ኢዮብ 7 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 7:1-21

1“የሰው ሕይወት በምድር ላይ ብርቱ ተጋድሎ አይደለምን?

ዘመኑስ እንደ ምንደኛ ዘመን አይደለምን?

2የምሽትን ጥላ እንደሚመኝ አገልጋይ፣

ደመወዙንም እንደሚናፍቅ ምንደኛ፣

3እንዲሁ ከንቱ ወራት ታደሉኝ፣

የጕስቍልና ሌሊቶችም ተወሰኑልኝ።

4በተኛሁ ጊዜ ‘መቼ ነግቶ እነሣለሁ?’

እላለሁ፤ ሌሊቱ ይረዝማል፤ እስኪነጋም እገላበጣለሁ።

5አካሌ ቈስሎ ትልና ቅርፊት ለብሷል፤

ቈዳዬ አፈክፍኳል፤ ቍስሌም አመርቅዟል።

6“ዘመኔ ከሸማኔ መወርወሪያ ይልቅ ይፈጥናል፤

ያለ ተስፋም ያልቃል።

7ሕይወቴ ትንፋሽ ያህል እንደ ሆነች ዐስብ፤

ዐይኔም ከእንግዲህ ደስታን አያይም።

8አሁን የሚያየኝ ሰው ዐይን ከእንግዲህ አያየኝም፤

ትፈልገኛለህ፤ እኔ ግን የለሁም።

9ደመና በንኖ እንደሚጠፋ፣

ወደ መቃብር7፥9 የዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። የሚወርድም አይመለስም።

10ወደ ቤቱ ዳግመኛ አይመለስም፤

ስፍራውም ከእንግዲህ አያውቀውም።

11“ስለዚህ ከቶ ዝም አልልም፤

በመንፈሴ ጭንቀት እናገራለሁ፤

በነፍሴም ምሬት አጕረመርማለሁ።

12በላዬ ጠባቂ ታደርግ ዘንድ፣

እኔ ባሕር ነኝን ወይስ የባሕር አውሬ?

13ዐልጋዬ ያጽናናኛል፣

መኝታዬም ማጕረምረሜን ይቀንስልኛል ባልሁ ጊዜ፣

14አንተ በሕልም ታስፈራራኛለህ፤

በራእይም ታስደነግጠኛለህ፤

15ስለዚህ እንዲህ ሆኖ ከመኖር፣

መታነቅና መሞትን እመርጣለሁ።

16ሕይወቴን እጸየፋለሁ፤ ዘላለም መኖር አልፈልግም፤

ዘመኔ እንደ እስትንፋስ ነውና ተወኝ።

17“ከፍ ከፍ ታደርገው ዘንድ፣

ልብህንም ትጥልበት ዘንድ ሰው ምንድን ነው?

18በየማለዳው ትመረምረዋለህ፤

በየጊዜውም ትፈትነዋለህ።

19ዐይንህን ከእኔ ላይ አታነሣምን?

ምራቄን እንኳ እስክውጥ ፋታ አትሰጠኝምን?

20ሰውን የምትከታተል ሆይ፤

ኀጢአት ብሠራ፣ አንተን ምን አደርግሃለሁ?

ለምን ዒላማህ አደረግኸኝ?

ለምንስ ሸክም ሆንሁብህ?7፥20 ጥቂት የማሶሬቲክ ጽሑፍ ቅጆች፣ የጥንት የዕብራውያን ጸሓፍት ትውፊትና ሰብዓ ሊቃናት እንዲሁ ሲሆኑ፣ አብዛኛው የማሶሬቲክ ጽሑፍ ቅጆች ግን ለራሴ ሸክም ሆንሁ ይላሉ።

21መተላለፌን ለምን ይቅር አትልም?

ኀጢአቴንስ ለምን አታስወግድልኝም?

ትቢያ ውስጥ የምጋደምበት ጊዜ ደርሷል፤

ትፈልገኛለህ፤ እኔ ግን የለሁም።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 7:1-21

1“人生在世岂不像服劳役吗?

他有生之年岂不像个雇工吗?

2他像切望阴凉的奴隶,

又如盼望报酬的雇工。

3同样,我注定要度过虚空的岁月,

熬过悲惨的黑夜。

4我躺在床上,想着何时起来。

长夜漫漫,我辗转难眠,直到拂晓。

5我身上布满蛆虫、伤疤,

皮肤破裂,流脓不止。

6我的年日飞逝,比梭还快,

转眼结束,毫无盼望。

7“上帝啊,别忘了我的生命不过是一口气,

我再也看不见幸福。

8注视我的眼睛将再也看不见我,

你将寻找我,而我已不复存在。

9人死后一去不返,

就像烟消云散;

10他永不再返回家园,

故土也不再认识他。

11“因此我不再缄默不语,

我要吐露胸中的悲愁,

倾诉心里的苦楚。

12上帝啊,我岂是大海,岂是海怪,

值得你这样防范我?

13我以为床铺是我的安慰,

卧榻可解除我的哀愁,

14你却用噩梦惊我,

用异象吓我,

15以致我宁愿窒息而死,

也不愿这样活着。

16我厌恶生命,不想永活。

不要管我,因为我的日子都是虚空。

17“人算什么,你竟这样看重他,

这样关注他?

18你天天早上察看他,

时时刻刻考验他。

19你的视线何时离开我,

给我咽口唾沫的时间?

20鉴察世人的主啊,

我若犯了罪,又于你何妨?

为何把我当成你的箭靶?

难道我成了你的重担?

21为何不赦免我的过犯,

饶恕我的罪恶?

我很快将归于尘土,

你将寻找我,

而我已不复存在。”