ኢዮብ 8 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 8:1-22

በልዳዶስ

1ሹሐዊውም በልዳዶስ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“እንዲህ ያለውን ነገር የምትናገረው፣

ቃልህም እንደ ብርቱ ነፋስ የሚሆነው እስከ መቼ ነው?

3እግዚአብሔር ፍትሕን ያጣምማልን?

ሁሉን ቻይ አምላክስ ጽድቅን ያጣምማልን?

4ልጆችህ በእርሱ ላይ ኀጢአት ሠርተው ከሆነ፣

ለኀጢአታቸው ቅጣት አሳልፎ ሰጥቷቸዋል።

5ነገር ግን አንተ ወደ እግዚአብሔር ብትመለከት፣

ሁሉን ቻይ አምላክን ብትማፀን፣

6ንጹሕና ቅን ብትሆን፣ እርሱ ስለ አንተ አሁኑኑ ይነሣል፤

ወደ ተገቢውም ስፍራህ ይመልስሃል።

7ጅማሬህ አነስተኛ ቢመስልም፣

ፍጻሜህ እጅግ ታላቅ ይሆናል።

8“የቀደመውን ትውልድ ጠይቅ፤

አባቶቻቸውም የደረሱበትን መርምረህ አግኝ፤

9እኛ ትናንት ስለ ተወለድን አንዳች አናውቅምና፤

ዘመናችንም በምድር ላይ እንደ ጥላ ነው።

10እነርሱ የሚያስተምሩህና የሚነግሩህ፣

ከልቦናቸውም ቃልን የሚያወጡ አይደሉምን?

11ደንገል ረግረግ በሌለበት ስፍራ ይበቅላልን?

ቄጠማስ ውሃ በሌለበት ይለመልማልን?

12ገና በማደግ ላይ እያለ ሳይታጨድ፣

ከሌሎች ዕፀዋት ፈጥኖ ይደርቃል።

13እግዚአብሔርን የሚረሱ መጨረሻቸው እንዲህ ነው፤

አምላክ የለሽ ኑሮ የሚኖሩም ሁሉ ተስፋቸው ትጠፋለች።

14መተማመኛው ቀጭን ክር፣8፥14 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም።

ድጋፉም የሸረሪት ድር ነው።

15ድሩ ላይ ቢደገፍ ይበጠስበታል፤

አጥብቆም ቢይዘው አይጸናም።

16ውሃ እንደ ጠገበ ተክል፣ ፀሓይ እየሞቀው፣

ቅርንጫፉን ሁሉ በአትክልቱ ስፍራ ላይ ይዘረጋል።

17ሥሩን በድንጋይ ክምር ላይ ይጠመጥማል፤

በዐለትም መካከል ስፍራ ያበጃል።

18ከስፍራው ሲወገድ ግን፣

ያ ቦታ ‘አይቼህ አላውቅም’ ብሎ ይክደዋል።

19እነሆ፤ ሕይወቱ በዚህ ያከትማል፤8፥19 ወይም ያለው ደስታ ሁሉ

ሌሎች አትክልትም ከመሬት ይበቅላሉ።

20“እነሆ፤ እግዚአብሔር እንከን የሌለበትን ሰው አይጥልም፤

የክፉዎችንም እጅ አያበረታም፤

21እንደ ገና አፍህን በሣቅ፤

ከንፈሮችህንም በእልልታ ይሞላል።

22ጠላቶችህ ኀፍረት ይለብሳሉ፤

የክፉዎችም ድንኳን ይጠፋል።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 8:1-22

比勒达发言

1书亚比勒达回答约伯说:

2“你要这样絮叨到何时?

你的话犹如阵阵狂风。

3上帝岂会歪曲正义?

全能者岂会颠倒是非?

4如果你的儿女得罪了祂,

祂会给他们应有的惩罚。

5但你若寻求上帝,

向全能者恳求;

6你若纯洁、正直,

祂必起身相助,

恢复你应有的家园。

7你起初虽然卑微,

日后必兴旺发达。

8“你要请教先辈,

探究祖先的经验。

9因为我们就像昨天才出生,一无所知,

我们在世的日子如同掠影。

10先辈必给你教诲和指点,

向你道出明智之言。

11“蒲草无泥岂可长高?

芦苇无水岂可茂盛?

12它们还在生长、尚未割下,

已比百草先枯萎。

13忘记上帝的人,结局也是如此;

不信上帝的人,盼望终必破灭。

14他所仰仗的虚若游丝,

他所倚靠的诚如蛛网。

15他倚靠它,它却支撑不住;

他抓紧它,它却支离破碎。

16他像阳光下生机勃勃的植物,

枝条爬满了园囿,

17根茎盘绕石堆,

深深扎入石缝。

18一旦他被连根拔起,

原处必否认见过他。

19他的生命就这样消逝8:19 他的生命就这样消逝”或译“这就是他一生的乐趣”。

地上会兴起其他人。

20“上帝决不会抛弃纯全的人,

也不会扶持邪恶的人。

21祂要使你笑口常开,

欢声不断。

22憎恨你的人必抱愧蒙羞,

恶人的帐篷必不复存在。”