ኤርምያስ 17 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 17:1-27

1“የይሁዳ ኀጢአት በብረት ብርዕ፣

በሾለ የአልማዝ ጫፍ፣ ተጽፏል፤

በልባቸው ጽላት፣

በመሠዊያቸውም ቀንዶች ላይ ተቀርጿል።

2ልጆቻቸው እንኳ ሳይቀሩ፣

በለመለሙ ዛፎች ሥር፣

ከፍ ባሉ ኰረብቶችም ላይ ያሉትን፣

መሠዊያቸውንና አሼራ የተባለችውን ጣዖት ምስል17፥2 ወይም የአሼራ ዐጸድ ያስባሉ።

3በአገርህ ሁሉ ከተፈጸመው ኀጢአት የተነሣ፣

በምድሪቱ ያለህ ተራራዬ፣17፥3 ወይም በምድሪቱ ያሉ ተራራዎችን

ሀብትህንና ንብረትህን ሁሉ፣

መስገጃ ኰረብቶችህንም ጭምር፣

ለብዝበዛ አደርገዋለሁ።

4በገዛ ጥፋትህ፣

የሰጠሁህን ርስት ታጣለህ፤

በማታውቀውም ምድር፣

ለጠላቶችህ ባሪያ አደርግሃለሁ፤

ለዘላለም የሚነድደውን፣

የቍጣዬን እሳት ጭረሃልና።”

5እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በሰው የሚታመን፣

በሥጋ ለባሽ የሚመካ፣

ልቡንም ከእግዚአብሔር የሚያርቅ የተረገመ ነው።

6በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፤

መልካም ነገር ሲመጣ አያይም፤

ሰው በሌለበት በጨው ምድር፣

በምድረ በዳ በደረቅ ስፍራ ይቀመጣል።

7“ነገር ግን በእግዚአብሔር የሚታመን፣

መታመኛውም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው።

8በውሃ ዳር እንደ ተተከለ፣

ሥሩንም ወደ ወንዝ እንደ ሰደደ ዛፍ ነው፣

ሙቀት ሲመጣ አይፈራም፤

ቅጠሉም ዘወትር እንደ ለመለመ ነው፤

በድርቅ ዘመን አይሠጋም፤

ፍሬ ማፍራቱንም አያቋርጥም።”

9የሰው ልብ ከሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ ነው፤

ፈውስም የለውም፤

ማንስ ሊረዳው ይችላል?

10“እኔ እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ እንደ መንገዱ፣

እንደ ሥራው ፍሬ ለመስጠት፣

ልብን እመረምራለሁ፤

የአእምሮንም ሐሳብ እፈትናለሁ።”

11ሀብትን በግፍ የሚያከማች ሰው፣

ያልፈለፈለችውን ጫጩት እንደምትታቀፍ ቆቅ ነው፤

በዕድሜው አጋማሽ ትቶት ይሄዳል፤

በመጨረሻም ሞኝነቱ ይረጋገጣል።

12የመቅደሳችን ስፍራ፣

ከጥንት ጀምሮ ከፍ ያለ የክብር ዙፋን ነው።

13የእስራኤል ተስፋ እግዚአብሔር ሆይ፤

ጥለውህ የሚሄዱ ሁሉ ያፍራሉ፤

ፊታቸውን ከአንተ የሚመልሱ በምድር ውስጥ ይጻፋሉ፤

የሕይወትን ውሃ ምንጭ፣

እግዚአብሔርን ትተዋልና።

14እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈውሰኝ፤ እፈወሳለሁ፤

አድነኝ እኔም እድናለሁ፤

አንተ ምስጋናዬ ነህና።

15እነርሱ ደጋግመው፣

የእግዚአብሔር ቃል የት አለ?

እስቲ አሁን ይፈጸም!” ይሉኛል።

16እረኛ ሆኜ አንተን ከማገልገል ወደ ኋላ አላልሁም፤

ክፉ ቀን እንዳልተመኘሁ ታውቃለህ፤

ከአንደበቴ የሚወጣውም በፊትህ ግልጽ ነው።

17አስደንጋጭ አትሁንብኝ፤

በመከራ ቀን መሸሸጊያዬ አንተ ነህ።

18አሳዳጆቼ ይፈሩ፤

እኔን ግን ከዕፍረት ጠብቀኝ፤

እነርሱ ይደንግጡ፤

እኔን ግን ከድንጋጤ ሰውረኝ፤

ክፉ ቀን አምጣባቸው፤

በዕጥፍ ድርብ ጥፋት አጥፋቸው።

ሰንበትን ማክበር

19እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፤ “ሄደህ የይሁዳ ነገሥታት በሚገቡበትና በሚወጡበት በሕዝቡ በር በሌሎቹም የኢየሩሳሌም በሮች ሁሉ ቁም፤ 20እንዲህም በላቸው፤ ‘በእነዚህ በሮች የምትገቡ የይሁዳ ነገሥታት ሆይ፤ የይሁዳ ሕዝብና በኢየሩሳሌም የምትኖሩ ሁሉ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ። 21እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በሰንበት ቀን ሸክም ተሸክማችሁ በኢየሩሳሌም በሮች እንዳታስገቡ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። 22አባቶቻችሁን እንዳዘዝኋቸው ሰንበትን አክብሩ እንጂ በሰንበት ቀን ከየቤታችሁ ሸክም ይዛችሁ አትውጡ፤ ምንም ሥራ አትሥሩ።” 23እነርሱ ግን አልሰሙም፤ ልብም አላሉም፤ እንዳይሰሙና እንዳይገሠጹም ዐንገታቸውን አደነደኑ። 24ነገር ግን በጥንቃቄ ብትታዘዙኝ ይላል እግዚአብሔር፤ በሰንበትም ቀን በዚህች ከተማ በሮች ሸክም ይዛችሁ ባትገቡ፣ የሰንበትንም ቀን ምንም ሳትሠሩ ብትቀድሱት፣ 25በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጡ ነገሥታትና መኳንንታቸው በዚህች ከተማ በሮች ይገባሉ፤ በፈረሶችና በሠረገሎች ተቀምጠው በይሁዳ ሰዎችና በኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ታጅበው ይመጣሉ፤ ይህችም ከተማ ለዘላለም የሰው መኖሪያ ትሆናለች። 26ሰዎች ከይሁዳ ከተሞች፣ ከኢየሩሳሌም ዙሪያ፣ ከብንያምም አገር፣ ከቈላውና ከደጋው አገር እንዲሁም ከኔጌቭ የሚቃጠል መሥዋዕትና ሌላ መሥዋዕት፣ የእህል ቍርባን፣ ዕጣንና የምስጋና መሥዋዕት ይዘው ወደ እግዚአብሔር ቤት ይመጣሉ። 27ነገር ግን የሰንበትን ቀን ሳትቀድሱ፣ በሰንበት ቀን ሸክም ተሸክማችሁ በኢየሩሳሌም በሮች በመግባት ትእዛዜን ብትጥሱ፣ በኢየሩሳሌም በሮች ላይ ምሽጎቿን የሚበላ፣ የማይጠፋ እሳት እጭራለሁ።’ ”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 17:1-27

1“บาปของยูดาห์ถูกสลักไว้ด้วยปากกาเหล็ก

จารึกไว้ด้วยปลายเพชร

ลงบนแผ่นหัวใจของเขา

และบนเชิงงอนที่แท่นบูชาของพวกเขา

2แม้แต่ลูกหลานของเขาก็ระลึกถึง

แท่นบูชาและเสาเจ้าแม่อาเชราห์17:2 คือ สัญลักษณ์ของเจ้าแม่อาเชราห์

ข้างต้นไม้ที่แผ่กิ่งก้านสาขา

และบนภูเขาสูงทั้งหลาย

3ภูเขาของเรา17:3 หรือภูเขาทั้งหลายในดินแดนนั้น

และทรัพย์สมบัติทั้งหมดของพวกเจ้า

ตลอดจนสถานบูชาบนที่สูงของเจ้า

เราจะให้ศัตรูมาริบไป

เพราะบาปทั่วแดนของเจ้า

4โดยความผิดของเจ้าเอง

เจ้าจะสูญเสียกรรมสิทธิ์ที่เรามอบให้

เราจะส่งเจ้าไปเป็นทาสของศัตรู

ในดินแดนซึ่งเจ้าไม่รู้จัก

เพราะเจ้าจุดไฟโทสะของเรา

มันจะเผาผลาญตลอดไป”

5องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“คำสาปแช่งตกอยู่แก่ผู้ที่ไว้วางใจในมนุษย์

พึ่งพละกำลังของเขา

และเอาใจออกห่างองค์พระผู้เป็นเจ้า

6เขาจะเป็นเหมือนพุ่มไม้ในถิ่นกันดาร

มองไม่เห็นความเจริญรุ่งเรืองที่มาถึง

เขาจะอาศัยในถิ่นแห้งแล้งของทะเลทราย

ในเขตดินกร่อยซึ่งไม่มีใครอาศัย

7“แต่ความสุขมีแก่ผู้ที่ไว้วางใจในองค์พระผู้เป็นเจ้า

ผู้ที่มีความเชื่อมั่นในพระองค์

8เขาจะเป็นเหมือนต้นไม้ที่ปลูกไว้ริมน้ำ

ซึ่งหยั่งรากลงไปริมธารน้ำ

มันไม่กลัวความร้อนที่มาถึง

ใบของมันเขียวขจีอยู่เสมอ

มันไม่วิตกในปีที่แห้งแล้ง

และไม่หยุดออกผล”

9จิตใจเป็นตัวล่อลวงเหนือกว่าสิ่งอื่นใด

และเสื่อมทรามจนสุดจะแก้

ใครจะเข้าใจจิตใจนั้นได้?

10“เราผู้เป็นพระยาห์เวห์พิเคราะห์ดูจิตใจ

และตรวจสอบความคิด

เพื่อให้บำเหน็จแก่ทุกคนตามผลการกระทำ

และตามความประพฤติของเขา”

11ผู้ซึ่งมั่งมีด้วยวิธีทุจริต

ก็เหมือนนกที่กกไข่ซึ่งมันไม่ได้วาง

เมื่อถึงวัยกลางคน ทรัพย์สมบัติก็พรากจากเขาไป

และในบั้นปลายเขาจะกลายเป็นคนโง่เขลา

12สถานนมัสการของข้าพระองค์ทั้งหลายเป็นบัลลังก์อันรุ่งเรือง

ได้รับการเทิดทูนไว้ตั้งแต่ต้น

13ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงเป็นความหวังของอิสราเอล

คนทั้งปวงที่ละทิ้งพระองค์จะอัปยศอดสู

ผู้ที่หันไปจากพระองค์จะถูกจารึกไว้ในธุลีดิน

เพราะเขาละทิ้งองค์พระผู้เป็นเจ้า

ผู้ทรงเป็นบ่อน้ำพุซึ่งมีน้ำที่ให้ชีวิต

14ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า ขอทรงรักษาข้าพระองค์ แล้วข้าพระองค์จะหายดี

ขอทรงช่วย แล้วข้าพระองค์จะรอด

เพราะพระองค์คือผู้ที่ข้าพระองค์ถวายการสรรเสริญ

15พวกเขาพร่ำพูดกับข้าพระองค์ว่า

“ไหนล่ะ พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้า?

ให้มันเป็นไปตามนั้น เดี๋ยวนี้สิ!”

16ข้าพระองค์ไม่ได้หนีจากการเป็นคนเลี้ยงแกะของพระองค์

พระองค์ทรงทราบว่าข้าพระองค์ไม่ได้ปรารถนาวันแห่งความสิ้นหวัง

สิ่งที่ข้าพระองค์เอ่ยปากบอกพวกเขา ก็แจ้งอยู่ต่อหน้าพระองค์

17ขออย่าทรงเป็นเหตุให้ข้าพระองค์คร้ามกลัว

พระองค์ทรงเป็นที่ลี้ภัยของข้าพระองค์ในวันแห่งภัยพิบัติ

18ขอให้ผู้กดขี่ข่มเหงข้าพระองค์ต้องอับอายขายหน้า

แต่ขอทรงปกป้องข้าพระองค์จากความอัปยศ

ขอให้พวกเขาอกสั่นขวัญแขวน

แต่ขอทรงคุ้มครองข้าพระองค์ให้พ้นจากความหวาดหวั่น

ขอทรงนำวันแห่งภัยพิบัติมายังเขา

ขอทรงทำลายเขาด้วยหายนะที่รุนแรงเป็นสองเท่า

รักษาวันสะบาโตให้บริสุทธิ์

19องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “จงไปยืนอยู่ที่ประตูเมืองเยรูซาเล็มซึ่งกษัตริย์ยูดาห์เสด็จเข้าออก รวมทั้งประตูอื่นๆ ทั้งหมดของเยรูซาเล็ม 20จงบอกคนทั้งปวงว่า ‘จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าเถิด กษัตริย์ยูดาห์ ชนยูดาห์ และชาวกรุงเยรูซาเล็มซึ่งผ่านเข้าออกประตูเหล่านี้ 21องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่าจงระวังอย่าแบกสิ่งของในวันสะบาโต หรือนำสิ่งใดผ่านเข้าออกประตูของเยรูซาเล็ม 22อย่าแบกสิ่งใดออกจากบ้านเรือนของเจ้า หรือกระทำกิจการงานใดๆ ในวันสะบาโต แต่จงรักษาวันสะบาโตให้บริสุทธิ์ตามที่เราได้บัญชาบรรพบุรุษของเจ้าไว้ 23แต่คนเหล่านั้นไม่ฟัง ไม่ใส่ใจ พวกเขาดื้อดึงหัวแข็ง ไม่ยอมใส่ใจและรับฟังคำตักเตือน 24องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า แต่ถ้าพวกเจ้าใส่ใจเชื่อฟังเรา และไม่แบกสิ่งใดผ่านประตูในวันสะบาโต แต่รักษาวันสะบาโตให้บริสุทธิ์โดยไม่ทำงานใดๆ ในวันนั้น 25เมื่อนั้นเหล่ากษัตริย์ผู้ครองบัลลังก์ของดาวิดจะเข้าออกประตูต่างๆ ของกรุงนี้พร้อมกับเหล่าขุนนาง พวกเขาจะนั่งบนรถม้าศึกและหลังม้า ติดตามด้วยชนยูดาห์และชาวเยรูซาเล็ม และกรุงนี้จะมีผู้คนอาศัยอยู่ตลอดไป 26ประชาชนจากเมืองต่างๆ ของยูดาห์ และหมู่บ้านต่างๆ รอบเยรูซาเล็ม จากเขตแดนของเบนยามิน จากเชิงเขาตะวันตก จากแถบภูเขาและเนเกบ จะนำเครื่องเผาบูชา ธัญบูชา เครื่องหอม และเครื่องบูชาขอบพระคุณมายังพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้า 27แต่หากพวกเจ้ายไม่เชื่อฟังเรา ไม่ยอมรักษาวันสะบาโตให้บริสุทธิ์ หากเจ้ายังนำสัมภาระผ่านประตูเมืองทั้งหลายของเยรูซาเล็มในวันสะบาโต เราก็จะจุดไฟเผาประตูเมืองเหล่านี้ เป็นไฟไม่รู้ดับซึ่งจะเผาผลาญป้อมต่างๆ ของเมืองนี้จนหมดสิ้น’ ”