken to you. 3The days are coming,” declares the Lord, “when I will bring my people Israel and Judah back from captivity30:3 Or will restore the fortunes of my people Israel and Judah and restore them to the land I gave to their ancestors to possess,” says the Lord.’

4These are the words the Lord spoke concerning Israel and Judah: 5‘This is what the Lord says:

‘ “Cries of fear are heard –

terror, not peace.

6Ask and see:

can a man bear children?

Then why do I see every strong man

with his hands on his stomach like a woman in labour,

every face turned deathly pale?

7How awful that day will be!

No other will be like it.

It will be a time of trouble for Jacob,

but he will be saved out of it.

8‘ “In that day,” declares the Lord Almighty,

“I will break the yoke off their necks

and will tear off their bonds;

no longer will foreigners enslave them.

9Instead, they will serve the Lord their God

and David their king,

whom I will raise up for them.

10‘ “So do not be afraid, Jacob my servant;

do not be dismayed, Israel,”

declares the Lord.

“I will surely save you out of a distant place,

your descendants from the land of their exile.

Jacob will again have peace and security,

and no-one will make him afraid.

11I am with you and will save you,”

declares the Lord.

“Though I completely destroy all the nations

among which I scatter you,

I will not completely destroy you.

I will discipline you but only in due measure;

I will not let you go entirely unpunished.”

12‘This is what the Lord says:

‘ “Your wound is incurable,

your injury beyond healing.

13There is no-one to plead your cause,

no remedy for your sore,

no healing for you.

14All your allies have forgotten you;

they care nothing for you.

I have struck you as an enemy would

and punished you as would the cruel,

because your guilt is so great

and your sins so many.

15Why do you cry out over your wound,

your pain that has no cure?

Because of your great guilt and many sins

I have done these things to you.

16‘ “But all who devour you will be devoured;

all your enemies will go into exile.

Those who plunder you will be plundered;

all who make spoil of you I will despoil.

17But I will restore you to health

and heal your wounds,” declares the Lord,

“because you are called an outcast,

Zion for whom no-one cares.”

18‘This is what the Lord says:

‘ “I will restore the fortunes of Jacob’s tents

and have compassion on his dwellings;

the city will be rebuilt on her ruins,

and the palace will stand in its proper place.

19From them will come songs of thanksgiving

and the sound of rejoicing.

I will add to their numbers,

and they will not be decreased;

I will bring them honour,

and they will not be disdained.

20Their children will be as in days of old,

and their community will be established before me;

I will punish all who oppress them.

21Their leader will be one of their own;

their ruler will arise from among them.

I will bring him near and he will come close to me –

for who is he who will devote himself

to be close to me?”

declares the Lord.

22“So you will be my people,

and I will be your God.” ’

23See, the storm of the Lord

will burst out in wrath,

a driving wind swirling down

on the heads of the wicked.

24The fierce anger of the Lord will not turn back

until he fully accomplishes

the purposes of his heart.

In days to come

you will understand this.