ኤርምያስ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 3:1-25

1“ሰው ሚስቱን ቢፈታ፣

እርሷም ሄዳ ሌላ ሰው ብታገባ፣

ወደ እርሷ ይመለሳልን?

ምድሪቱስ ፈጽማ አትረክስምን?

አንቺ ግን ከብዙ ወዳጆችሽ ጋር አመንዝረሻል፤

ታዲያ አሁን ወደ እኔ መመለስ ትፈልጊያለሽን?”

ይላል እግዚአብሔር

2“እስቲ ቀና ብለሽ ጭር ያሉትን ኰረብቶች ተመልከቺ፣

በርኩሰት ያልተጋደምሽበት ቦታ ይገኛልን?

በበረሓ እንደ ተቀመጠ ዘላን ዐረብ፣

በየመንገዱ ዳር ተቀምጠሽ ወዳጆችሽን ጠበቅሽ።

በዝሙትሽና በክፋትሽ፣

ምድሪቱን አረከስሽ።

3ስለዚህ ካፊያ ተከለከለ፤

ኋለኛው ዝናብም ጠፋ።

አንቺ ግን አሁንም የጋለሞታ ገጽታ አለብሽ፤

ዐይንሽን በዕፍረት አልሰብር ብለሻል።

4አሁንም ወደ እኔ ተጣርተሽ፣

‘አባቴ፣ የልጅነት ወዳጄ፣

5ሁልጊዜ ትቈጣለህን?

ቍጣህስ ለዘላለም ነውን?’ አላልሽኝም?

የምትናገሪው እንዲህ ነው፤

ይሁን እንጂ የቻልሽውን ክፋት ሁሉ ታደርጊያለሽ።”

ከዳተኛዋ እስራኤል

6እግዚአብሔር በንጉሥ ኢዮስያስ ዘመን እንዲህ አለኝ፤ “ከዳተኛዪቱ እስራኤል ያደረገችውን አየህን? ከፍ ወዳለው ኰረብታ ሁሉ ወጥታ፣ ወደ ለመለመው ዛፍ ሥር ሁሉ ሄዳ በዚያ አመነዘረች። 7ይህን ሁሉ ካደረገች በኋላ፣ ወደ እኔ ትመለሳለች ብዬ ነበር፤ ሆኖም አልተመለሰችም፤ ከሓዲዋ እኅቷ ይሁዳም ይህን አየች። 8ለከዳተኛዪቱ እስራኤል ስለ ምንዝርናዋ ሁሉ የፍች ወረቀቷን ሰጥቼ አባረርኋት። ከሓዲዋ እኅቷ ይሁዳም ይህን አይታ እንዳልፈራች አየሁ፤ ወጥታም አመነዘረች። 9በቅሌቷም ምድሪቱን አረከሰች፤ ከድንጋይና ከግንድ ጋር አመነዘረች፤ 10ይህም ሁሉ ሆኖ ከሓዲዋ እኅቷ ይሁዳ ወደ እኔ የተመለሰችው በማስመሰል እንጂ በሙሉ ልቧ አልነበረም” ይላል እግዚአብሔር

11እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፤ “ከከሓዲዋ ይሁዳ ይልቅ ከዳተኛዪቱ እስራኤል ጻድቅ ሆና ተገኘች። 12ሂድና ይህን መልእክት ወደ ሰሜን እንዲህ ብለህ ተናገር፤

“ ‘ከዳተኛዪቱ እስራኤል ሆይ፤ ተመለሽ’ ይላል እግዚአብሔር

‘እኔ መሓሪ ስለሆንሁ፣

ከእንግዲህ በቍጣ ዐይን አላይሽም’

ይላል እግዚአብሔር። ‘ለዘላለም አልቈጣም።

13በአምላክሽ በእግዚአብሔር ላይ በማመፅሽ፣

ክብርሽንም ለእንግዶች አማልክት፣

በየለምለሙ ዛፍ ሥር አሳልፈሽ በመስጠት፣

ለእኔ ባለመታዘዝሽ፣

በደለኛ መሆንሽን ይህን አንድ ነገር ብቻ እመኚ’ ”

ይላል እግዚአብሔር

14“ከዳተኛ ልጆች ሆይ፤ እኔ ባለቤታችሁ ነኝና ተመለሱ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ከአንድ ከተማ አንድ፣ ከአንድ ነገድ ሁለት መርጫችሁ ወደ ጽዮን አመጣችኋለሁ። 15እንደ ልቤም የሆኑ፣ በዕውቀትና በማስተዋል የሚመሯችሁን እረኞች እሰጣችኋለሁ። 16ቍጥራችሁ በምድሪቱ እጅግ በሚበዛበት ጊዜም” ይላል እግዚአብሔር፤ “በዚያ ዘመን፣ ‘የእግዚአብሔር የኪዳኑ ታቦት’ ብለው ከእንግዲህ አይጠሩም፤ ትዝ አይላቸውም፤ አያስታውሱትምም፤ አይጠፋም፤ ሌላም አይሠራም። 17በዚያ ጊዜ ኢየሩሳሌምን፣ ‘የእግዚአብሔር ዙፋን’ ብለው ይጠሯታል፤ መንግሥታትም ሁሉ የእግዚአብሔርን ስም ለማክበር በኢየሩሳሌም ይሰበሰባሉ፤ የክፉ ልባቸውንም እልኸኝነት ከእንግዲህ አይከተሉም። 18በዚያን ዘመን የይሁዳ ቤትና የእስራኤል ቤት በአንድነት ሆነው ከሰሜን ምድር ለአባቶቻቸው ርስት አድርጌ ወደ ሰጠኋቸው ምድር ይመጣሉ።

19“እኔም፣

“ ‘የተመረጠችውን ምድር፣

የትኛውም ሕዝብ ያላገኘውን የተዋበች ርስት ልሰጥሽ፣

እንደ ወንዶች ልጆቼ ምንኛ በደስታ ልቍጠርሽ’ አልሁ፤

‘አባቴ’ ብለሽ የምትጠሪኝ፣

እኔንም ከመከተል ዘወር የማትዪ መስሎኝ ነበር።

20የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ለባሏ ታማኝ እንዳልሆነች ሚስት፣

ስታታልሉኝ ኖራችኋል፤”

ይላል እግዚአብሔር

21እግዚአብሔር አምላካቸውን በመርሳት፣

መንገዳቸውን አጣመዋልና፣

የእስራኤል ሕዝብ ጩኸት፣

አሳዛኝ ልቅሶ ባድማ ከሆኑት ኰረብታዎች ተሰማ።

22“እናንት ከዳተኞች ልጆች ተመለሱ፤

ከዳተኝነታችሁን እፈውሳለሁ።

“አንተ እግዚአብሔር አምላካችን ነህና፤

አዎን፤ ወደ አንተ እንመጣለን።

23በርግጥ በኰረብቶች ላይ፣

እንዲሁም በተራሮች ላይ፣ ሆ! ብለን መውጣታችን መታለል ነው፤

በርግጥ የእስራኤል መዳን፣

በአምላካችን በእግዚአብሔር ነው።

24ከለጋ ዕድሜያችን ጀምሮ፣

የአባቶቻችንን የድካም ፍሬዎች፣

በጎቻቸውንና ከብቶቻቸውን፣

ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን፣ ነውረኛ ጣዖቶች በሏቸው።

25እንግዲህ ዕፍረታችንን ተከናንበን እንተኛ፤

ውርደታችንም ይሸፍነን፤

እኛም አባቶቻችንም፣

እግዚአብሔር አምላካችንን በድለናልና፤

ከልጅነታችን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ፣

አምላካችንን እግዚአብሔርን አልታዘዝንም።”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 3:1-25

1“หากชายใดหย่าขาดจากภรรยา

และนางไปแต่งงานกับชายอีกคน

เขาควรจะกลับไปหานางอีกหรือ?

จะไม่ทำให้แผ่นดินแปดเปื้อนมลทินไปหมดหรอกหรือ?

แต่เจ้าก็ใช้ชีวิตเยี่ยงโสเภณีที่มีชู้รักหลายคน

บัดนี้เจ้าจะกลับมาหาเราหรือ?”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

2“จงแหงนหน้ามองบนที่สูงอันเริศร้างทั้งหลาย

ดูเถิด มีที่ไหนบ้างที่เจ้าไม่ได้ไปทำตัวแปดเปื้อนด้วยการล่วงประเวณี?

เจ้านั่งคอยบรรดาชู้รักอยู่ริมทาง

นั่งคอยเหมือนชนเผ่าเร่ร่อน3:2 หรือคนอาหรับในทะเลทราย

เจ้าทำให้แผ่นดินเป็นมลทิน

เนื่องด้วยความสำส่อนและความชั่วร้ายของเจ้า

3ฉะนั้นฝนจึงถูกระงับเสีย

และฝนฤดูใบไม้ผลิก็ไม่ตกลงมา

ถึงกระนั้นเจ้าก็ยังหน้าด้านเหมือนหญิงโสเภณี

เจ้าไม่มียางอายเอาเสียเลย

4เจ้าเพิ่งร้องทูลเราไม่ใช่หรือว่า

‘พระบิดาของข้าพระองค์ ผู้ทรงเป็นมิตรสหายมาตั้งแต่ข้าพระองค์ยังแรกรุ่น

5พระองค์จะกริ้วอยู่เนืองนิตย์หรือ?

พระพิโรธของพระองค์จะคงอยู่ตลอดไปหรือ?’

เจ้าพูดเช่นนี้แหละ

แต่เจ้าก็ยังคงทำชั่วทุกอย่างอยู่ร่ำไป”

อิสราเอลผู้ไม่ซื่อสัตย์

6ในรัชสมัยของกษัตริย์โยสิยาห์ องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสกับข้าพเจ้าว่า “เจ้าเห็นสิ่งที่อิสราเอลผู้นอกใจทำหรือไม่? อิสราเอลคบชู้ด้วยการเที่ยวไปนมัสการพระต่างๆ บนภูเขาสูงทุกลูกและใต้ต้นไม้ใบดกทุกต้น 7เราคิดว่าหลังจากที่อิสราเอลได้ทำทุกสิ่งเหล่านี้แล้ว นางจะกลับมาหาเรา แต่ก็เปล่า และยูดาห์น้องสาวผู้ไร้สัตย์ของนางก็เห็น 8เราจึงทำหนังสือหย่าขาดจากอิสราเอลผู้นอกใจและไล่นางไปเพราะการคบชู้ทั้งหมดของนาง แต่ถึงอย่างนั้นเราก็ได้เห็นว่ายูดาห์น้องสาวผู้ไร้สัตย์ของนางไม่ขยาดกลัวเลย ยูดาห์เองก็ออกไปคบชู้ด้วย 9เพราะนางเห็นว่าความเสื่อมศีลธรรมของอิสราเอลเป็นเรื่องเล็กน้อย นางจึงทำให้แผ่นดินเป็นมลทิน และคบชู้โดยไปนมัสการรูปเคารพซึ่งทำจากไม้และหิน 10ถึงขนาดนี้แล้ว ยูดาห์น้องสาวผู้ไร้สัตย์ของนางก็ยังไม่หวนกลับมาหาเราอย่างสุดใจ มีแต่เสแสร้งแกล้งทำ” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

11องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “อิสราเอลผู้ไม่ซื่อก็ยังชอบธรรมกว่ายูดาห์ผู้ไร้สัตย์ 12บัดนี้จงไปประกาศแก่พวกทางเหนือว่า

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า ‘อิสราเอลผู้ไม่ซื่อเอ๋ย กลับมาเถิด

เราจะไม่หน้าบึ้งใส่เจ้าอีกต่อไป

เพราะเราเปี่ยมด้วยเมตตา’ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้

‘เราจะไม่โกรธขึ้งตลอดไป

13เพียงแต่เจ้ายอมรับผิด

ว่าเจ้าได้กบฏต่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของเจ้า

เจ้าได้ปันใจให้พระต่างชาติทั้งหลาย

ใต้ต้นไม้ใบดกทุกต้น

และไม่ได้เชื่อฟังเรา’ ”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

14“หันกลับมาเถิด ประชากรที่ไม่ซื่อสัตย์” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้ “เพราะเราเป็นสามีของเจ้า เราจะเลือกสรรเจ้าคนหนึ่งจากเมืองหนึ่งและสองคนจากตระกูลหนึ่ง และจะนำเจ้ากลับมายังศิโยน 15แล้วเราจะให้บรรดาผู้เลี้ยงซึ่งถูกใจเราแก่เจ้า ผู้ที่จะนำเจ้าด้วยความรู้และความเข้าใจ 16เมื่อถึงเวลานั้น เมื่อเจ้ามีลูกเต็มบ้านมีหลานเต็มเมืองในแผ่นดินนั้น” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้ “ผู้คนจะไม่พูดถึง ‘หีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้า’ อีก จะไม่คิดถึง ไม่จดจำ ไม่ถวิลหา และไม่สร้างหีบพันธสัญญาขึ้นมาใหม่ 17แต่ในเวลานั้น พวกเขาจะเรียกเยรูซาเล็มว่า ‘พระบัลลังก์ขององค์พระผู้เป็นเจ้า’ ประชาชาติทั้งปวงจะมาชุมนุมกันที่กรุงเยรูซาเล็มเพื่อถวายพระเกียรติแด่พระนามของพระยาห์เวห์ พวกเขาจะไม่ดื้อดึงทำตามใจชั่วของตนอีกต่อไป 18เมื่อถึงเวลานั้นพงศ์พันธุ์ยูดาห์จะสมทบกับพงศ์พันธุ์อิสราเอล พวกเขาจะรวมกันมาจากดินแดนทางเหนือ มายังดินแดนซึ่งเราได้ยกให้เป็นกรรมสิทธิ์แก่บรรพบุรุษของเจ้าทั้งหลาย

19“เราเองลั่นวาจาไว้ว่า

“ ‘เรายินดีเหลือเกินที่จะปฏิบัติต่อเจ้าเยี่ยงลูก

และมอบดินแดนอันน่าปรารถนาแก่เจ้า

เป็นสมบัติอันงดงามที่สุดของชาติต่างๆ’

เราคิดว่าเจ้าจะเรียกเราว่า ‘พ่อ’

และจะติดตามเราโดยไม่หันหนีไปไหนอีกเลย

20แต่พงศ์พันธุ์อิสราเอลเอ๋ย เจ้าก็ไม่ซื่อสัตย์ต่อเรา

เหมือนภรรยาที่ไม่ซื่อสัตย์ต่อสามี”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

21มีเสียงหนึ่งร่ำไห้ดังจากยอดเขาอันเปล่าเปลี่ยว

เป็นเสียงร่ำไห้อ้อนวอนของชนอิสราเอล

เพราะพวกเขาได้บิดเบือนวิถีทางของตน

และได้ลืมพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกเขา

22“กลับมาเถิด ประชากรผู้ไม่ซื่อสัตย์

เราจะรักษาเจ้าจากการหลงผิด”

“แน่แล้ว ข้าพระองค์ทั้งหลายจะมาหาพระองค์

เพราะพระองค์ทรงเป็นพระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพระองค์ทั้งหลาย

23แท้จริงการกราบไหว้รูปเคารพบนเนินเขาและภูเขาต่างๆ

ล้วนเป็นเรื่องหลอกลวงและไร้ประโยชน์

แท้จริงความรอดของอิสราเอล

อยู่ในพระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพระองค์ทั้งหลาย

24ตั้งแต่ข้าพระองค์ทั้งหลายยังเยาว์วัย เทพเจ้าอันน่าอับอายเหล่านั้นได้ล้างผลาญ

ผลแห่งหยาดเหงื่อแรงงานของบรรพบุรุษของข้าพระองค์ทั้งหลาย

ทั้งฝูงแพะแกะและฝูงสัตว์

ลูกชายและลูกสาว

25ให้ข้าพระองค์ทั้งหลายนอนลงด้วยความอับอาย

และเอาความอัปยศอดสูคลุมกาย

ทั้งข้าพระองค์ทั้งหลายและบรรพบุรุษ

ได้ทำบาปต่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพระองค์ทั้งหลาย

ตั้งแต่ข้าพระองค์ทั้งหลายยังเยาว์วัยตราบจนบัดนี้

ข้าพระองค์ทั้งหลายไม่ได้เชื่อฟังพระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพระองค์ทั้งหลาย”