ኢዮብ 42 – NASV & HOF

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 42:1-17

ኢዮብ

1ኢዮብም እንዲህ ሲል ለእግዚአብሔር መለሰ፤

2“አንተ ሁሉን ማድረግ እንደምትችል፣

ዕቅድህም ከቶ እንደማይሰናከል ዐወቅሁ።

3አንተ፣ ‘ያለ ዕውቀት ዕቅዴን የሚያደበዝዝ ይህ ማን ነው?’ አልኸኝ፤

በርግጥ ያልገባኝን ነገር፣

የማላውቀውንና ላስተውለው የማልችለውን ጕዳይ ተናገርሁ።

4“ ‘ስማኝ፣ ልናገር እኔ እጠይቃለሁ፤

አንተ ትመልስልኛለህ’ አልኸኝ።

5ጆሮዬ ስለ አንተ ሰምታ ነበር፤

አሁን ግን ዐይኔ አየችህ።

6ስለዚህ ራሴን እንቃለሁ፤

በትቢያና በዐመድ ላይ ተቀምጬ ንስሓ እገባለሁ።”

መደምደሚያ

7እግዚአብሔር ይህን ለኢዮብ ከተናገረ በኋላ፣ ቴማናዊውን ኤልፋዝን እንዲህ አለው፤ “እንደ አገልጋዬ እንደ ኢዮብ ስለ እኔ ቅን ነገር ስላልተናገራችሁ፣ ቍጣዬ በአንተና በሁለቱ ባልንጀሮችህ ላይ ነድዷል። 8አሁን እንግዲህ ሰባት ወይፈኖችና ሰባት አውራ በጎች ይዛችሁ ወደ አገልጋዬ ወደ ኢዮብ ሂዱ፤ የሚቃጠል መሥዋዕትም ስለ ራሳችሁ አቅርቡ። እንደ አሳፋሪ ተግባራችሁ እንዳላደርግባችሁ አገልጋዬ ኢዮብ ስለ እናንተ ይጸልያል፤ እኔም ጸሎቱን እቀበላለሁ፤ እንደ አገልጋዬ እንደ ኢዮብ ስለ እኔ ቅን ነገር አልተናገራችሁምና።” 9ቴማናዊው ኤልፋዝ፣ ሹሐዊው በልዳዶስና ናዕማታዊው ሶፋር እግዚአብሔር እንደ ተናገራቸው አደረጉ፤ እግዚአብሔርም የኢዮብን ጸሎት ተቀበለ።

10ኢዮብ ለወዳጆቹ ከጸለየ በኋላ፣ እግዚአብሔር እንደ ገና አበለጸገው፤ ቀድሞ በነበረው ፈንታ ዕጥፍ አድርጎ ሰጠው። 11ወንድሞቹና እኅቶቹ፣ ቀድሞም ያውቁት የነበሩ ሁሉ ወደ እርሱ መጡ፤ በቤቱም ከእርሱ ጋር ምግብ በሉ። እነርሱም ሐዘናቸውን ገለጡለት፤ እግዚአብሔርም ካመጣበት መከራ ሁሉ አጽናኑት፤ እያንዳንዳቸውም ጥሬ ብርና42፥11 ዕብራይስጡ፣ ኬሊታ ይላል፤ ኬሊታ የገንዘብ ዐይነት ነው፤ ክብደቱና መጠኑ ግን በትክክል አይታወቅም። የወርቅ ቀለበት ሰጡት።

12እግዚአብሔርም ከፊተኛው ይልቅ የኋለኛውን የኢዮብን ሕይወት ባረከ። እርሱም ዐሥራ አራት ሺሕ በጎች፣ ስድስት ሺሕ ግመሎች፣ አንድ ሺሕ ጥማድ በሬዎች፣ አንድ ሺሕ እንስት አህዮችም ነበሩት። 13ደግሞም ሰባት ወንዶችና ሦስት ሴቶች ልጆች ነበሩት፤ 14የመጀመሪያዋን ይሚማ፣ ሁለተኛዋን ቃሥያ፣ ሦስተኛዋንም አማልቶያስ ቂራስ ብሎ ሰየማቸው። 15እንደ ኢዮብ ሴቶች ልጆች የተዋቡ ሴቶች በምድሪቱ ሁሉ አልተገኙም፤ አባታቸውም ከወንድሞቻቸው ጋር ርስት ሰጣቸው።

16ከዚህ በኋላ ኢዮብ አንድ መቶ አርባ ዓመት ኖረ፤ ልጆቹንና የልጅ ልጆቹን እስከ አራት ትውልድ ድረስ አየ። 17በዚህ ሁኔታ አርጅቶ፣ ዕድሜ ጠግቦ ሞተ።

Hoffnung für Alle

Hiob 42:1-17

Gott wendet Hiobs Schicksal zum Guten

(Kapitel 42)

Hiobs letztes Wort

1Da antwortete Hiob:

2»Herr, ich erkenne, dass du alles zu tun vermagst;

nichts und niemand kann deinen Plan vereiteln.

3Du hast gefragt:

›Wer bist du, dass du meine Weisheit anzweifelst

mit Worten ohne Verstand?‹

Ja, es ist wahr:

Ich habe von Dingen geredet, die ich nicht begreife,

sie sind zu hoch für mich und übersteigen meinen Verstand.

4Du hast gesagt:

›Hör mir zu, jetzt rede ich, ich will dich fragen,

und du sollst mir antworten!‹

5Herr, ich kannte dich nur vom Hörensagen,

jetzt aber habe ich dich mit eigenen Augen gesehen!

6Darum widerrufe ich meine Worte,

ich bereue in Staub und Asche!«

Gott stellt sich hinter Hiob

7Nachdem der Herr dies alles zu Hiob gesagt hatte, wandte er sich an Elifas aus Teman: »Ich bin voller Zorn über dich und deine beiden Freunde, ihr habt nicht die Wahrheit über mich gesagt, so wie mein Diener Hiob es tat! 8Bringt nun sieben junge Stiere und sieben Schafböcke, geht damit zu meinem Diener Hiob und bringt sie als Brandopfer dar! Hiob soll für euch beten, denn nur ihn will ich erhören und euch um seinetwillen nichts Böses tun. Denn ihr habt nicht wie er die Wahrheit über mich gesagt.«

9Da taten Elifas aus Teman, Bildad aus Schuach und Zofar aus Naama, was ihnen der Herr befohlen hatte. Und Gott erhörte Hiobs Gebet.

10Als Hiob für seine Freunde betete, da wendete der Herr für ihn alles zum Guten. Er gab ihm doppelt so viel, wie er früher besessen hatte. 11Alle seine Brüder und Schwestern und die früheren Bekannten besuchten ihn wieder. Sie aßen mit ihm in seinem Haus und trösteten ihn wegen des Unglücks, das der Herr über ihn gebracht hatte. Jeder schenkte ihm ein Silberstück und einen Ring aus Gold.

12Der Herr segnete Hiob von jetzt an mehr als zuvor. Bald besaß er 14.000 Schafe und Ziegen, 6000 Kamele, 1000 Rindergespanne und 1000 Esel. 13Er bekam auch wieder sieben Söhne und drei Töchter. 14Die erste nannte er Jemima (»Täubchen«), die zweite Kezia (»Zimtblüte«) und die dritte Keren-Happuch (»Schminkdöschen«). 15Im ganzen Land gab es keine schöneren Frauen als Hiobs Töchter; sie durften mit ihren Brüdern das Erbe teilen.

16Hiob lebte noch 140 Jahre, er sah Kinder und Enkel bis in die vierte Generation. 17Schließlich starb er in hohem Alter nach einem reichen und erfüllten Leben.