ኤርምያስ 22 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 22:1-30

በክፉዎች ነገሥታት ላይ የተሰጠ ፍርድ

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ወደ ይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት ውረድ፤ ይህንም መልእክት በዚያ እንዲህ ብለህ ተናገር፤ 2‘በዳዊት ዙፋን የተቀመጥህ፣ የይሁዳ ንጉሥ ሆይ፤ አንተና መኳንንትህ፣ በእነዚህም በሮች የሚገባ ሕዝብህ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ። 3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ፍትሕንና ጽድቅን አድርጉ፤ የተበዘበዘውን ከጨቋኙ እጅ አድኑት፤ መጻተኛውን፣ ወላጅ የሌለውንና መበለቲቱን አትበድሉ፤ አትግፏቸውም፤ በዚህም ስፍራ ንጹሕ ደም አታፍስሱ። 4እነዚህን ትእዛዞች በሚገባ ብትጠብቁ፣ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጡ ነገሥታት፣ ከመኳንንታቸውና ከሕዝባቸው ጋር በሠረገሎችና በፈረሶች ተቀምጠው በዚህ ቤተ መንግሥት በሮች ይገባሉ፤ ይወጣሉም። 5ነገር ግን እነዚህን ትእዛዞች ባትጠብቁ፣ ይህ ቤተ መንግሥት እንዲወድም በራሴ ምያለሁ፤” ይላል እግዚአብሔር።’ ”

6ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት እንዲህ ይላል፤

“አንተ ለእኔ እንደ ገለዓድ፣

እንደ ሊባኖስ ተራራ ጫፍ ውብ ብትሆንም፣

በርግጥ እንደ ምድረ በዳ፣

ሰው እንደማይኖርባቸው ከተሞች አደርግሃለሁ።

7በነፍስ ወከፍ መሣሪያ የሚይዙትን፣

አጥፊዎችን በአንተ ላይ አዘጋጃለሁ።

ምርጥ የዝግባ ዛፎችን ይቈርጣሉ፤

ወደ እሳትም ይጥሏቸዋል።

8“ከተለያየ አገር የመጡ ሕዝቦች በዚህች ከተማ በኩል ሲያልፉ፣ ‘እግዚአብሔር በዚህች ታላቅ ከተማ ላይ ለምን እንዲህ አደረገ?’ እያሉ እርስ በርስ ይነጋገራሉ፤ 9ከዚያም፣ ‘የአምላካቸውን የእግዚአብሔርን ኪዳን ትተው ሌሎችን አማልክት ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው’ ይላሉ።”

10ከእንግዲህ ስለማይመለስ፣

የተወለደባትንም ምድር ዳግመኛ ስለማያይ፣

ለተማረከው ንጉሥ አምርራችሁ አልቅሱ እንጂ፣

ቀድሞ ለሞተው አታልቅሱ፤ አትዘኑም።

11በአባቱ ምትክ በይሁዳ ላይ ስለ ነገሠው፣ ከዚህ ስፍራ በምርኮ ስለ ተወሰደው፣ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ሰሎ22፥11 ኢዮአካዝ ተብሎም ይጠራል። እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ “ከእንግዲህ አይመለስም፤ 12ተማርኮ በሄደበት አገር ይሞታል እንጂ ይህችን ምድር ዳግመኛ አያይም።”

13“ቤተ መንግሥቱን በግፍ ለሚሠራ፣

ሰገነቱንም ፍትሕ በማዛባት ለሚገነባ፣

ወገኑን በነጻ ለሚያሠራ፣

የድካሙንም ዋጋ ለማይከፍለው፣

14‘ባለ ትልልቅ ሰገነት፣

ሰፊ ቤተ መንግሥት ለራሴ እሠራለሁ’ ለሚል ወዮለት!

ሰፋፊ መስኮቶችን ያበጅለታል፤

በዝግባ ዕንጨት ያስጌጠዋል፤

ቀይ ቀለምም ይቀባዋል።

15“በዝግባ ዕንጨት ብዛት፣

የነገሥህ ይመስልሃልን?

አባትህስ ፍትሕንና ጽድቅን በማድረጉ፣

የሚበላውና የሚጠጣው ጐድሎት ነበርን?

እነሆ፤ ሁሉም መልካም ሆነለት።

16የድኾችንና የችግረኞችን ፍትሕ አላጓደለም፤

ስለዚህም ሁሉ መልካም ሆነለት።

እኔን ማወቅ ማለት ይህ አይደለምን?”

ይላል እግዚአብሔር

17“የአንተ ዐይንና ልብ ያረፉት ግን፣

አጭበርብሮ ጥቅምን በማግኘት፣

የንጹሑን ደም በማፍሰስ፣

ጭቈናንና ግፍን በመሥራት ላይ ብቻ ነው።”

18ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ኢዮአቄም እንዲህ ይላል፤

“ ‘ዋይ ወንድሜ! ዋይ፣ እኅቴን!’

ብለው አያለቅሱለትም።

‘ዋይ፣ ጌታዬን! ዋይ፣ ለግርማዊነቱ!’

ብለውም አያለቅሱለትም።

19አህያ እንደሚቀበር ይቀበራል፤

ከኢየሩሳሌም በሮች ውጪ፤

ተጐትቶ ይጣላል።

20“ሊባኖስ ላይ ወጥተሽ ጩኺ፤

ድምፅሽን በባሳን አሰሚ፤

በዓባሪም ሆነሽ ጩኺ፤

ወዳጆችሽ ሁሉ ወድመዋልና።

21ተመችቶሽ በነበረ ጊዜ አስጠነቀቅሁሽ፤

አንቺ ግን፣ ‘አልሰማም’ አልሽ፤

ከትንሽነትሽ ጀምሮ መንገድሽ ይኸው ነበር፤

ቃሌንም አልሰማሽም።

22እረኞችሽ ሁሉ በነፋስ ይወሰዳሉ፤

ወዳጆችሽም ተማርከው ይሄዳሉ፤

ከክፋትሽም ሁሉ የተነሣ፣

ታፍሪያለሽ፤ ትዋረጂያለሽም።

23አንቺ፣ ‘በሊባኖስ’22፥23 ሊባኖስ የተባለው በኢየሩሳሌም ያለው ቤተ መንግሥት ነው (1ነገ 7፥23 ይመ)። ውስጥ የምትኖሪ፣

መኖሪያሽን በዝግባ ዛፍ የሠራሽ ሆይ፤

ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

መከራ በላይሽ ሲመጣ ጩኸትሽ እንዴት ይሆን!

24“በሕያውነቴ እምላለሁ”፤ ይላል እግዚአብሔር “የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም ልጅ ኢኮንያን22፥24 በዕብራይስጥ ኮንያ ሲሆን የኢዮአኪን አቻ ስም ቃል ነው፤ 28 ይመ። የቀኝ እጄ የቀለበት ማኅተም ብትሆን እንኳ ኖሮ፣ አውልቄ እጥልሃለሁ፤ 25ሕይወትህን ለሚሿት፣ ለምትፈራቸው ለባቢሎናውያንና22፥25 ወይም ከለዳውያን ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር አሳልፌ እሰጥሃለሁ። 26አንተንና የወለደችህን እናትህን ወዳልተወለዳችሁበት ወደ ሌላ አገር ወርውሬ እጥላችኋለሁ፤ በዚያም ትሞታላችሁ። 27ልትመለሱባት ወደ ምትናፍቋት ምድር ከቶ አትመለሱም።”

28ይህ ኢኮንያን የተባለ ሰው፣ የተናቀና የተሰበረ ገንቦ፣

ማንም የማይፈልገው ዕቃ ነውን?

እርሱና ልጆቹ ለምን ወደ ውጪ ተጣሉ?

ወደማያውቁትስ ምድር ለምን ተወረወሩ?

29ምድር ሆይ፤ አንቺ ምድር፣ አንቺ ምድር፤

የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ!

30እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“አንድ እንኳ የረባ ዘር የማይወጣለት፣

አንድ እንኳ በዳዊት ዙፋን የሚቀመጥ፣

ወይም በይሁዳ የሚገዛ የማይኖረው ነውና፤

በሕይወት ዘመኑ የማይከናወንለት፣

መካን ሰው ብላችሁ መዝግቡት።”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 22:1-30

การพิพากษาเหล่ากษัตริย์ผู้ชั่วร้าย

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “จงไปที่วังของกษัตริย์ยูดาห์และประกาศว่า 2‘จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าเถิด กษัตริย์ยูดาห์ผู้นั่งบนบัลลังก์ของดาวิด ตลอดจนข้าราชการและประชาชนของเจ้าที่ผ่านเข้าออกประตูเหล่านี้ 3องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า จงทำสิ่งที่ถูกต้องและเที่ยงธรรม ช่วยเหลือผู้ที่ถูกปล้นชิงให้พ้นจากเงื้อมมือของผู้ที่ข่มเหงรังแก อย่าทารุณหรือรังแกคนต่างด้าว ลูกกำพร้าพ่อ หรือหญิงม่าย และอย่าทำให้ผู้บริสุทธิ์ต้องหลั่งเลือดที่นี่ 4เพราะหากเจ้าใส่ใจปฏิบัติตามคำบัญชาเหล่านี้ กษัตริย์ที่นั่งบนบัลลังก์ของดาวิดจะได้นั่งรถม้าศึกหรือขี่ม้าผ่านเข้าออกประตูวังนี้ พร้อมด้วยข้าราชการและราษฎรทั้งหลาย 5แต่หากเจ้าทั้งปวงไม่ยอมเชื่อฟังคำสั่งนี้ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า เราขอสาบานในนามของเราเองว่า พระราชวังแห่งนี้จะกลายเป็นซากปรักหักพัง’ ”

6เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสเกี่ยวกับวังของกษัตริย์ยูดาห์ว่า

“แม้เจ้าจะเป็นเหมือนกิเลอาดสำหรับเรา

เหมือนยอดเขาแห่งเลบานอน

เราก็จะทำให้เจ้าเหมือนถิ่นกันดาร

เหมือนเมืองซึ่งไม่มีใครอยู่อาศัย

7เราจะส่งผู้ทำลายมาเล่นงานเจ้า

แต่ละคนถืออาวุธของตนมา

เขาจะรื้อคานสนซีดาร์ชั้นดีของเจ้าออก

และโยนเข้ากองไฟ

8“ผู้คนจากหลายชาติจะเดินผ่านซากปรักหักพังของกรุงนี้และถามกันว่า ‘ทำไมหนอองค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงทำกับกรุงใหญ่ถึงเพียงนี้’ 9คำตอบที่จะได้ก็คือ ‘เพราะเหล่าประชากรละทิ้งพันธสัญญาของพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกเขาไปปรนนิบัตินมัสการพระอื่นๆ’ ”

10อย่าร่ำไห้ให้แก่กษัตริย์ที่ตายหรือคร่ำครวญถึงความสูญเสียของเขาเลย

แต่จงร้องไห้อย่างขมขื่นให้แก่บรรดาคนที่ตกเป็นเชลย

เพราะเขาจะไม่ได้กลับมา

เห็นบ้านเกิดเมืองนอนอีกแล้ว

11เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสถึงชัลลูม22:11 มีอีกชื่อหนึ่งว่าเยโฮอาหาสบุตรของโยสิยาห์ ผู้ครองราชย์ในยูดาห์ต่อจากโยสิยาห์ราชบิดาแต่ต้องไปจากสถานที่แห่งนี้ว่า “เขาจะไม่ได้กลับมาอีก 12เขาจะตายในที่ซึ่งถูกจับไปเป็นเชลย เขาจะไม่ได้กลับมาเห็นดินแดนนี้อีก”

13“วิบัติแก่เขา22:13 คือ กษัตริย์เยโฮยาคิมซึ่งสร้างวังของตนจากความอธรรม

และต่อเติมตำหนักชั้นบนจากความอยุติธรรม

เกณฑ์ให้พี่น้องร่วมชาติทำงานโดยไม่มีค่าตอบแทน

ใช้แรงงานพวกเขาโดยไม่มีค่าจ้าง

14เขาพูดว่า ‘เราจะสร้างวังของเราให้ใหญ่โต

มีตำหนักชั้นบนซึ่งกว้างใหญ่’

แล้วเขาก็เจาะหน้าต่างบานใหญ่

กรุด้วยไม้สนซีดาร์

ประดับประดาด้วยสีแดง

15“เจ้าได้เป็นกษัตริย์

เพราะเจ้าสะสมไม้สนซีดาร์มากๆ หรือ?

บิดาของเจ้ากินดีอยู่ดีไม่ใช่หรือ?

เขาได้ทำสิ่งที่ถูกต้องและยุติธรรม

เพราะเหตุนี้ เขาจึงอยู่เย็นเป็นสุข

16เขาได้ตัดสินคดีของคนยากไร้และคนขัดสนอย่างยุติธรรม

เขาจึงอยู่เย็นเป็นสุข

การรู้จักเราหมายความอย่างนั้นไม่ใช่หรือ?”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

17“แต่ส่วนเจ้า ทั้งตาทั้งใจ

มุ่งอยู่ที่ผลกำไรทุจริต

อยู่ที่การทำให้ผู้บริสุทธิ์ต้องหลั่งเลือด

การกดขี่ข่มเหงและการรีดนาทาเร้น”

18ฉะนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสเกี่ยวกับเยโฮยาคิมโอรสกษัตริย์โยสิยาห์แห่งยูดาห์ว่า

“ผู้คนจะไม่ร่ำไห้อาลัยให้เขาว่า

‘อนิจจา พี่น้องของเรา!’

ผู้คนจะไม่ร่ำไห้อาลัยให้เขาว่า

‘อนิจจา นายเหนือหัว! อนิจจา ฝ่าพระบาท!’

19ศพของเขาจะถูกจัดการเหมือนลาตัวหนึ่ง

คือถูกลากออกไปโยนทิ้ง

นอกประตูเมืองเยรูซาเล็ม”

20“จงขึ้นไปบนภูเขาเลบานอนและป่าวร้อง

จงเปล่งเสียงในบาชาน

จงร้องออกมาจากอาบาริม

เพราะพันธมิตรทั้งปวงของเจ้าถูกบดขยี้หมดแล้ว

21เราได้เตือนเจ้าตั้งแต่ครั้งที่เจ้ายังรู้สึกมั่นคงปลอดภัย

แต่เจ้าตอบว่า ‘ข้าพระองค์จะไม่ฟัง!’

เจ้าเป็นแบบนี้มาตั้งแต่เด็ก

คือไม่ยอมเชื่อฟังเรา

22ลมจะพัดคนเลี้ยงแกะทุกคนของเจ้ากระจัดกระจายไป

และพันธมิตรของเจ้าจะตกเป็นเชลย

แล้วเจ้าจะอับอายขายหน้า

เพราะความชั่วช้าทั้งปวงของเจ้า

23เจ้าผู้อาศัยใน ‘ตำหนักเลบานอน22:23 คือ พระราชวังในเยรูซาเล็ม (ดู1พกษ.7:2)

ผู้พักสบายในเรือนไม้สนซีดาร์

เจ้าจะร้องครวญครางสักเท่าใด เมื่อความเจ็บปวดมาถึงเจ้า

เหมือนความเจ็บปวดของหญิงที่คลอดลูก!”

24องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “เรามีชีวิตอยู่แน่ฉันใด ถึงแม้ว่าเจ้าเยโฮยาคีน22:24 ภาษาฮีบรูว่าโคนิยาห์เป็นอีกรูปหนึ่งของเยโฮยาคีนเช่นเดียวกับข้อ 28บุตรกษัตริย์เยโฮยาคิมแห่งยูดาห์เป็นแหวนตราประจำมือขวาของเรา เราก็ยังจะถอดเจ้าออกฉันนั้น 25เราจะมอบเจ้าให้แก่บรรดาผู้มุ่งเอาชีวิตของเจ้า ผู้ที่เจ้าหวาดกลัว คือกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนและชาวบาบิโลน22:25 หรือชาวเคลเดียทั้งหลาย 26เราจะเหวี่ยงเจ้าและแม่ของเจ้าออกจากบ้านเกิดเมืองนอน และเจ้าจะตายในต่างแดน 27เจ้าจะไม่ได้กลับมายังดินแดนซึ่งเจ้าปรารถนาจะกลับมาอีก”

28เยโฮยาคีนผู้นี้เป็นหม้อแตกที่ถูกเหยียดหยาม

เป็นสิ่งที่ไม่มีใครต้องการหรือ?

เหตุใดเขากับลูกๆ จะถูกเหวี่ยงออกไป

ยังดินแดนที่พวกเขาไม่รู้จัก?

29แผ่นดินเอ๋ย แผ่นดินเอ๋ย แผ่นดินเอ๋ย

จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าเถิด!

30องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“จงบันทึกถึงชายผู้นี้

ราวกับว่าเขาไร้ทายาท

เป็นผู้ที่จะไม่เจริญเลยตลอดชีวิต

เพราะไม่มีลูกคนไหนของเขาเจริญรุ่งเรือง

หรือจะได้นั่งบนบัลลังก์ของดาวิด

หรือปกครองในยูดาห์อีกต่อไป”