ኢዮብ 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 9:1-35

ኢዮብ

1ኢዮብ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“በርግጥ ነገሩ እንዲህ እንደ ሆነ ዐውቃለሁ፤

ነገር ግን ሥጋ ለባሽ በእግዚአብሔር ፊት እንዴት ጻድቅ ሊሆን ይችላል?

3ሰው ከእርሱ ጋር ለመከራከር ቢፈልግ፣

ከሺሕ ጥያቄ አንዱን እንኳ መመለስ አይችልም።

4ጥበቡ ጥልቅ፣ ኀይሉም ታላቅ ነውና፤

እርሱን ተቃውሞ ያለ አንዳች ጕዳት የሄደ ማን ነው?

5ሳያውቁት፣ ተራሮችን ይነቅላቸዋል፤

በቍጣውም ይገለብጣቸዋል።

6ምድርን ከስፍራዋ ያናውጣታል፤

ምሰሶዎቿንም ያንቀጠቅጣል።

7ፀሓይን ያዝዛታል፤ አትወጣምም፤

ከዋክብትንም በማኅተም ያሽጋል።

8እርሱ ብቻውን ሰማያትን ዘርግቷል፤

በባሕርም ማዕበል ላይ ይራመዳል።

9እርሱ የድብና የኦሪዮን፣

የፕልያዲስና የደቡብ ከዋክብት ፈጣሪ ነው፤

10የማይመረመሩ ድንቅ ነገሮችን፣

የማይቈጠሩ ታምራትንም ያደርጋል።

11እነሆ፤ በአጠገቤ ሲያልፍ አላየውም፤

በጐኔም ሲሄድ፣ ልገነዘበው አልችልም።

12ቢነጥቅ፣ ማን ይከለክለዋል?

‘ምን መሥራትህ ነው?’ የሚለውስ፣ ማን ነው?

13እግዚአብሔር ቍጣውን አይመልስም፤

ረዓብን የሚረዱ እንኳ ይሰግዱለታል።

14“ታዲያ፣ ከእርሱ ጋር እሟገት ዘንድ፣

ልከራከረውም ቃላት እመርጥ ዘንድ፣ እንዴት እችላለሁ?

15ጻድቅ ብሆንም እንኳ፣ ልመልስለት አልችልም፤

ዳኛዬን ምሕረት ከመለመን ሌላ ላደርግ የምችለው የለም።

16ጠርቼው ‘አቤት!’ ቢለኝም፣

ያዳምጠኛል ብዬ አላምንም።

17በዐውሎ ነፋስ ይሰብረኛል፤

ቍስሌንም ያለ ምክንያት ያበዛል፤

18ምሬትን አጠገበኝ እንጂ፣

ለመተንፈስ እንኳ ፋታ አልሰጠኝም።

19የኀይል ነገር ከተነሣ፣ እርሱ ኀያል ነው!

የፍትሕም ነገር ከተነሣ፣ መጥሪያ ሊሰጠው9፥19 ሰብዓ ሊቃናት ይመልከቱ፤ የዕብራይስጡ ሊሰጠኝ ይላል። የሚችል ማን ነው?

20ንጹሕ ብሆን እንኳ፣ አንደበቴ ይፈርድብኛል፤

እንከን የለሽ እንኳ ብሆን፣ በደለኛ ያደርገኛል።

21“ያለ ነቀፋ ብሆንም እንኳ፣

ስለ ራሴ ግድ የለኝም፤

የገዛ ሕይወቴንም እንቃታለሁ።

22ሁሉም አንድ ነው፤

‘እርሱ ጻድቁንና ኀጥኡን ያጠፋል’ የምለውም ለዚህ ነው።

23መዓት ወርዶ ድንገት ሰው ሲጨርስ፣

በንጹሓን መከራ ይሣለቃል።

24ምድር በክፉዎች እጅ ስትወድቅ፣

እርሱ የፈራጆቿን ዐይን ይሸፍናል፤

ታዲያ፣ ይህን ያደረገው እርሱ ካልሆነ ማን ሊሆን ይችላል?

25“ዘመኔ ከሚሮጥ ሰው ይልቅ ይፈጥናል፤

አንዳችም ደስታ ሳያይ ያልፋል።

26ከደንገል እንደ ተሠራ ታንኳ፣

ለመንጠቅ ቍልቍል እንደሚበርር ንስር ይፈጥናል።

27‘ማጕረምረሜን እረሳለሁ፤

ገጽታዬን ቀይሬ ፈገግ እላለሁ’ ብል፣

28ንጹሕ አድርገህ እንደማትቈጥረኝ ስለማውቅ፣

መከራዬን ሁሉ እፈራለሁ።

29በደለኛ መሆኔ ካልቀረ፣

ለምን በከንቱ እለፋለሁ?

30ሰውነቴን በሳሙና9፥30 ወይም በረዶ ብታጠብ፣

እጄንም በልዩ መታጠቢያ ባነጻ፣

31ልብሴ እንኳ እስኪጸየፈኝ ድረስ፣

በዐዘቅት ውስጥ ታሰጥመኛለህ።

32“መልስ እሰጠው ዘንድ፣ እሟገተውም ዘንድ፣

እርሱ እንደ እኔ ሰው አይደለም።

33በሁለታችን ላይ እጅ የሚጭን፣

በመካከላችንም የሚዳኝ ቢኖር፣

34ግርማው እንዳያስፈራኝ፣

እግዚአብሔር በትሩን ከእኔ ላይ ቢያነሣ፣

35ሳልፈራው በተናገርሁት ነበር፤

አሁን ባለሁበት ሁኔታ ግን፣ አልችልም።

Thai New Contemporary Bible

โยบ 9:1-35

โยบ

1โยบจึงตอบว่า

2“จริงอยู่ ข้ารู้แล้วว่าเป็นอย่างนั้น

แต่มนุษย์จะชอบธรรมสำหรับพระเจ้าได้อย่างไร?

3แม้คนใดปรารถนาจะโต้แย้งกับพระเจ้า

เขาก็ไม่สามารถตอบพระองค์ได้แม้แต่ครั้งเดียวจากพันครั้ง

4เพราะสติปัญญาของพระเจ้าลึกซึ้ง และฤทธิ์อำนาจของพระองค์มหาศาล

ใครเล่าจะต่อต้านพระเจ้าและรอดมาโดยไม่มีอันตราย?

5พระองค์ทรงเคลื่อนภูเขาโดยที่มันไม่ทันรู้ตัว

และพลิกคว่ำมันด้วยพระพิโรธ

6พระองค์ทรงเขย่าโลกให้ออกจากที่

ทำให้เสาหลักของมันสั่นคลอน

7พระองค์ตรัสสั่ง ดวงอาทิตย์ก็ไม่ส่องแสง

พระองค์ทรงผนึกดวงดาวไม่ให้ฉายแสง

8พระองค์แต่ผู้เดียวที่ทรงคลี่ฟ้าสวรรค์ออก

และทรงย่ำเหนือคลื่นทะเล

9พระองค์ทรงสร้างดาวจระเข้และดาวไถ

ดาวลูกไก่และหมู่ดาวแห่งทิศใต้

10พระองค์ทรงกระทำการอัศจรรย์

ที่เกินการหยั่งรู้และเหลือคณานับ

11เมื่อพระองค์เสด็จผ่านข้า ข้าไม่สามารถเห็นพระองค์

เมื่อเสด็จผ่านไป ข้าไม่สามารถประจักษ์

12เมื่อพระองค์ทรงฉวยไป ใครจะยับยั้งพระองค์ได้?

ใครจะอาจหาญทูลถามพระองค์ว่า ‘ทรงทำอะไรนั่น?’

13พระเจ้าไม่ได้ทรงยับยั้งพระพิโรธ

แม้แต่กองกำลังของราหับก็กลัวลานอยู่แทบพระบาทพระองค์

14“แล้วข้าจะบังอาจโต้แย้งกับพระเจ้าหรือ?

ข้าจะสรรหาคำอะไรมาโต้เถียงกับพระองค์หรือ?

15แม้ข้าไม่ผิด ข้าก็ไม่อาจโต้ตอบพระองค์

ได้แต่วอนขอความเมตตาจากองค์ตุลาการ

16ถึงแม้ว่าข้าทูลร้องเรียกและพระองค์ทรงขานตอบ

ข้าก็ไม่เชื่อว่าพระองค์จะทรงสดับฟัง

17พระองค์คงจะทรงบดขยี้ข้าด้วยลมพายุ

และทวีบาดแผลของข้าโดยไม่มีสาเหตุ

18พระองค์จะไม่ทรงยอมให้ข้าหายใจ

แต่เติมความรันทดขมขื่นใส่ข้าจนล้นปรี่

19ถ้าจะว่าด้วยเรื่องพลัง พระองค์ทรงเกรียงไกรนัก!

ถ้าจะว่าด้วยเรื่องความยุติธรรม ใครจะเรียกพระองค์มาให้การได้?9:19 ภาษาฮีบรูว่าใครจะเรียกข้ามาให้การได้?

20ถึงแม้ข้าไร้ผิด ปากของข้าเองยังกล่าวโทษข้า

แม้ข้าดีพร้อม ปากของข้าก็ยังจะพูดว่าตัวเองมีมลทิน

21“แม้ว่าข้าไร้ตำหนิ

ข้าก็ไม่แยแสตัวเอง

ข้าชิงชังชีวิตของข้าเองยิ่งนัก

22มันไม่ต่างอะไรกัน ฉะนั้นข้าจึงกล่าวว่า

‘พระองค์ทรงทำลายทั้งคนดีพร้อมและคนชั่วร้าย’

23เมื่อโทษทัณฑ์นำความตายมาโดยฉับพลัน

พระองค์ทรงยิ้มเยาะความสิ้นหวังของผู้ที่ไม่มีความผิด

24เมื่อแผ่นดินตกอยู่ในมือของคนชั่ว

พระเจ้าทรงทำให้ตาของบรรดาตุลาการมืดบอด

หากไม่ใช่พระองค์แล้วจะเป็นใครเล่า?

25“วันคืนของข้าพระองค์ไวยิ่งกว่านักวิ่ง

ลอยลับไปโดยไม่มีความชื่นใจแม้แต่น้อยนิด

26มันแล่นปราดไปเหมือนเรือพาไพรัส

เหมือนนกอินทรีโฉบลงบนเหยื่อ

27หากกล่าวว่า ‘ข้าพระองค์จะลืมคำโอดครวญของตน

ข้าพระองค์จะเปลี่ยนสีหน้าและยิ้มแย้มร่าเริง’

28แต่ข้าพระองค์ก็ยังขยาดความทุกข์ยากทั้งสิ้นของข้าพระองค์

เพราะรู้ว่าพระองค์ยังทรงถือว่าข้าพระองค์มีความผิด

29ในเมื่อถูกตัดสินว่าผิด

ก็แล้วข้าพระองค์จะดิ้นรนต่อสู้ให้เปล่าประโยชน์ไปทำไม?

30ถึงข้าพระองค์จะอาบน้ำชำระกายด้วยสบู่9:30 หรือด้วยหิมะ

เอาด่างล้างมือให้สะอาด

31พระองค์ก็จะทรงเหวี่ยงข้าพระองค์ลงในบ่อโคลน

จนแม้แต่เสื้อผ้าของข้าพระองค์ก็ยังรังเกียจตัวข้าพระองค์เอง

32“พระเจ้าไม่ใช่มนุษย์อย่างข้า ที่ข้าจะไปโต้ตอบได้

ที่เราจะเผชิญหน้ากันในศาล

33อยากให้มีใครสักคนเป็นคนกลางระหว่างเราทั้งสอง

เผื่อจะได้ช่วยไกล่เกลี่ย

34ใครสักคนที่จะช่วยเก็บไม้เรียวของพระเจ้าไปจากข้า

เพื่อข้าจะได้เลิกหวาดหวั่นพระอาชญาของพระองค์

35แล้วข้าจะพูดโดยไม่ต้องหวาดกลัวพระองค์

แต่ขณะนี้ข้าทำเช่นนั้นไม่ได้