ኤርምያስ 2 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 2:1-37

የእስራኤል ሕዝብ አምላኩን መተው

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“ሂድና ጮኸህ ይህን ለኢየሩሳሌም ጆሮ አሰማ፤

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘በወጣትነትሽ ጊዜ የነበረሽን ታማኝነት፣

በሙሽርነትሽም ወራት እንዴት እንደ ወደድሽኝ፣

በምድረ በዳ ዘር በማይዘራበት ምድር፣

እንዴት እንደ ተከተልሽኝ አስታውሳለሁ።

3እስራኤል ለእግዚአብሔር ቅዱስ ነበረች፤

የመከሩም በኵር ነበረች፤

የዋጧት ሁሉ በደለኞች ሆኑ፤

መዓትም ደረሰባቸው’ ”

ይላል እግዚአብሔር

4የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ የእስራኤል ቤት ወገን ሁላችሁ፣

የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ።

5እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“አባቶቻችሁ ከእኔ የራቁት፣

ከንቱ ነገርን የተከተሉት፣

ራሳቸውም ከንቱ የሆኑት፣

ምን ጥፋት አግኝተውብኝ ነው?

6እነርሱም፣ ‘ከግብፅ ምድር ያወጣን፣

በወና ምድረ በዳ፣

በጐድጓዳና በበረሓ መሬት፣

በደረቅና በጨለማ2፥6 ወይም በሞት ጥላ ቦታ፣

ሰው በማያልፍበትና በማይኖርበት ስፍራ

የመራን እግዚአብሔር ወዴት ነው?’ ብለው አልጠየቁም።

7እኔ፣ ፍሬዋንና በረከቷን እንድትበሉ፣

ለም ወደ ሆነ መሬት አመጣኋችሁ፤

እናንተ ግን መጥታችሁ ምድሬን አረከሳችሁ፤

ርስቴንም ጸያፍ አደረጋችሁ።

8እግዚአብሔር ወዴት ነው?’ ብለው

ካህናቱ አልጠየቁም፤

ከሕጉ ጋር የሚውሉት አላወቁኝም፤

መሪዎቹ ዐመፁብኝ፤

ነቢያቱም በበኣል ስም ተነበዩ፤

ከንቱ ነገሮችን ተከተሉ።

9“ስለዚህ እንደ ገና ከእናንተ ጋር እፋረዳለሁ፤

ከልጅ ልጆቻችሁም ጋር እከራከራለሁ።”

ይላል እግዚአብሔር

10“ወደ ኪቲም2፥10 ኪቲም ቆጵሮስና የምዕራባዊ የባሕር ዳርቻ ማለት ነው። ጠረፍ ተሻገሩና እዩ፤

ወደ ቄዳርም2፥10 ቄዳር በሶርያዊ ዓረቢያ ምድረ በዳ የሚገኙ የበዶይን ነገዶች መኖሪያ፤ ልካችሁ በጥንቃቄ መርምሩ፣

እንዲህ ዐይነት ነገር ተደርጎ ያውቅ እንደ ሆነ ተመልከቱ፤

11የእውነት አማልክት ባይሆኑም እንኳ፣

አማልክቱን የለወጠ ሕዝብ አለን?

ሕዝቤ ግን ክብራቸው2፥11 የዕብራውያን የጥንት ጸሐፍት ትውፊት የሆነው የማሶሬቲክ ጽሑፍ ክብሬን ይላል። የሆነውን፣

በከንቱ ነገር ለወጡ።

12ሰማያት ሆይ፤ በዚህ ተገረሙ፤

በታላቅ ድንጋጤም ተንቀጥቀጡ፤”

ይላል እግዚአብሔር

13“ሕዝቤ ሁለት ኀጢአት ፈጽመዋል፤

ሕያው የውሃ ምንጭ የሆንሁትን፣

እኔን ትተዋል፤

ውሃ መያዝ የማይችሉትን ቀዳዳ የውሃ ማጠራቀሚያ ጕድጓዶች፣

ለራሳቸው ቈፍረዋል።

14እስራኤል ባሪያ ነውን? ወይስ የቤት ውልድ ባሪያ?

ታዲያ፣ ስለ ምን ለብዝበዛ ተዳረገ?

15አንበሶች በእርሱ ላይ አገሡ፤

በኀይለኛ ድምፅም ጮኹበት።

ምድሩን ባድማ አድርገውበታል፤

ከተሞቹ ተቃጥለዋል፤ ወናም ሆነዋል።

16ደግሞም የሜምፎስና2፥16 ሜምፎስ በዕብራይስጡ ኖፍ ይላል፤ ወይም ጭንቅላትሽን ፈጠፈጡ ወይም ሰነጠቀ የጣፍናስ ሰዎች፣

መኻል ዐናትሽን ላጩሽ።

17በመንገድ የሚመራሽን፣

እግዚአብሔር አምላክሽን በመተውሽ፣

ይህን በራስሽ ላይ አላመጣሽምን?

18ከሺሖር2፥18 የአባይ ወንዝ አንዱ ተነጣይ ጅረት ነው። ወንዝ ውሃ ለመጠጣት፣

አሁንስ ለምን ወደ ግብፅ ወረድሽ?

ከኤፍራጥስ ወንዝስ ውሃ ለመጠጣት፣

ወደ አሦር መውረድ ለምን አስፈለገሽ?

19ክፋትሽ ቅጣት ያስከትልብሻል፤

ክሕደትሽም ተግሣጽ ያመጣብሻል፤

እግዚአብሔር አምላክሽን ስትተዪ፣

እኔንም መፍራት ችላ ስትይ፣

ምን ያህል ክፉና መራራ እንደሚሆንብሽ

አስቢ፤ እስቲ አስተውዪ፤”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

20“ከጥንት ጀምሮ ቀንበርሽን ሰበርሁ፤

እስራትሽን በጣጠስሁ፤

አንቺም፣ ‘አላገለግልህም’ አልሽ፤

ከፍ ባለውም ኰረብታ ሁሉ ሥር፣

በያንዳንዱም ለምለም ዛፍ ሥር፣

ለማመንዘር ተጋደምሽ።

21እኔ፣ እንደ ምርጥ የወይን ተክል፣

ጤናማና አስተማማኝ ዘር አድርጌ ተክዬሽ ነበር፤

ታዲያ ብልሹ የዱር ወይን ተክል ሆነሽ፣

እንዴት ተለወጥሽብኝ?

22በልዩ ቅጠል ብትታጠቢ፣

ብዙ ሳሙና ብትጠቀሚም፣

የበደልሽ ዕድፍ አሁንም በፊቴ ነው፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

23“ ‘አልረከስሁም፣

በኣሊምን አልተከተልሁም’ እንዴት ትያለሽ?

በሸለቆ ውስጥ ምን እንዳደረግሽ

እስቲ አስቢ፣

ምንስ እንደ ፈጸምሽ ተገንዘቢ፤

እንደምትፋንን ፈጣን ግመል ሆነሻል፤

24በምድረ በዳ እንደ ለመደች፣

በፍትወቷ ነፋስን እንደምታነፈንፍ፣ የሜዳ አህያ ነሽ፤

ከመጐምጀቷ ማን ሊገታት ይችላል?

ለሚፈልጓት ሁሉ ያለ ምንም ድካም

በፍትወቷ ወራት በቀላሉ ትገኝላቸዋለች።

25እግርሽ እስኪነቃ አትሩጪ፤

ጕረሮሽም በውሃ ጥም እስኪደርቅ አትቅበዝበዢ።

አንቺ ግን፣ ‘በከንቱ አትድከም፤

ባዕዳን አማልክትን ወድጃለሁ፤

እነርሱን እከተላለሁ’ አልሽ።

26“ሌባ በተያዘ ጊዜ እንደሚያፍር፣

የእስራኤልም ቤት ዐፍሯል፤

እነርሱ፣ ንጉሦቻቸውና ሹሞቻቸው፣

ካህናታቸውና ነቢያታቸው እንዲሁ ያፍራሉ።

27ዛፉን፣ ‘አንተ አባቴ ነህ’

ድንጋዩንም፣ ‘አንተ ወለድኸኝ’ አሉ፤

ፊታቸውን ሳይሆን፣

ጀርባቸውን ሰጥተውኛልና፤

በመከራቸው ጊዜ ግን፣

‘መጥተህ አድነን’ ይላሉ።

28ታዲያ፣ ልታመልካቸው ያበጀሃቸው አማልክት ወዴት ናቸው?

በመከራህ ጊዜ ሊያድኑህ የሚችሉ ከሆነ፣

ይሁዳ ሆይ፤ እስቲ ይምጡና ያድኑህ፤

የከተሞችህን ቍጥር ያህል፣

የአማልክትህም ብዛት እንዲሁ ነውና።

29“ለምን በእኔ ታማርራላችሁ?

ያመፃችሁብኝ እናንተ ሁላችሁ ናችሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

30“ልጆቻችሁን በከንቱ ቀጣኋቸው፤

እነርሱም አልታረሙም።

ሰይፋችሁ እንደ ተራበ አንበሳ

ነቢያታችሁን በልቷል።

31“የዚህ ትውልድ ሰዎች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል አስተውሉ፤

“እኔ ለእስራኤል ሕዝብ ምድረ በዳ፣

ወይስ ድቅድቅ ጨለማ ያለበት ምድር ሆንሁበትን?

ሕዝቤ፣ ‘እንደ ልባችን ልንሆን እንፈልጋለን፤

ተመልሰንም ወደ አንተ አንመጣም’ ለምን ይላል?

32ለመሆኑ ቈንጆ ጌጣጌጧን፣

ሙሽራ የሰርግ ልብሷን ትረሳለችን?

ሕዝቤ ግን፣

እጅግ ብዙ ቀን ረስቶኛል።

33በፍትወት ለማጥመድ እንዴት ሥልጡን ነሽ?

ልክስክስ ክፉ ሴቶች እንኳ ከመንገድሽ ብዙ ክፋት ይማራሉ።

34በስርቆት ያልያዝሻቸው፣

የንጹሓን ድኾች ደም፣

በልብስሽ ላይ ተገኝቷል።

ይህን ሁሉ አድርገሽም፣

35‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤

በርግጥ ቍጣው ከእኔ ርቋል’ ትያለሽ።

እኔ ግን እፈርድብሻለሁ፤

‘ኀጢአት አልሠራሁም’ ብለሻልና።

36መንገድሽን እየለዋወጥሽ፣

ለምን ትሮጫለሽ?

አሦር እንዳዋረደሽ፣

ግብፅም እንዲሁ ያዋርድሻል።

37የታመንሽባቸውን እግዚአብሔር ስላዋረደ፣

በእነርሱም ስለማይከናወንልሽ፣

እጆችሽን በራስሽ ላይ አድርገሽ

ከዚያም ትወጫለሽ።

New International Version – UK

Jeremiah 2:1-37

Israel forsakes God

1The word of the Lord came to me: 2‘Go and proclaim in the hearing of Jerusalem:

‘This is what the Lord says:

‘ “I remember the devotion of your youth,

how as a bride you loved me

and followed me through the wilderness,

through a land not sown.

3Israel was holy to the Lord,

the firstfruits of his harvest;

all who devoured her were held guilty,

and disaster overtook them,” ’

declares the Lord.

4Hear the word of the Lord, you descendants of Jacob,

all you clans of Israel.

5This is what the Lord says:

‘What fault did your ancestors find in me,

that they strayed so far from me?

They followed worthless idols

and became worthless themselves.

6They did not ask, “Where is the Lord,

who brought us up out of Egypt

and led us through the barren wilderness,

through a land of deserts and ravines,

a land of drought and utter darkness,

a land where no-one travels and no-one lives?”

7I brought you into a fertile land

to eat its fruit and rich produce.

But you came and defiled my land

and made my inheritance detestable.

8The priests did not ask,

“Where is the Lord?”

Those who deal with the law did not know me;

the leaders rebelled against me.

The prophets prophesied by Baal,

following worthless idols.

9‘Therefore I bring charges against you again,’

declares the Lord.

‘And I will bring charges against your children’s children.

10Cross over to the coasts of Cyprus and look,

send to Kedar2:10 In the Syro-Arabian desert and observe closely;

see if there has ever been anything like this:

11has a nation ever changed its gods?

(Yet they are not gods at all.)

But my people have exchanged their glorious God

for worthless idols.

12Be appalled at this, you heavens,

and shudder with great horror,’

declares the Lord.

13‘My people have committed two sins:

They have forsaken me,

the spring of living water,

and have dug their own cisterns,

broken cisterns that cannot hold water.

14Is Israel a servant, a slave by birth?

Why then has he become plunder?

15Lions have roared;

they have growled at him.

They have laid waste his land;

his towns are burned and deserted.

16Also, the men of Memphis and Tahpanhes

have cracked your skull.

17Have you not brought this on yourselves

by forsaking the Lord your God

when he led you in the way?

18Now why go to Egypt

to drink water from the Nile2:18 Hebrew Shihor; that is, a branch of the Nile?

And why go to Assyria

to drink water from the Euphrates?

19Your wickedness will punish you;

your backsliding will rebuke you.

Consider then and realise

how evil and bitter it is for you

when you forsake the Lord your God

and have no awe of me,’

declares the Lord, the Lord Almighty.

20‘Long ago you broke off your yoke

and tore off your bonds;

you said, “I will not serve you!”

Indeed, on every high hill

and under every spreading tree

you lay down as a prostitute.

21I had planted you like a choice vine

of sound and reliable stock.

How then did you turn against me

into a corrupt, wild vine?

22Although you wash yourself with soap

and use an abundance of cleansing powder,

the stain of your guilt is still before me,’

declares the Sovereign Lord.

23‘How can you say, “I am not defiled;

I have not run after the Baals”?

See how you behaved in the valley;

consider what you have done.

You are a swift she-camel

running here and there,

24a wild donkey accustomed to the desert,

sniffing the wind in her craving –

in her heat who can restrain her?

Any males that pursue her need not tire themselves;

at mating time they will find her.

25Do not run until your feet are bare

and your throat is dry.

But you said, “It’s no use!

I love foreign gods,

and I must go after them.”

26‘As a thief is disgraced when he is caught,

so the people of Israel are disgraced –

they, their kings and their officials,

their priests and their prophets.

27They say to wood, “You are my father,”

and to stone, “You gave me birth.”

They have turned their backs to me

and not their faces;

yet when they are in trouble, they say,

“Come and save us!”

28Where then are the gods you made for yourselves?

Let them come if they can save you

when you are in trouble!

For you, Judah, have as many gods

as you have towns.

29‘Why do you bring charges against me?

You have all rebelled against me,’

declares the Lord.

30‘In vain I punished your people;

they did not respond to correction.

Your sword has devoured your prophets

like a ravenous lion.

31‘You of this generation, consider the word of the Lord:

‘Have I been a desert to Israel

or a land of great darkness?

Why do my people say, “We are free to roam;

we will come to you no more”?

32Does a young woman forget her jewellery,

a bride her wedding ornaments?

Yet my people have forgotten me,

days without number.

33How skilled you are at pursuing love!

Even the worst of women can learn from your ways.

34On your clothes is found

the lifeblood of the innocent poor,

though you did not catch them breaking in.

Yet in spite of all this

35you say, “I am innocent;

he is not angry with me.”

But I will pass judgment on you

because you say, “I have not sinned.”

36Why do you go about so much,

changing your ways?

You will be disappointed by Egypt

as you were by Assyria.

37You will also leave that place

with your hands on your head,

for the Lord has rejected those you trust;

you will not be helped by them.