ኤርምያስ 29 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 29:1-32

በምርኮ ላሉት የተላከ ደብዳቤ

1ነቢዩ ኤርምያስ በምርኮ ተወስደው በሕይወት ለቀሩት ሽማግሌዎች፣ ለካህናቱ፣ ለነቢያቱና ናቡከደነፆር ከኢየሩሳሌም ወደ ባቢሎን ማርኮ ለወሰዳቸው ሕዝብ ሁሉ የላከው የደብዳቤ ቃል ይህ ነው፤ 2ይህም የሆነው ንጉሡ ኢኮንያን29፥2 ኢኮንያን የኢዮአኪን ሌላው አቻ ስም ነው እቴጌዪቱ እናቱ፣ የቤተ መንግሥቱ ባለሟሎች፣ የይሁዳና የኢየሩሳሌም መሪዎች፣ ዐናጺዎችና ብረት ቀጥቃጮች ተማርከው ከኢየሩሳሌም ከተወሰዱ በኋላ ነበር። 3ደብዳቤውንም ከይሁዳ ንጉሥ ከሴዴቅያስ ወደ ባቢሎን ንጉሥ ወደ ናቡከደነፆር በተላኩት መልእክተኞች በሳፋን ልጅ በኤልዓሣና በኬልቅያስ ልጅ በገማርያ እጅ ላከው፤ ደብዳቤውም እንዲህ የሚል ነበር፤

4የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣ ከኢየሩሳሌም ወደ ባቢሎን ላስማረካቸው ሁሉ እንዲህ ይላል፤ 5“ቤት ሠርታችሁ ተቀመጡ፤ አትክልት ተክላችሁ ፍሬውን ብሉ፤ 6አግብታችሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ውለዱ፤ ወንዶች ልጆቻችሁንና ሴቶች ልጆቻችሁን አጋቡ፤ እነርሱም ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ይውለዱ፤ ቍጥራችሁም በዚያ ምድር ይብዛ እንጂ አይነስ። 7ተማርካችሁ ለሄዳችሁባት ከተማ ሰላምና ብልጽግናን እሹ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጸልዩላት፤ ምክንያቱም እርሷ ብትበለጽግ እናንተም ትበለጽጋላችሁ።” 8የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በርግጥ እንዲህ ይላልና፤ “በመካከላችሁ ያሉት ነቢያትና ጠንቋዮች አያታልሏችሁ፤ የሚያልሙላችሁንም ሕልም አትስሙ፤ 9በስሜ ሐሰተኛ ትንቢት ይነግሯችኋል እንጂ እኔ አልላክኋቸውም” ይላል እግዚአብሔር

10እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ሰባው ዓመት የባቢሎን ቈይታችሁ በተፈጸመ ጊዜ እጐበኛችኋለሁ፤ ወደዚህም ሥፍራ ልመልሳችሁ የገባሁላችሁን መልካሚቱን ቃሌን እፈጽምላችኋለሁ። 11ለእናንተ ያለኝን ዕቅድ እኔ ዐውቃለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ዕቅዱም ፍጻሜው ያማረና ተስፋ የሚሰጥ፣ እናንተንም የሚጠቅም እንጂ የሚጐዳ አይደለም። 12እናንተም ትጠሩኛላችሁ፤ ቀርባችሁ ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፤ እኔም እሰማችኋለሁ። 13እናንተ ትፈልጉኛላችሁ፤ በፍጹም ልባችሁም ከፈለጋችሁኝ ታገኙኛላችሁ፤ 14እኔም እገኝላችኋለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ከምርኮም29፥14 ወይም ዕድል ፈንታችሁን እመልስላችኋለሁ እመልሳችኋለሁ፤ እናንተንም ከበተንሁበት አገርና ስፍራ ሁሉ እመልሳችኋለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “በምርኮ ምክንያት ወዳስለቀቅኋችሁም ምድር እመልሳችኋለሁ።”

15እናንተም፣ “እግዚአብሔር በባቢሎን ነቢያት አስነሥቶልናል” ትላላችሁ፤ 16እግዚአብሔር ግን በዳዊት ዙፋን ላይ ስለሚቀመጠው ንጉሥና ከእናንተ ጋር ተማርኮ ስላልሄደው ወገንህ በዚህ ከተማ ስለ ቀረው ሕዝብ ሁሉ እንዲህ ይላል፤ 17የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በርግጥ እንዲህ ይላል፤ “ሰይፍን፣ ራብንና መቅሠፍትን እሰድድባቸዋለሁ፤ ከመበላሸቱ የተነሣም ሊበላ እንደማይቻል እንደ መጥፎ የበለስ ፍሬ አደርጋቸዋለሁ። 18በሰይፍ፣ በራብና በመቅሠፍት አሳድዳቸዋለሁ፤ በምድር መንግሥታት ሁሉ ፊት የሚያስጸይፉ አደርጋቸዋለሁ፤ በማሳድድባቸውም ሕዝቦች ዘንድ የርግማንና የድንጋጤ፣ የመሣቂያና የመዘባበቻ ምልክት ይሆናሉ፤ 19በአገልጋዮቼ በነቢያት በኩል ደጋግሜ የላክሁላቸውን ቃሌን አልሰሙምና” ይላል እግዚአብሔር፤ “እናንተ ምርኮኞችም አልሰማችሁም” ይላል እግዚአብሔር

20ስለዚህ ከኢየሩሳሌም ወደ ባቢሎን የሰደድኋችሁ ምርኮኞች ሁሉ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ። 21የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በስሜ የሐሰት ትንቢት ስለሚነግሯችሁ ስለ ቆላያ ልጅ ስለ አክዓብና ስለ መዕሤያ ልጅ ስለ ሴዴቅያስ እንዲህ ይላል፤ “እነዚህን ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ፤ እርሱም ዐይናችሁ እያየ ይገድላቸዋል። 22በእነርሱ ላይ ከደረሰው የተነሣ በባቢሎን ያሉ የይሁዳ ምርኮኞች ሁሉ፣ ‘እግዚአብሔር፣ የባቢሎን ንጉሥ በእሳት እንደ ጠበሳቸው እንደ ሴዴቅያስና እንደ አክዓብ ያድርግብህ’ ብለው ይራገማሉ፤ 23ከባልንጀሮቻቸው ሚስቶች ጋር በማመንዘርና ያልነገርኋቸውን ቃል በስሜ በሐሰት በመናገር በእስራኤል ዘንድ በደል ፈጽመዋልና። ይህንም እኔ ዐውቃለሁ፤ ምስክር ነኝ” ይላል እግዚአብሔር

ለሸማያ የተላከ መልእክት

24“ለኔሔላማዊው ለሸማያ እንዲህ ብለህ ንገረው፤ 25‘የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በኢየሩሳሌም ላለው ሕዝብ ሁሉ፣ ለካህኑ ለመዕሤያ ልጅ ለሶፎንያስና ለሌሎችም ካህናት ሁሉ በገዛ ስምህ ደብዳቤዎችን ልከሃል፤ ለሶፎንያስም እንዲህ ብለሃል፤ 26በእግዚአብሔር ቤት ኀላፊ ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር በካህኑ በዮዳሄ ምትክ ካህን አድርጎ ሾሞሃል፤ ነቢይ ነኝ እያለ ትንቢት የሚናገር ማንኛውም ያበደ ሰው እግሩን በግንድ፣ ዐንገቱን በሰንሰለት መቀፍደድ ይገባሃል።” ’ 27ታዲያ፣ ነቢይ ነኝ ባዩን የዓናቶቱን ኤርምያስን ለምን አልገሠጽኸውም? 28ይህ ሰው፣ ‘የምርኮው ጊዜ ረዥም ስለሆነ፣ ቤት ሠርታችሁ ተቀመጡ፤ አትክልትም ተክላችሁ ፍሬውን ብሉ’ በማለት ወደ ባቢሎን መልእክት ልኮብናል።”

29ካህኑ ሶፎንያስም ደብዳቤውን ለነቢዩ ኤርምያስ አነበበለት። 30የእግዚአብሔርም ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 31“ይህን መልእክት በምርኮ ላሉት ሁሉ እንዲህ ብለህ ላክ፤ ስለ ኔሔላማዊው ስለ ሸማያ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እኔ ሳልልከው ሸማያ ትንቢት ተናግሮላችሁ፣ በሐሰት እንድትታመኑ አድርጓችኋልና፣ 32እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ ኔሔላማዊውን ሸማያንና ዘሩን እቀጣለሁ፤ በእኔ ላይ ዐመፅን ተናግሯልና፣ በዚህ ሕዝብ መካከል የሚተርፍ ዘር አይኖረውም” ’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘ለሕዝቤ የማደርገውንም መልካም ነገር አያይም።’ ”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

耶利米书 29:1-32

致信给被掳的人

1-2耶哥尼雅王、太后、宫廷侍臣、犹大耶路撒冷的官员、技工和工匠被尼布甲尼撒王掳到巴比伦后,耶利米先知从耶路撒冷寄信给被掳之人中幸存的长老、先知和众民。 3犹大西底迦沙番的儿子以利亚萨希勒迦的儿子基玛利把这封信送给巴比伦尼布甲尼撒。以下是信的内容:

4以色列的上帝——万军之耶和华对所有从耶路撒冷被掳到巴比伦的人说: 5“你们要建造房子住下来,要耕种田园,吃田中的出产。 6你们要娶妻生子,也要给你们的儿女娶妻选夫,使他们生儿育女,你们好在那里人丁兴旺,不致人口减少。 7你们要为所住的城市谋求福祉,向耶和华祷告,因为你们的福祉有赖于那城的福祉。” 8以色列的上帝——万军之耶和华说:“不要被你们中间的先知和占卜者欺骗,不要听信他们做的梦。 9他们以我的名义对你们说假预言,其实我并没有差遣他们。这是耶和华说的。”

10耶和华说:“你们被掳到巴比伦七十年期满后,我就要眷顾你们,成就我充满恩典的应许,把你们带回这地方。 11因为我知道我为你们安排的计划。我的计划不是要降祸给你们,而是要赐福给你们,使你们的未来充满希望。这是耶和华说的。 12那时,你们必呼求我,向我祷告,我也必垂听。 13你们寻求我,就必寻见。只要你们全心寻求我, 14我必让你们寻见。这是耶和华说的。我必把你们从流放之地招聚起来,使你们回到故土。这是耶和华说的。

15“你们说耶和华在巴比伦为你们选立了先知, 16但论到坐在大卫宝座上的君王和这城里的百姓,就是没有与你们一同被掳的同胞, 17万军之耶和华这样说,‘看啊,我必使战争、饥荒和瘟疫临到他们,使他们像烂得不能吃的无花果。 18我要使他们饱受战争、饥荒和瘟疫之灾,使他们的遭遇令天下万国惊惧。在我流放他们去的地方,他们必受凌辱、嘲笑、讥讽和咒诅。 19这都是因为他们不听我的话。这是耶和华说的。我曾屡次差遣我的仆人——众先知去警告他们,他们却不肯听。’这是耶和华说的。 20因此,你们这些从耶路撒冷被掳到巴比伦的人啊!要听耶和华的话。 21以色列的上帝——万军之耶和华说,‘哥赖雅的儿子亚哈玛西雅的儿子西底迦以我的名义说假预言,我要把他们交在巴比伦尼布甲尼撒的手中,让他当着你们的面处死他们。 22被掳到巴比伦犹大人咒诅人的时候会说,“愿耶和华使你的下场像被巴比伦王烧死的西底迦亚哈一样!” 23因为他们二人在以色列做了恶事,与他人的妻子通奸。我没有差派他们,他们却奉我的名说假预言。我知道他们的所作所为,我对这一切了如指掌。’这是耶和华说的。”

24耶和华吩咐我对尼希兰示玛雅说: 25以色列的上帝——万军之耶和华说,你曾以自己的名义写信给住在耶路撒冷的众民、玛西雅的儿子西番雅祭司及其他祭司。你在信中对西番雅说, 26‘耶和华已立你为祭司代替耶何耶大,管理耶和华的殿,负责拘捕妄自发预言的狂人,给他们戴上铁链枷锁。 27现在,亚拿突耶利米在你们当中自称为先知,你为什么不斥责他呢? 28他甚至寄信给我们这些在巴比伦的人,说被掳的日子还很长久,要我们建房子住下来,耕种田园,吃田中的出产。’”

29西番雅祭司就把示玛雅的信读给耶利米先知听。 30耶和华对耶利米说: 31“你派人送信给所有被掳的人,说,‘耶和华说祂没有差遣尼希兰示玛雅,他却说预言,诱使你们听信谎言, 32所以耶和华必惩罚他和他的后代,使他断子绝孙,看不到耶和华赐给祂子民的福祉,因为他说了悖逆耶和华的话。这是耶和华说的。’”