ኢዮብ 8 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 8:1-22

በልዳዶስ

1ሹሐዊውም በልዳዶስ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“እንዲህ ያለውን ነገር የምትናገረው፣

ቃልህም እንደ ብርቱ ነፋስ የሚሆነው እስከ መቼ ነው?

3እግዚአብሔር ፍትሕን ያጣምማልን?

ሁሉን ቻይ አምላክስ ጽድቅን ያጣምማልን?

4ልጆችህ በእርሱ ላይ ኀጢአት ሠርተው ከሆነ፣

ለኀጢአታቸው ቅጣት አሳልፎ ሰጥቷቸዋል።

5ነገር ግን አንተ ወደ እግዚአብሔር ብትመለከት፣

ሁሉን ቻይ አምላክን ብትማፀን፣

6ንጹሕና ቅን ብትሆን፣ እርሱ ስለ አንተ አሁኑኑ ይነሣል፤

ወደ ተገቢውም ስፍራህ ይመልስሃል።

7ጅማሬህ አነስተኛ ቢመስልም፣

ፍጻሜህ እጅግ ታላቅ ይሆናል።

8“የቀደመውን ትውልድ ጠይቅ፤

አባቶቻቸውም የደረሱበትን መርምረህ አግኝ፤

9እኛ ትናንት ስለ ተወለድን አንዳች አናውቅምና፤

ዘመናችንም በምድር ላይ እንደ ጥላ ነው።

10እነርሱ የሚያስተምሩህና የሚነግሩህ፣

ከልቦናቸውም ቃልን የሚያወጡ አይደሉምን?

11ደንገል ረግረግ በሌለበት ስፍራ ይበቅላልን?

ቄጠማስ ውሃ በሌለበት ይለመልማልን?

12ገና በማደግ ላይ እያለ ሳይታጨድ፣

ከሌሎች ዕፀዋት ፈጥኖ ይደርቃል።

13እግዚአብሔርን የሚረሱ መጨረሻቸው እንዲህ ነው፤

አምላክ የለሽ ኑሮ የሚኖሩም ሁሉ ተስፋቸው ትጠፋለች።

14መተማመኛው ቀጭን ክር፣8፥14 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም።

ድጋፉም የሸረሪት ድር ነው።

15ድሩ ላይ ቢደገፍ ይበጠስበታል፤

አጥብቆም ቢይዘው አይጸናም።

16ውሃ እንደ ጠገበ ተክል፣ ፀሓይ እየሞቀው፣

ቅርንጫፉን ሁሉ በአትክልቱ ስፍራ ላይ ይዘረጋል።

17ሥሩን በድንጋይ ክምር ላይ ይጠመጥማል፤

በዐለትም መካከል ስፍራ ያበጃል።

18ከስፍራው ሲወገድ ግን፣

ያ ቦታ ‘አይቼህ አላውቅም’ ብሎ ይክደዋል።

19እነሆ፤ ሕይወቱ በዚህ ያከትማል፤8፥19 ወይም ያለው ደስታ ሁሉ

ሌሎች አትክልትም ከመሬት ይበቅላሉ።

20“እነሆ፤ እግዚአብሔር እንከን የሌለበትን ሰው አይጥልም፤

የክፉዎችንም እጅ አያበረታም፤

21እንደ ገና አፍህን በሣቅ፤

ከንፈሮችህንም በእልልታ ይሞላል።

22ጠላቶችህ ኀፍረት ይለብሳሉ፤

የክፉዎችም ድንኳን ይጠፋል።”

Japanese Contemporary Bible

ヨブ 記 8:1-22

8

ビルダデのことば

1シュアハ人ビルダデのヨブへの返答。

2「ヨブ、いつまでそんなことを言い続けるのか。

そんな激しいことばでまくし立てるのはやめよ。

3神が正義を曲げるだろうか。

4あなたの子どもたちが罪を犯し、

神から罰を受けても、

5あなたが全能の神に嘆願するなら、

6神は祈りを聞き、

元どおりの幸福な家庭としてくださる。

もっとも、あなたが潔白で正しければの話だが。

7たとえ一から出直しても、

やがて多くの財産を築くだろう。

8歴史の書物をひもとき、調べてみるがいい。

9私たちは生まれたばかりの赤ん坊のような者で、

ほんのわずかのことしか知らないのだ。

われわれの一生は影のようにはかない。

10だが、昔の人の知恵は大したものだ。

ほかの人の経験から、

あなたは次のことを学ぶことができる。

11-13神を忘れる者の望みは断たれる。

彼らは根を下ろす土のない葦や

水分を断たれた草のように、

鎌を入れないうちからしおれる。

14神を追い出した者は、

くもの巣を頼りにするようなもので、

頼みの綱はみな断ち切られる。

15自分の家にいれば安全だと思っていても、

家はいつまでもあるわけではない。

16朝のうちは、青々と茂る木のように力にあふれ、

枝は庭いっぱいに張っている。

17根は石地を伝い広がり、地下水にまで届く。

18ところが、そんな者が急に姿を消しても、

だれも悲しんではくれない。

19彼が期待できることといえば、これくらいだ。

そればかりか、彼の代わりに

ほかの者が地から芽を出す。

20いいか、考えてもみよ。

神は正しい人をお見捨てにならないし、

悪い者を栄えさせることもないのだ。

21あなたにも、いつか必ず笑顔を取り戻し、

喜びの叫びをあげる日がくる。

22あなたを憎む者は、結局は恥をかき、

悪者は滅ぶことになるのだ。」