ኢዮብ 9 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 9:1-35

ኢዮብ

1ኢዮብ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“በርግጥ ነገሩ እንዲህ እንደ ሆነ ዐውቃለሁ፤

ነገር ግን ሥጋ ለባሽ በእግዚአብሔር ፊት እንዴት ጻድቅ ሊሆን ይችላል?

3ሰው ከእርሱ ጋር ለመከራከር ቢፈልግ፣

ከሺሕ ጥያቄ አንዱን እንኳ መመለስ አይችልም።

4ጥበቡ ጥልቅ፣ ኀይሉም ታላቅ ነውና፤

እርሱን ተቃውሞ ያለ አንዳች ጕዳት የሄደ ማን ነው?

5ሳያውቁት፣ ተራሮችን ይነቅላቸዋል፤

በቍጣውም ይገለብጣቸዋል።

6ምድርን ከስፍራዋ ያናውጣታል፤

ምሰሶዎቿንም ያንቀጠቅጣል።

7ፀሓይን ያዝዛታል፤ አትወጣምም፤

ከዋክብትንም በማኅተም ያሽጋል።

8እርሱ ብቻውን ሰማያትን ዘርግቷል፤

በባሕርም ማዕበል ላይ ይራመዳል።

9እርሱ የድብና የኦሪዮን፣

የፕልያዲስና የደቡብ ከዋክብት ፈጣሪ ነው፤

10የማይመረመሩ ድንቅ ነገሮችን፣

የማይቈጠሩ ታምራትንም ያደርጋል።

11እነሆ፤ በአጠገቤ ሲያልፍ አላየውም፤

በጐኔም ሲሄድ፣ ልገነዘበው አልችልም።

12ቢነጥቅ፣ ማን ይከለክለዋል?

‘ምን መሥራትህ ነው?’ የሚለውስ፣ ማን ነው?

13እግዚአብሔር ቍጣውን አይመልስም፤

ረዓብን የሚረዱ እንኳ ይሰግዱለታል።

14“ታዲያ፣ ከእርሱ ጋር እሟገት ዘንድ፣

ልከራከረውም ቃላት እመርጥ ዘንድ፣ እንዴት እችላለሁ?

15ጻድቅ ብሆንም እንኳ፣ ልመልስለት አልችልም፤

ዳኛዬን ምሕረት ከመለመን ሌላ ላደርግ የምችለው የለም።

16ጠርቼው ‘አቤት!’ ቢለኝም፣

ያዳምጠኛል ብዬ አላምንም።

17በዐውሎ ነፋስ ይሰብረኛል፤

ቍስሌንም ያለ ምክንያት ያበዛል፤

18ምሬትን አጠገበኝ እንጂ፣

ለመተንፈስ እንኳ ፋታ አልሰጠኝም።

19የኀይል ነገር ከተነሣ፣ እርሱ ኀያል ነው!

የፍትሕም ነገር ከተነሣ፣ መጥሪያ ሊሰጠው9፥19 ሰብዓ ሊቃናት ይመልከቱ፤ የዕብራይስጡ ሊሰጠኝ ይላል። የሚችል ማን ነው?

20ንጹሕ ብሆን እንኳ፣ አንደበቴ ይፈርድብኛል፤

እንከን የለሽ እንኳ ብሆን፣ በደለኛ ያደርገኛል።

21“ያለ ነቀፋ ብሆንም እንኳ፣

ስለ ራሴ ግድ የለኝም፤

የገዛ ሕይወቴንም እንቃታለሁ።

22ሁሉም አንድ ነው፤

‘እርሱ ጻድቁንና ኀጥኡን ያጠፋል’ የምለውም ለዚህ ነው።

23መዓት ወርዶ ድንገት ሰው ሲጨርስ፣

በንጹሓን መከራ ይሣለቃል።

24ምድር በክፉዎች እጅ ስትወድቅ፣

እርሱ የፈራጆቿን ዐይን ይሸፍናል፤

ታዲያ፣ ይህን ያደረገው እርሱ ካልሆነ ማን ሊሆን ይችላል?

25“ዘመኔ ከሚሮጥ ሰው ይልቅ ይፈጥናል፤

አንዳችም ደስታ ሳያይ ያልፋል።

26ከደንገል እንደ ተሠራ ታንኳ፣

ለመንጠቅ ቍልቍል እንደሚበርር ንስር ይፈጥናል።

27‘ማጕረምረሜን እረሳለሁ፤

ገጽታዬን ቀይሬ ፈገግ እላለሁ’ ብል፣

28ንጹሕ አድርገህ እንደማትቈጥረኝ ስለማውቅ፣

መከራዬን ሁሉ እፈራለሁ።

29በደለኛ መሆኔ ካልቀረ፣

ለምን በከንቱ እለፋለሁ?

30ሰውነቴን በሳሙና9፥30 ወይም በረዶ ብታጠብ፣

እጄንም በልዩ መታጠቢያ ባነጻ፣

31ልብሴ እንኳ እስኪጸየፈኝ ድረስ፣

በዐዘቅት ውስጥ ታሰጥመኛለህ።

32“መልስ እሰጠው ዘንድ፣ እሟገተውም ዘንድ፣

እርሱ እንደ እኔ ሰው አይደለም።

33በሁለታችን ላይ እጅ የሚጭን፣

በመካከላችንም የሚዳኝ ቢኖር፣

34ግርማው እንዳያስፈራኝ፣

እግዚአብሔር በትሩን ከእኔ ላይ ቢያነሣ፣

35ሳልፈራው በተናገርሁት ነበር፤

አሁን ባለሁበት ሁኔታ ግን፣ አልችልም።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約伯記 9:1-35

約伯的回應

1約伯回答說:

2「不錯,我知道你所言不虛,

但人怎能在上帝面前算為義人?

3人若想與祂辯駁,

千次也不能勝一次。

4祂充滿智慧,能力無比,

誰能抗拒祂還可平安無恙?

5祂可猝然挪動群山,

在怒氣中把山翻倒。

6祂震動大地,使其挪位,

以致地的支柱搖撼。

7祂一聲令下,

太陽便不再升起,

眾星也不再發光。

8祂獨自鋪展穹蒼,

步行在海浪之上。

9祂創造了北斗星、參星、昴星及南天的星座。

10祂行的奇事不可測度,

奇蹟不可勝數。

11祂經過我身旁,我卻看不見;

祂從旁邊掠過,我也無法察覺。

12祂若奪取,誰能阻擋?

誰敢問祂,『你做什麽?』

13上帝不會忍怒不發,

海怪9·13 海怪」希伯來文是「拉哈伯」,下同26·12的幫手必屈膝在祂腳前。

14「因此,我怎敢與祂辯駁?

怎敢措辭與祂理論?

15我縱然無辜,也無法申訴,

只能乞求我的審判者施恩。

16即使我呼喚祂的時候,祂回應我,

我仍不相信祂會垂聽我的聲音。

17祂用暴風摧毀我,

無故地使我飽受創傷。

18祂不肯讓我喘息,

祂使我嚐盡苦頭。

19若論力量,祂甚強大;

若上公堂,誰敢傳祂?

20即使我清白無辜,我的口也會認罪;

即使我純全無過,祂也會判我有罪。

21我雖純全無過,也已毫不在乎,

我厭惡我的生命。

22因為,我認為都是一樣,

純全無過的人和惡人都會被祂毀滅。

23災禍突然奪走人命時,

祂嘲笑無辜者的遭遇。

24大地落入惡人手中,

蒙蔽審判官眼睛的不是祂是誰?

25「我的年日比信差還快,

匆匆而過,不見幸福。

26我的歲月疾馳如快船,

快如急降抓食的老鷹。

27即使我說要忘掉怨恨,

拋開愁容,強顏歡笑,

28諸多的患難仍使我懼怕,

我知道祂9·28 」希伯來文是「你」,下同31節。不承認我無辜。

29既然我被定為有罪,

又何必徒然掙扎?

30即使我用雪水淨身,

用鹼水洗手,

31祂仍會把我扔進污坑,

連我的衣服也嫌棄我。

32祂並非我的同類,

我無法與祂爭辯,一起對簿公堂。

33我倆中間沒有仲裁者,

無人為我們斷定是非9·33 為我們斷定是非」希伯來文是「把手按在我們身上」。

34若能拿開祂責打我的刑杖,

使我不再受祂的驚嚇,

35我就會放膽發言,不必對祂心存恐懼,

但現在我卻不能這樣9·35 但現在我卻不能這樣」或譯「因為我知道自己的清白」。