ኤርምያስ 26 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 26:1-24

በኤርምያስ ላይ የግድያ ዛቻ

1በይሁዳ ንጉሥ፣ በኢዮስያስ ልጅ፣ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ ላይ ይህ ቃል ከእግዚአብሔር ዘንድ መጣ፤ 2እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በእግዚአብሔር ቤት አደባባይ ቆመህ፣ ለማምለክ ወደ እግዚአብሔር ቤት ከይሁዳ ከተሞች ለሚመጣው ሕዝብ ሁሉ ተናገር፤ አንዲትም ቃል ሳታስቀር የማዝዝህን ሁሉ ንገራቸው። 3ምናልባትም ሰምተው እያንዳንዳቸው ከክፉ መንገዳቸው ይመለሱ ይሆናል፤ እኔም ስላደረጉት ክፋት ላመጣባቸው ያሰብሁትን ቅጣት እተዋለሁ። 4እንዲህም በላቸው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ባትሰሙኝና የሰጠኋችሁን ሕጌን ባትጠብቁ፣ 5ልትሰሟቸው ይገባ የነበረውን ወደ እናንተ ደጋግሜ የላክኋቸውን የአገልጋዮቼን የነቢያትን ቃል ባትሰሙ፣ 6ይህን ቤት እንደ ሴሎ አደርጋለሁ፤ ይህችንም ከተማ በምድር ሕዝብ ሁሉ ፊት የተረገመች አደርጋታለሁ።’ ”

7ኤርምያስ ይህን ቃል በእግዚአብሔር ቤት ሲናገር፣ ካህናቱና ነቢያቱ፣ ሕዝቡም ሁሉ ሰሙ። 8ነገር ግን ኤርምያስ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ሁሉ እንዲናገር ያዘዘውን ሁሉ ተናግሮ በጨረሰ ጊዜ፣ ካህናቱ፣ ነቢያቱና ሕዝቡም ሁሉ ይዘውት እንዲህ አሉ፤ “አንተ መገደል አለብህ! 9ይህ ቤት እንደ ሴሎ ይሆናል፤ ይህችም ከተማ ባድማና ወና ትሆናለች ብለህ በእግዚአብሔር ስም ለምን ትንቢት ትናገራለህ?” ሕዝቡም ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ተሰብስበው ኤርምያስን ከበቡት።

10የይሁዳም ባለሥልጣኖች ስለ እነዚህ ነገሮች በሰሙ ጊዜ፣ ከቤተ መንግሥት ወደ እግዚአብሔር ቤት ወጡ፤ በእግዚአብሔር ቤት፣ አዲሱ በር በተባለው መግቢያ ተቀመጡ። 11ካህናቱና ነቢያቱም ለባለሥልጣኖቹና ለሕዝቡ ሁሉ፣ “በጆሯችሁ እንደ ሰማችሁት ይህ ሰው በዚህች ከተማ ላይ ትንቢት ስለ ተናገረ ሞት ይገባዋል” አሉ።

12ኤርምያስም፣ ለባለሥልጣኖቹና ለሕዝቡ ሁሉ እንዲህ አለ፤ “የሰማችሁትን ሁሉ በዚህ ቤትና በዚህች ከተማ ላይ ትንቢት እንድናገር እግዚአብሔር ልኮኛል። 13አሁንም መንገዳችሁንና ሥራችሁን አስተካክሉ፣ አምላካችሁን እግዚአብሔርን ታዘዙ። እግዚአብሔርም በእናንተ ላይ ለማምጣት የተናገረውን ክፉ ነገር ይተዋል። 14ስለ እኔ ከሆነ ግን እነሆ፤ በእጃችሁ ነኝ፤ መልካምና ተገቢ መስሎ የሚታያችሁን ሁሉ አድርጉብኝ። 15ነገር ግን የሰማችሁትን ይህን ሁሉ ቃል በጆሯችሁ እንድናገር እግዚአብሔር በርግጥ ስለ ላከኝ ብትገድሉኝ፣ የንጹሕ ሰው ደም በማፍሰሳችሁ እናንተ ራሳችሁንና ይህችን ከተማ፣ በውስጧም የሚኖረውን በደለኛ እንዳታደርጉ ተጠንቀቁ።”

16ባለሥልጣኖቹና ሕዝቡም ሁሉ ለካህናትና ለነቢያት፣ “ይህ ሰው በአምላካችን በእግዚአብሔር ስም ተናግሯልና ሊገደል አይገባውም” አሉ።

17ከአገሩ ሽማግሌዎችም አንዳንዶቹ ተነሥተው ለተሰበሰበው ሕዝብ ሁሉ እንዲህ አሉ፤ 18“ሞሬታዊው ሚክያስ በይሁዳ ንጉሥ በሕዝቅያስ ዘመን፣ ለይሁዳም ሕዝብ ሁሉ እንዲህ ሲል ትንቢት ተናግሮ ነበር፤ ‘የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ጽዮን እንደ ዕርሻ ትታረሳለች፤

ኢየሩሳሌም የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች፤

የቤተ መቅደሱም ተራራ፣ ዳዋ የወረሰው ኰረብታ ይሆናል።’26፥18 ሚክ 3፥12

19“ታዲያ፣ የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስም ሆነ የይሁዳ ሕዝብ ሁሉ ገደሉትን? ሕዝቅያስ እግዚአብሔርን ፈርቶ ምሕረት አልለመነምን? እግዚአብሔርስ በእነርሱ ላይ ለማምጣት ያሰበውን ቅጣት አልተወምን? በራሳችን ላይ እኮ ታላቅ ጥፋት እያመጣን ነው።”

20ደግሞም የቂርያትይዓሪም ሰው፣ የሸማያ ልጅ ኦርዮ፣ በእግዚአብሔር ስም ትንቢት የተናገረ ሌላው ሰው ነበር፤ እርሱም እንደ ኤርምያስ በዚህች ከተማና በዚህ ምድር ላይ ትንቢት ተናግሮ ነበር። 21ንጉሥ ኢዮአቄም፣ የጦር አለቆቹና ባለሥልጣኖቹ ሁሉ ይህን በሰሙ ጊዜ፣ ንጉሡ ሊገድለው ፈለገ፤ ኦርዮም ይህን ሰምቶ በፍርሀት ወደ ግብፅ ሸሸ። 22ይሁን እንጂ ንጉሥ ኢዮአቄም የዓክቦርን ልጅ ኤልናታንንና ከእርሱም ጋር ሌሎችን ሰዎች ወደ ግብፅ ላካቸው፤ 23እነርሱም ኦርዮን ከግብፅ አምጥተው፣ ወደ ንጉሥ ኢዮአቄም ወሰዱት፤ እርሱም በሰይፍ ገደለው፤ ሬሳውንም ተራ ሰዎች በሚቀበሩበት ስፍራ ጣለው።

24ነገር ግን የሳፋን ልጅ አኪቃም ከኤርምያስ ጐን ስለ ቆመ፣ ኤርምያስ ይገደል ዘንድ ለሕዝቡ ዐልፎ አልተሰጠም።

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 26:1-24

เยเรมีย์ถูกขู่ฆ่า

1มีพระดำรัสจากองค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์ในต้นรัชกาลเยโฮยาคิมโอรสของกษัตริย์โยสิยาห์แห่งยูดาห์ 2องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า จงยืนอยู่ที่ลานพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้าและประกาศแก่ชาวเมืองต่างๆ ของยูดาห์ซึ่งมานมัสการที่พระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า จงแจ้งทุกสิ่งตามที่เราสั่ง อย่าเว้นแม้แต่คำเดียว 3บางทีพวกเขาอาจจะรับฟังและหันจากทางชั่วของตน แล้วเราจะอดใจไว้ไม่นำภัยพิบัติมายังเขาตามที่เราคิดเพราะความชั่วที่พวกเขาได้ทำ 4จงบอกพวกเขาว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า หากเจ้าไม่ฟังคำของเราและปฏิบัติตามบทบัญญัติของเราซึ่งเราตั้งไว้ต่อหน้าเจ้า 5และหากเจ้าไม่ยอมฟังคำผู้รับใช้ของเราคือเหล่าผู้เผยพระวจนะซึ่งเราได้ส่งมาเตือนเจ้าครั้งแล้วครั้งเล่า (แม้ว่าเจ้าไม่ฟัง) 6เมื่อนั้นเราจะทำลายพระนิเวศแห่งนี้เหมือนที่เราได้ทำลายพลับพลาแห่งชิโลห์และเราจะทำให้เยรูซาเล็มเป็นที่สาปแช่งในหมู่ประชาชาติทั่วโลก’ ”

7บรรดาปุโรหิต ผู้เผยพระวจนะและประชาชนทั้งปวงได้ยินเยเรมีย์กล่าวถ้อยคำเหล่านี้ในพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้า 8ทันทีที่เยเรมีย์ได้กล่าวทุกสิ่งแก่ประชาชนเสร็จสิ้นตามที่ องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสสั่งไว้ บรรดาปุโรหิต ผู้เผยพระวจนะ และประชาชนทั้งปวงก็กรูเข้าไปจับเขาและร้องว่า “แกต้องตาย! 9ทำไมมาพยากรณ์ในพระนามพระยาห์เวห์ว่าพระนิเวศแห่งนี้จะเป็นเหมือนชิโลห์และกรุงนี้จะต้องถูกทิ้งร้าง?” แล้วประชาชนทั้งหมดก็กรูเข้าล้อมตัวเยเรมีย์ในพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้า

10เมื่อบรรดาขุนนางของยูดาห์ได้ยินเรื่องนี้ ก็ออกจากพระราชวังมาที่พระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า มานั่งประจำที่อยู่ที่ประตูใหม่ของพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 11แล้วบรรดาปุโรหิตและผู้เผยพระวจนะก็แจ้งเหล่าขุนนางและประชาชนทั้งปวงว่า “ชายผู้นี้สมควรรับโทษถึงตายเพราะเขาพยากรณ์ให้ร้ายกรุงนี้ ท่านก็ได้ยินกับหูของท่านเองแล้ว!”

12เยเรมีย์จึงกล่าวแก่บรรดาขุนนางและประชาชนทั้งปวงว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงใช้ข้าพเจ้ามาพยากรณ์แก่พระนิเวศนี้และกรุงนี้ตามที่ท่านได้ยินมาทั้งหมด 13บัดนี้พวกท่านจงแก้ไขแนวทางและความประพฤติของท่าน จงเชื่อฟังพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงอดพระทัยไว้ ไม่นำภัยพิบัติซึ่งได้ทรงประกาศไว้มาเหนือพวกท่าน 14ส่วนข้าพเจ้าอยู่ในกำมือของท่านแล้ว เชิญทำแก่ข้าพเจ้าตามที่ท่านเห็นดีเห็นชอบเถิด 15แต่ที่แน่ๆ คือหากพวกท่านฆ่าข้าพเจ้า ก็ได้ฆ่าผู้บริสุทธิ์คนหนึ่งและความผิดนี้จะตกอยู่แก่ท่าน แก่กรุงนี้และแก่ชาวกรุงนี้ เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงใช้ข้าพเจ้ามาจริงๆ ให้กล่าวถ้อยคำทั้งปวงตามที่พวกท่านได้ยินแล้ว”

16บรรดาขุนนางและประชาชนทั้งปวงจึงกล่าวแก่เหล่าปุโรหิตและผู้เผยพระวจนะว่า “ชายผู้นี้ไม่สมควรได้รับโทษประหาร! เพราะเขาพูดกับเราในพระนามพระยาห์เวห์พระเจ้าของเรา”

17มีบางคนในหมู่ผู้อาวุโสของแผ่นดินนั้นลุกขึ้นก้าวออกมากล่าวแก่ที่ประชุมประชาชนทั้งหมดว่า 18“ในรัชกาลกษัตริย์เฮเซคียาห์แห่งยูดาห์ มีคาห์แห่งโมเรเชทได้แจ้งคำพยากรณ์แก่ประชากรยูดาห์ว่า ‘พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสว่า

“ ‘ศิโยนจะถูกไถเหมือนนา

และเยรูซาเล็มจะกลายเป็นซากปรักหักพัง

ภูเขาที่ตั้งของพระวิหารจะกลายเป็นป่ารก’26:18 มคา.3:12

19กษัตริย์เฮเซคียาห์แห่งยูดาห์หรือใครอื่นในยูดาห์ได้ฆ่ามีคาห์หรือ? เฮเซคียาห์ไม่ได้ยำเกรงองค์พระผู้เป็นเจ้าและทูลอ้อนวอนพระองค์หรอกหรือ? แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าก็อดพระทัยไว้ ไม่นำภัยพิบัติที่ทรงประกาศไว้มาเหนือพวกเขาไม่ใช่หรือ? ส่วนเรากำลังหาเรื่องนำหายนะร้ายแรงมาสู่ตนเอง!”

20(ครั้งนั้นอุรียาห์บุตรเชไมอาห์จากคีริยาทเยอาริมซึ่งเป็นอีกผู้หนึ่งที่เผยพระวจนะในพระนามของพระยาห์เวห์ก็ได้กล่าวพยากรณ์เกี่ยวกับกรุงนี้และดินแดนนี้เช่นเดียวกับเยเรมีย์ 21เมื่อกษัตริย์เยโฮยาคิม บรรดานายทหาร และข้าราชการได้ยินสิ่งที่อุรียาห์พูด กษัตริย์ก็ส่งคนไปฆ่าเขา แต่อุรียาห์ได้ยินข่าวนี้จึงหนีไปที่อียิปต์ด้วยความกลัว 22แต่กษัตริย์เยโฮยาคิมทรงใช้เอลนาธันบุตรของอัคโบร์ พร้อมทั้งคนอื่นไปที่อียิปต์เพื่อจับกุมอุรียาห์ 23อุรียาห์ถูกคุมตัวจากอียิปต์มาเข้าเฝ้ากษัตริย์เยโฮยาคิม พระองค์ทรงประหารเขาด้วยดาบ และให้โยนศพไว้ในที่ฝังศพของสามัญชน)

24ยิ่งกว่านั้นเยเรมีย์ได้รับความช่วยเหลือจากอาหิคัมบุตรชาฟาน จึงไม่ถูกมอบตัวให้ประชาชนฆ่า