ኤርምያስ 13 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 13:1-27

ከተልባ እግር የተሠራ መቀነት

1እግዚአብሔር፣ “ሄደህ ከተልባ እግር የተሠራ መቀነት ግዛ፤ ወገብህንም ታጠቅበት፤ ነገር ግን ውሃ አታስነካው” አለኝ። 2ስለዚህ እግዚአብሔር እንዳዘዘኝ መቀነቱን ገዛሁ፤ ወገቤንም ታጠቅሁበት።

3ለሁለተኛም ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፤ 4“ገዝተህ የታጠቅህበትን መቀነት ይዘህ ወደ ኤፍራጥስ13፥4 ወይም ፌሬጥ ሂድ፤ በዚያም በዐለት ንቃቃት ውስጥ ሸሽገው።” 5ስለዚህ እግዚአብሔር በነገረኝ መሠረት ወደ ኤፍራጥስ ሄጄ ሸሸግሁት።

6ከብዙ ቀን በኋላም እግዚአብሔር፣ “ተነሥተህ ወደ ኤፍራጥስ ሂድ፤ በዚያ እንድትሸሽገው የነገርሁህን መቀነት አምጣ” አለኝ። 7እኔም ወደ ኤፍራጥስ ሄጄ፣ መታጠቂያውን ከሸሸግሁበት ቦታ ቈፍሬ አወጣሁ፤ መታጠቂያውም ተበላሽቶ፣ ከጥቅም ውጭም ሆኖ ነበር።

8የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፤ 9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የይሁዳን ትዕቢትና የኢየሩሳሌምን እብሪት እንደዚሁ አጠፋለሁ። 10ቃሌን መስማት እንቢ ብለው በልባቸው እልኸኝነት በመሄድ ሊያመልኳቸውና ሊሰግዱላቸው ሌሎችን ጣዖቶች የሚከተሉ እነዚህ ክፉ ሕዝቦች ከጥቅም ውጭ እንደ ሆነው እንደዚህ መቀነት ይበላሻሉ። 11መቀነት በሰው ወገብ ላይ እንደሚታሰር፣ መላው የእስራኤልና የይሁዳ ቤት ከእኔ ጋር ተጣብቆ ለስሜ ምስጋናና ክብር፣ የእኔ ሕዝብ እንዲሆንልኝ አድርጌው ነበር፤ ሕዝቤ ግን አልሰማም’ ይላል እግዚአብሔር

የወይን ጠጅ ማድጋ

12“እንዲህ በላቸው፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ማድጋ ሁሉ በወይን ጠጅ ይሞላል’፤ እነርሱም፣ ‘ማድጋ ሁሉ በወይን ጠጅ እንደሚሞላ እኛ አናውቅምን?’ ቢሉህ፣ 13እንዲህ በላቸው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጡ ነገሥታትን፣ ካህናትን፣ ነቢያትን እንዲሁም በኢየሩሳሌም የሚኖሩትን ሁሉ ጨምሮ በዚህች ምድር የሚኖሩትን ሁሉ በስካር እሞላቸዋለሁ። 14አንዱን ሰው ከሌላው ጋር፣ አባትንና ወንድ ልጅን እርስ በእርስ አጋጫለሁ፤” ይላል እግዚአብሔር፤ ያለ ሐዘኔታ፣ ያለ ምሕረትና ያለ ርኅራኄ አጠፋቸዋለሁ።’ ”

የትዕቢት ውጤት

15እግዚአብሔር ተናግሯልና፣

ስሙ፤ ልብ በሉ፤

ትዕቢተኛም አትሁኑ።

16ጨለማን ሳያመጣ፣

በሚጨልሙትም ተራሮች ላይ፣

እግሮቻችሁ ሳይሰናከሉ፣

ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር ክብርን ስጡ።

ብርሃንን ተስፋ ታደርጋላችሁ፤

እርሱ ወደ ጨለማ ይለውጠዋል፤

ድቅድቅ ጨለማም ያደርገዋል።

17ባትሰሙ ግን፣

ነፍሴ ስለ ትዕቢታችሁ፣

በስውር ታለቅሳለች፤

የእግዚአብሔር መንጋ ተማርኳልና፣

ዐይኔ አምርሮ ያለቅሳል፤

እንባዬም እንደ ጐርፍ ይወርዳል።

18ለንጉሡና ለእናቱ ለእቴጌዪቱ፣

“የክብር ዘውዳችሁ ከራሳችሁ ይወድቃልና፣

ከዙፋናችሁ ውረዱ” በላቸው።

19በኔጌቭ ያሉ ከተሞች ይዘጋሉ፤

የሚከፍታቸውም አይኖርም።

ይሁዳ ሁሉ ተማርኮ ይሄዳል፤

ሙሉ በሙሉም ይዘጋል።

20ዐይኖቻችሁን ከፍታችሁ፣

ከሰሜን የሚመጡትን እዩ።

ለአንቺ የተሰጠው መንጋ፣

የተመካሽባቸው በጎች የት አሉ?

21ልዩ ወዳጆች እንዲሆኑሽ ያስተማርሻቸው፣

ባለ ሥልጣን ሲሆኑብሽ ምን ትያለሽ?

እንደምትወልድ ሴት፣

ምጥ አይዝሽምን?

22“ይህ ለምን ደረሰብኝ?” ብለሽ

ራስሽን ብትጠይቂ፣

ልብስሽን ተገልበሽ የተገፈተርሽው፣

በሰውም እጅ የተንገላታሽው፣

ከኀጢአትሽ ብዛት የተነሣ ነው።

23ኢትዮጵያዊ13፥23 ዕብራይስጡ ኩሻዊ ይላል (ምናልባት በላይኛው አባይ አካባቢ የሚኖር ሰው ሊሆን ይችላል)። መልኩን፣

ነብርስ ዝንጕርጕርነቱን መለወጥ ይችላልን?

እናንት ክፉ ማድረግ የለመዳችሁትም፣

መልካም ማድረግ አትችሉም።

24“የበረሓ ነፋስ ብትንትኑን እንደሚያወጣው ገለባ፣

እንዲሁ እበታትናችኋለሁ።

25እኔን ረስተሽ፣

በከንቱ አማልክት ስለ ታመንሽ፣

ያወጅሁልሽ ድርሻሽ፣

ዕጣ ፈንታሽ ይህ ነው፤”

ይላል እግዚአብሔር

26“ኀፍረትሽ እንዲገለጥ፣

ልብስሽን ፊትሽ ድረስ እገልባለሁ፤

27በኰረብቶችና በሜዳዎች ላይ፣

አስጸያፊ ተግባርሽን፣

ምንዝርናሽንና ማሽካካትሽን፣

ኀፍረተ ቢስ ግልሙትናሽን አይቻለሁ።

ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ወዮልሽ፤

ከርኩሰትሽ የማትጸጂው እስከ መቼ ነው?”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 13:1-27

ผ้าคาดเอวลินิน

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “ไปซื้อผ้าคาดเอวลินินมาคาดไว้ แต่อย่าให้มันถูกน้ำ” 2ฉะนั้นข้าพเจ้าจึงไปซื้อผ้าลินินผืนหนึ่งมาคาดเอวไว้ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่ง

3แล้วพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าเป็นครั้งที่สองว่า 4“จงเอาผ้าคาดเอวที่เจ้าซื้อและคาดอยู่นั้นออกไปที่แม่น้ำยูเฟรติส13:4 อาจเรียกอีกอย่างหนึ่งว่าเปรัทเช่นเดียวกับข้อ 5-7 และซ่อนมันไว้ในซอกหิน” 5ดังนั้นข้าพเจ้าก็ออกไปที่แม่น้ำยูเฟรติสและซ่อนมันไว้ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่ง

6หลายวันต่อมา องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “บัดนี้จงไปที่แม่น้ำนั้น เอาผ้าคาดเอวที่เราสั่งให้เจ้าซ่อนไว้มา” 7ดังนั้นข้าพเจ้าก็ไปที่แม่น้ำยูเฟรติสและขุดผ้าคาดเอวออกมาจากซอกที่ได้เอาไปซ่อนไว้ แต่บัดนี้มันขาดยุ่ยใช้การไม่ได้เลย

8แล้วพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าว่า 9องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘เราจะทำลายเกียรติภูมิของยูดาห์และเยรูซาเล็มอย่างนี้แหละ 10ประชากรที่ชั่วร้ายเหล่านี้ ซึ่งไม่ยอมฟังถ้อยคำของเรา ชอบดื้อดึงทำตามใจตนเอง และหันไปติดตามปรนนิบัตินมัสการพระอื่นๆ จะเป็นเหมือนผ้าคาดเอวนี้คือใช้การไม่ได้เลย!’ 11องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘ผ้าคาดเอวแนบติดกับเอวของคนฉันใด เราได้ทำให้ยูดาห์และอิสราเอลแนบสนิทกับเราเพื่อเป็นประชากรของเรา เป็นเกียรติภูมิ ชื่อเสียง และคำสรรเสริญของเราฉันนั้น แต่พวกเขาไม่ยอมฟัง’

ถุงหนังใส่เหล้าองุ่น

12“จงบอกพวกเขาว่า ‘พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสว่า ถุงหนังใส่เหล้าองุ่นทุกใบควรจะมีเหล้าองุ่นเต็ม’ และหากพวกเขาตอบว่า ‘เรารู้แล้วไม่ใช่หรือว่าถุงหนังใส่เหล้าองุ่นทุกใบควรจะมีเหล้าองุ่นเต็ม?’ 13ก็จงบอกพวกเขาว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า เราจะทำให้ทุกคนที่อาศัยในดินแดนนี้เมามาย ตั้งแต่กษัตริย์ที่นั่งบนบัลลังก์ของดาวิด บรรดาปุโรหิตและผู้เผยพระวจนะ ตลอดจนคนทั้งปวงซึ่งอาศัยในกรุงเยรูซาเล็ม 14เราจะจับพวกเขากระแทกกันเอง ไม่ว่าพ่อหรือลูก เราจะไม่ยอมให้ความสงสารหรือความเมตตาเอ็นดูมายับยั้งเราไม่ให้ทำลายล้างพวกเขาเลย องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น’ ”

จะต้องตกเป็นเชลย

15จงฟังและใส่ใจ

อย่าเย่อหยิ่ง

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสไว้แล้ว

16จงถวายเกียรติแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน

ก่อนที่พระองค์จะทรงนำความมืดมนมา

ก่อนที่เท้าของท่านสะดุดล้ม

บนภูเขาอันมืดมน

ท่านมุ่งหวังความสว่าง

แต่พระองค์ทรงผันแปรมันเป็นความมืดมน

เปลี่ยนมันเป็นความมืดทึบ

17แต่หากท่านไม่ยอมฟัง

ข้าพเจ้าจะแอบร้องไห้

เนื่องด้วยความหยิ่งยโสของท่าน

ข้าพเจ้าจะร่ำไห้ด้วยความขมขื่น

ดวงตาของข้าพเจ้าจะหลั่งน้ำตานองหน้า

เพราะฝูงแกะขององค์พระผู้เป็นเจ้าถูกจับไปเป็นเชลย

18จงทูลกษัตริย์และราชมารดาว่า

“ลงมาจากราชบัลลังก์เถิด

เพราะมงกุฎอันธำรงเกียรติ

จะร่วงหล่นจากพระเศียรของพระองค์”

19เมืองต่างๆ ในเนเกบจะถูกปิด

และจะไม่มีใครเปิดได้

ยูดาห์จะถูกกวาดต้อนไปเป็นเชลย

ถูกกวาดต้อนไปจนหมดสิ้น

20จงเงยหน้าขึ้นมองดูคนทั้งหลาย

ที่มาจากทางเหนือ

ไหนล่ะฝูงแกะที่เรามอบหมายให้เจ้าดูแล

ฝูงแกะที่เจ้าโอ้อวด?

21เจ้าจะว่าอย่างไรเมื่อองค์พระผู้เป็นเจ้า

ทรงตั้งผู้ที่เจ้าถือว่าเป็นพันธมิตรนั้นมาครอบครองเจ้า?

เจ้าจะไม่เจ็บปวด

เหมือนผู้หญิงที่กำลังคลอดลูกหรือ?

22และหากเจ้าถามตัวเองว่า

“ทำไมหนอเรื่องทั้งหมดนี้จึงเกิดขึ้นกับเรา?”

ก็เพราะบาปมากมายของเจ้าน่ะสิ

กระโปรงของเจ้าจึงถูกฉีกขาด

และกายของเจ้าถูกย่ำยี

23ชาวเอธิโอเปีย13:23 ภาษาฮีบรูว่าชาวคูชคงจะเป็นคนจากตอนบนของลุ่มแม่น้ำไนล์จะเปลี่ยนสีผิวของตนได้หรือ?

เสือดาวจะลบลายของมันได้หรือ?

พวกเจ้าซึ่งคุ้นเคยกับการทำชั่ว

ก็ไม่สามารถทำดีได้

24“เราจะทำให้เจ้ากระจัดกระจายเหมือนแกลบ

ที่ถูกลมทะเลทรายพัดปลิวไป

25นี่คือชะตากรรมของเจ้า

เป็นส่วนที่เรากำหนดให้เจ้า”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้

“เพราะเจ้าลืมเรา

และไปวางใจในเทพเจ้าจอมปลอม

26เราจะถลกกระโปรงของเจ้าขึ้นปิดหน้าเจ้า

เพื่อให้ความอัปยศอดสูของเจ้าเป็นที่ประจักษ์

27คือการล่วงประเวณี ความมักมากในกาม

การขายเนื้อขายตัวอย่างไร้ยางอายของเจ้า!

เราได้เห็นความประพฤติอันน่าเดียดฉันท์ของเจ้า

บนภูเขาทั้งหลายและตามท้องทุ่งต่างๆ

วิบัติแก่เจ้า เยรูซาเล็มเอ๋ย!

เจ้าจะแปดเปื้อนมลทินไปอีกนานสักเท่าใดหนอ?”