ኤርምያስ 24 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 24:1-10

መልካሙና መጥፎው በለስ

1የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር፣ የኢዮአቄምን ልጅ የይሁዳን ንጉሥ ኢኮንያንንና24፥1 በዕብራይስጡ ኢኮንያን፣ የኢዮአኪን አቻ ስም ነው። ባለሥልጣኖቹን እንዲሁም የይሁዳን ዐናጺዎችና ብረት ቀጥቃጮች ከኢየሩሳሌም ወደ ባቢሎን ማርኮ ከወሰዳቸው በኋላ፣ እግዚአብሔር ሁለት ቅርጫት በለስ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ፊት ለፊት ተቀምጦ አሳየኝ። 2አንዱ ቅርጫት፣ ቶሎ የደረሰ ፍሬ የሚመስል እጅግ መልካም በለስ ነበረበት፣ በሌላው ቅርጫት ግን ከመበላሸቱ የተነሣ ሊበላ የማይቻል እጅግ መጥፎ በለስ ነበረበት።

3እግዚአብሔርም፣ “ኤርምያስ ሆይ፤ የምታየው ምንድን ነው?” አለኝ።

እኔም፣ “በለስን አያለሁ፤ ጥሩ የሆነው እጅግ መልካም ነው፤ የተበላሸው ግን እጅግ መጥፎ በመሆኑ ሊበላ የማይችል ነው” አልሁ።

4እንደ ገናም የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፤ 5“የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እንደዚህ እንደ መልካሙ በለስ፣ ከዚህ ስፍራ ወደ ባቢሎናውያን24፥5 ወይም ከለዳውያን ምድር የሰደድሁትን የይሁዳ ምርኮ በመልካም አስበዋለሁ። 6ዐይኔን ለበጎነት በእነርሱ ላይ አደርጋለሁ፤ ወደዚህችም ምድር እመልሳቸዋለሁ፤ እሠራቸዋለሁ እንጂ አላፈርሳቸውም፤ እተክላቸዋለሁ እንጂ አልነቅላቸውም። 7እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ የሚያውቅ ልብ እሰጣቸዋለሁ፤ በፍጹም ልባቸውም ወደ እኔ ስለሚመለሱ፣ እነርሱ ሕዝብ ይሆኑኛል፤ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ።

8“ ‘ነገር ግን ከመበላሸቱ የተነሣ ሊበላ እንደ ማይቻለው እንደ መጥፎ በለስ’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘የይሁዳን ንጉሥ ሴዴቅያስንና ባለሥልጣኖቹን እንዲሁም በኢየሩሳሌም የቀሩትንም ሆነ በግብፅ የሚኖሩትን፣ እንዲሁ አደርግባቸዋለሁ። 9በምድር መንግሥታት ሁሉ ፊት የሚያስጸይፉና የሚሰደቡ ይሆናሉ፤ በምበትናቸውም ስፍራ ሁሉ ለማላገጫና ለመተረቻ፣ ለመሣለቂያና ለርግማን አደርጋቸዋለሁ። 10ለእነርሱና ለአባቶቻቸው ከሰጠኋቸው ምድር እስኪጠፉ ድረስ ሰይፍ፣ ራብና መቅሠፍት እሰድባቸዋለሁ።’ ”

Persian Contemporary Bible

ارميا 24:1-10

دو سبد انجير

1پس از آنكه نبوكدنصر، پادشاه بابل، يهوياكين (پسر يهوياقيم) پادشاه يهودا را همراه با بزرگان يهودا و صنعتگران و آهنگران به بابل به اسارت برد، خداوند در رؤيا، دو سبد انجير به من نشان داد كه در مقابل خانهٔ خداوند در اورشليم قرار داشت. 2در يک سبد انجيرهای رسيده و تازه بود و در سبد ديگر انجيرهای بد و گنديده‌ای كه نمی‌شد خورد. 3خداوند به من فرمود: «ارميا، چه می‌بينی؟»

جواب دادم: «انجير! انجيرهای خوب خيلی خوبند؛ ولی انجيرهای بد آنقدر بدند كه نمی‌شود خورد.»

4‏-5آنگاه خداوند فرمود: «انجيرهای خوب نمونهٔ اسيرانی است كه از راه لطف به بابل فرستاده‌ام. 6من بر آنان نظر لطف انداخته، مراقب خواهم بود كه در آنجا با ايشان خوش‌رفتاری شود و ايشان را به اين سرزمين باز خواهم گرداند؛ من نخواهم گذاشت ايشان ريشه‌كن و نابود شوند بلكه ايشان را حمايت كرده، استوار خواهم ساخت. 7به ايشان دلی خواهم داد كه مشتاق شناخت من باشد؛ آنها قوم من خواهند شد و من خدای ايشان، چون با تمام دل نزد من باز خواهند گشت.

8«ولی انجيرهای بد، نمونهٔ صدقيا، پادشاه يهودا، اطرافيان او و بقيهٔ مردم اورشليم است كه در اين سرزمين باقی مانده‌اند و يا در مصر ساكنند. من با ايشان همان كاری را خواهم كرد كه با انجيرهای گنديدهٔ بی‌مصرف می‌كنند. 9ايشان را مورد نفرت تمام مردم دنيا قرار خواهم داد و در هر جايی كه ايشان را آواره كنم، مورد تمسخر، سرزنش و نفرين واقع خواهند شد. 10همه را گرفتار جنگ و قحطی و بيماری خواهم نمود تا از سرزمين اسرائيل كه آن را به ايشان و به پدرانشان دادم، محو و نابود شوند.»