ኤርምያስ 2 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 2:1-37

የእስራኤል ሕዝብ አምላኩን መተው

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“ሂድና ጮኸህ ይህን ለኢየሩሳሌም ጆሮ አሰማ፤

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘በወጣትነትሽ ጊዜ የነበረሽን ታማኝነት፣

በሙሽርነትሽም ወራት እንዴት እንደ ወደድሽኝ፣

በምድረ በዳ ዘር በማይዘራበት ምድር፣

እንዴት እንደ ተከተልሽኝ አስታውሳለሁ።

3እስራኤል ለእግዚአብሔር ቅዱስ ነበረች፤

የመከሩም በኵር ነበረች፤

የዋጧት ሁሉ በደለኞች ሆኑ፤

መዓትም ደረሰባቸው’ ”

ይላል እግዚአብሔር

4የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ የእስራኤል ቤት ወገን ሁላችሁ፣

የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ።

5እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“አባቶቻችሁ ከእኔ የራቁት፣

ከንቱ ነገርን የተከተሉት፣

ራሳቸውም ከንቱ የሆኑት፣

ምን ጥፋት አግኝተውብኝ ነው?

6እነርሱም፣ ‘ከግብፅ ምድር ያወጣን፣

በወና ምድረ በዳ፣

በጐድጓዳና በበረሓ መሬት፣

በደረቅና በጨለማ2፥6 ወይም በሞት ጥላ ቦታ፣

ሰው በማያልፍበትና በማይኖርበት ስፍራ

የመራን እግዚአብሔር ወዴት ነው?’ ብለው አልጠየቁም።

7እኔ፣ ፍሬዋንና በረከቷን እንድትበሉ፣

ለም ወደ ሆነ መሬት አመጣኋችሁ፤

እናንተ ግን መጥታችሁ ምድሬን አረከሳችሁ፤

ርስቴንም ጸያፍ አደረጋችሁ።

8እግዚአብሔር ወዴት ነው?’ ብለው

ካህናቱ አልጠየቁም፤

ከሕጉ ጋር የሚውሉት አላወቁኝም፤

መሪዎቹ ዐመፁብኝ፤

ነቢያቱም በበኣል ስም ተነበዩ፤

ከንቱ ነገሮችን ተከተሉ።

9“ስለዚህ እንደ ገና ከእናንተ ጋር እፋረዳለሁ፤

ከልጅ ልጆቻችሁም ጋር እከራከራለሁ።”

ይላል እግዚአብሔር

10“ወደ ኪቲም2፥10 ኪቲም ቆጵሮስና የምዕራባዊ የባሕር ዳርቻ ማለት ነው። ጠረፍ ተሻገሩና እዩ፤

ወደ ቄዳርም2፥10 ቄዳር በሶርያዊ ዓረቢያ ምድረ በዳ የሚገኙ የበዶይን ነገዶች መኖሪያ፤ ልካችሁ በጥንቃቄ መርምሩ፣

እንዲህ ዐይነት ነገር ተደርጎ ያውቅ እንደ ሆነ ተመልከቱ፤

11የእውነት አማልክት ባይሆኑም እንኳ፣

አማልክቱን የለወጠ ሕዝብ አለን?

ሕዝቤ ግን ክብራቸው2፥11 የዕብራውያን የጥንት ጸሐፍት ትውፊት የሆነው የማሶሬቲክ ጽሑፍ ክብሬን ይላል። የሆነውን፣

በከንቱ ነገር ለወጡ።

12ሰማያት ሆይ፤ በዚህ ተገረሙ፤

በታላቅ ድንጋጤም ተንቀጥቀጡ፤”

ይላል እግዚአብሔር

13“ሕዝቤ ሁለት ኀጢአት ፈጽመዋል፤

ሕያው የውሃ ምንጭ የሆንሁትን፣

እኔን ትተዋል፤

ውሃ መያዝ የማይችሉትን ቀዳዳ የውሃ ማጠራቀሚያ ጕድጓዶች፣

ለራሳቸው ቈፍረዋል።

14እስራኤል ባሪያ ነውን? ወይስ የቤት ውልድ ባሪያ?

ታዲያ፣ ስለ ምን ለብዝበዛ ተዳረገ?

15አንበሶች በእርሱ ላይ አገሡ፤

በኀይለኛ ድምፅም ጮኹበት።

ምድሩን ባድማ አድርገውበታል፤

ከተሞቹ ተቃጥለዋል፤ ወናም ሆነዋል።

16ደግሞም የሜምፎስና2፥16 ሜምፎስ በዕብራይስጡ ኖፍ ይላል፤ ወይም ጭንቅላትሽን ፈጠፈጡ ወይም ሰነጠቀ የጣፍናስ ሰዎች፣

መኻል ዐናትሽን ላጩሽ።

17በመንገድ የሚመራሽን፣

እግዚአብሔር አምላክሽን በመተውሽ፣

ይህን በራስሽ ላይ አላመጣሽምን?

18ከሺሖር2፥18 የአባይ ወንዝ አንዱ ተነጣይ ጅረት ነው። ወንዝ ውሃ ለመጠጣት፣

አሁንስ ለምን ወደ ግብፅ ወረድሽ?

ከኤፍራጥስ ወንዝስ ውሃ ለመጠጣት፣

ወደ አሦር መውረድ ለምን አስፈለገሽ?

19ክፋትሽ ቅጣት ያስከትልብሻል፤

ክሕደትሽም ተግሣጽ ያመጣብሻል፤

እግዚአብሔር አምላክሽን ስትተዪ፣

እኔንም መፍራት ችላ ስትይ፣

ምን ያህል ክፉና መራራ እንደሚሆንብሽ

አስቢ፤ እስቲ አስተውዪ፤”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

20“ከጥንት ጀምሮ ቀንበርሽን ሰበርሁ፤

እስራትሽን በጣጠስሁ፤

አንቺም፣ ‘አላገለግልህም’ አልሽ፤

ከፍ ባለውም ኰረብታ ሁሉ ሥር፣

በያንዳንዱም ለምለም ዛፍ ሥር፣

ለማመንዘር ተጋደምሽ።

21እኔ፣ እንደ ምርጥ የወይን ተክል፣

ጤናማና አስተማማኝ ዘር አድርጌ ተክዬሽ ነበር፤

ታዲያ ብልሹ የዱር ወይን ተክል ሆነሽ፣

እንዴት ተለወጥሽብኝ?

22በልዩ ቅጠል ብትታጠቢ፣

ብዙ ሳሙና ብትጠቀሚም፣

የበደልሽ ዕድፍ አሁንም በፊቴ ነው፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

23“ ‘አልረከስሁም፣

በኣሊምን አልተከተልሁም’ እንዴት ትያለሽ?

በሸለቆ ውስጥ ምን እንዳደረግሽ

እስቲ አስቢ፣

ምንስ እንደ ፈጸምሽ ተገንዘቢ፤

እንደምትፋንን ፈጣን ግመል ሆነሻል፤

24በምድረ በዳ እንደ ለመደች፣

በፍትወቷ ነፋስን እንደምታነፈንፍ፣ የሜዳ አህያ ነሽ፤

ከመጐምጀቷ ማን ሊገታት ይችላል?

ለሚፈልጓት ሁሉ ያለ ምንም ድካም

በፍትወቷ ወራት በቀላሉ ትገኝላቸዋለች።

25እግርሽ እስኪነቃ አትሩጪ፤

ጕረሮሽም በውሃ ጥም እስኪደርቅ አትቅበዝበዢ።

አንቺ ግን፣ ‘በከንቱ አትድከም፤

ባዕዳን አማልክትን ወድጃለሁ፤

እነርሱን እከተላለሁ’ አልሽ።

26“ሌባ በተያዘ ጊዜ እንደሚያፍር፣

የእስራኤልም ቤት ዐፍሯል፤

እነርሱ፣ ንጉሦቻቸውና ሹሞቻቸው፣

ካህናታቸውና ነቢያታቸው እንዲሁ ያፍራሉ።

27ዛፉን፣ ‘አንተ አባቴ ነህ’

ድንጋዩንም፣ ‘አንተ ወለድኸኝ’ አሉ፤

ፊታቸውን ሳይሆን፣

ጀርባቸውን ሰጥተውኛልና፤

በመከራቸው ጊዜ ግን፣

‘መጥተህ አድነን’ ይላሉ።

28ታዲያ፣ ልታመልካቸው ያበጀሃቸው አማልክት ወዴት ናቸው?

በመከራህ ጊዜ ሊያድኑህ የሚችሉ ከሆነ፣

ይሁዳ ሆይ፤ እስቲ ይምጡና ያድኑህ፤

የከተሞችህን ቍጥር ያህል፣

የአማልክትህም ብዛት እንዲሁ ነውና።

29“ለምን በእኔ ታማርራላችሁ?

ያመፃችሁብኝ እናንተ ሁላችሁ ናችሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

30“ልጆቻችሁን በከንቱ ቀጣኋቸው፤

እነርሱም አልታረሙም።

ሰይፋችሁ እንደ ተራበ አንበሳ

ነቢያታችሁን በልቷል።

31“የዚህ ትውልድ ሰዎች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል አስተውሉ፤

“እኔ ለእስራኤል ሕዝብ ምድረ በዳ፣

ወይስ ድቅድቅ ጨለማ ያለበት ምድር ሆንሁበትን?

ሕዝቤ፣ ‘እንደ ልባችን ልንሆን እንፈልጋለን፤

ተመልሰንም ወደ አንተ አንመጣም’ ለምን ይላል?

32ለመሆኑ ቈንጆ ጌጣጌጧን፣

ሙሽራ የሰርግ ልብሷን ትረሳለችን?

ሕዝቤ ግን፣

እጅግ ብዙ ቀን ረስቶኛል።

33በፍትወት ለማጥመድ እንዴት ሥልጡን ነሽ?

ልክስክስ ክፉ ሴቶች እንኳ ከመንገድሽ ብዙ ክፋት ይማራሉ።

34በስርቆት ያልያዝሻቸው፣

የንጹሓን ድኾች ደም፣

በልብስሽ ላይ ተገኝቷል።

ይህን ሁሉ አድርገሽም፣

35‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤

በርግጥ ቍጣው ከእኔ ርቋል’ ትያለሽ።

እኔ ግን እፈርድብሻለሁ፤

‘ኀጢአት አልሠራሁም’ ብለሻልና።

36መንገድሽን እየለዋወጥሽ፣

ለምን ትሮጫለሽ?

አሦር እንዳዋረደሽ፣

ግብፅም እንዲሁ ያዋርድሻል።

37የታመንሽባቸውን እግዚአብሔር ስላዋረደ፣

በእነርሱም ስለማይከናወንልሽ፣

እጆችሽን በራስሽ ላይ አድርገሽ

ከዚያም ትወጫለሽ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

耶利米書 2:1-37

以色列人背棄上帝

1耶和華對我說:

2「你去告訴耶路撒冷人,

『耶和華說,

我記得你們年輕時對我充滿熱情,

愛我如新娘愛新郎,

跟隨我穿越曠野,

穿越不毛之地。

3以色列是耶和華的聖民,

是屬於祂的初熟果子。

吞吃它的必擔當罪責,

大禍臨頭。

這是耶和華說的。』」

4雅各家啊,以色列各宗族啊!你們要聽耶和華的話。 5耶和華說:

「你們的祖先在我身上找到什麼過錯,

以致他們遠離我,

去追隨虛妄的神明,

使自己變得虛妄呢?

6他們從不自問,

『耶和華曾把我們帶出埃及

引導我們走過沙漠縱橫、

深坑滿布、乾旱幽暗、

杳無人跡的曠野,

祂如今在哪裡呢?』

7我帶領你們進入肥沃之地,

享受那裡富饒的物產。

但你們一進來,就玷污我的地,

使我的產業成為可憎之地。

8眾祭司從來不問『耶和華在哪裡?』

執掌律法的不認識我,

首領背叛我,

先知靠巴力說預言,

隨從無用的假神。

9因此,我要指控你們和你們的後代。

這是耶和華說的。

10你們去對岸的基提看看,

派人去基達仔細觀察一下,

看看有沒有這樣的事?

11雖然列國的神明根本不是真神,

卻沒有一國更換自己的神明。

但我的子民卻把自己榮耀的上帝換作了無用的假神。

12諸天啊,要因此而震驚戰慄、

大感淒涼。

這是耶和華說的。

13因為我的子民犯了兩項罪,

他們離棄了我這活水源泉,

為自己挖了不能蓄水的破池子。

14以色列是奴隸嗎?

是生來為奴的嗎?

為什麼她竟成了別人的獵物呢?

15敵人像獅子般向她咆哮吼叫,

使她的土地一片荒涼,

她的城邑一片廢墟,杳無人煙。

16以色列啊,

挪弗人和答比匿人打破了你的頭顱。

17你這不是自食其果嗎?

因為你的上帝耶和華一路引導你的時候,

你卻背棄祂。

18現在,你去埃及尼羅河的水有什麼用呢?

你去亞述幼發拉底河的水有什麼用呢?

19你必因自己的罪惡而受懲罰,

因自己的背叛而受責備。

因此,你要省察且明白,

背棄你的上帝耶和華、

不敬畏我是多麼邪惡、痛苦。

這是萬軍之耶和華說的。

20「很久以前,我折斷你的軛,

解開你的捆索,

你卻拒絕事奉我,

在各高崗上、綠樹下躺臥淫亂。

21你原本是我栽種的上等葡萄樹,

是最好的品種。

你怎麼自甘墮落,

變成了野葡萄?

22縱然你用鹼和許多肥皂清洗,

你在我面前仍然罪跡斑斑。」

這是主耶和華說的。

23「你怎能說,

『我沒有玷污自己,

也沒有隨從巴力』?

看看你在山谷中幹的勾當,

想想你的所作所為。

你是一隻發情的母駱駝,

煩躁不安,跑來跑去。

24你是一隻習慣在曠野生活的母驢,

求偶心切時便呼呼喘氣,

發情時誰也控制不了。

公驢找你不費工夫,

在你發情的時候很容易找到你。

25我說,『不要因追隨假神而跑破鞋子,喉嚨乾渴。』

你卻說,『不行!

我愛外族的神明,一定要跟隨他們。』

26以色列人啊,

你們和你們的君王、官長、

祭司和先知必蒙羞,

如同被擒的盜賊。

27你們認木頭為父,

認石頭為母。

你們不是面向我而是背對我,

危難時卻向我求救。

28你們為自己造的神明在哪裡呢?

危難時讓他們救你們吧!

猶大人啊,你們神明的數目與你們的城邑一樣多!

29「你們為什麼指控我呢?

你們都背叛了我。

這是耶和華說的。

30我責打你們的兒女,卻是徒勞,

因為他們不受管教。

你們殺害你們的先知,

殘暴如獅子。

31這世代的人啊,

要留心聽耶和華的話。

以色列人來說,

難道我是曠野,

是幽暗之地嗎?

為什麼我的子民竟說,

『我們可以四處遊蕩,

不再追隨你』?

32少女會忘記她的首飾嗎?

新娘會忘記她的禮服嗎?

我的子民卻早已把我拋諸腦後。

33「你們真善於求愛啊!

甚至把技巧教給妓女。

34你們的衣服沾滿無辜窮人的血,

他們並沒有進你們的家偷竊。

35你們還說,『我們是無辜的,

耶和華不再向我們發怒。』

看啊,我必審判你們,

因為你們拒不認罪。

36你們為什麼這樣忽東忽西地變來變去呢?

你們投奔埃及必蒙羞辱,

就像從前投奔亞述一樣。

37你們必灰頭土臉地離開埃及

因為耶和華棄絕了你們的靠山,

你們從他們那裡必得不到幫助。」