ኢዮብ 4 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 4:1-21

ኤልፋዝ

1ቴማናዊው ኤልፋዝም እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“አንድ ሰው ከአንተ ጋር ለመናገር ቢሞክር፣ ቅር ይልሃልን?

ዳሩ ግን ከመናገር ማን ሊቈጠብ ይችላል?

3እነሆ፤ አንተ ብዙዎችን ታስተምር እንደ ነበር ዐስብ፤

የደከሙትንም እጆች ታበረታ ነበር፤

4ቃልህ የተሰናከሉትን ያነሣ ነበር፤

የሚብረከረከውንም ጕልበት ታጸና ነበር።

5አሁን ግን መከራ አገኘህ፣ አንተም ተስፋ ቈረጥህ፤

ሸነቈጠህ፤ ደነገጥህም።

6እግዚአብሔርን መፍራት መታመኛህ፣

ቀና አካሄድህም ተስፋህ አይደለምን?

7“አሁንም አስተውል፤ ንጹሕ ሆኖ የጠፋ ማን ነው?

ቅኖችስ መች ተደምስሰው ያውቃሉ?

8እኔ እንዳየሁ ክፋትን የሚያርሱ፣

መከራንም የሚዘሩ ያንኑ ያጭዳሉ።

9በእግዚአብሔር እስትንፋስ ይጠፋሉ፤

በቍጣውም ወላፈን ይደመሰሳሉ።

10አንበሳ ያገሣል፤ ቍጡውም አንበሳ ይጮኻል፤

የደቦል አንበሳው ጥርስ ግን ተሰብሯል።

11ብርቱው አንበሳ ዐደን በማጣት ይሞታል፤

የአንበሳዪቱም ግልገሎች ይበተናሉ።

12“ቃል በምስጢር መጣልኝ፤

ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች።

13በሚያስጨንቅ የሌሊት ሕልም ውስጥ፣

ከባድ እንቅልፍም በሰዎች ላይ በወደቀ ጊዜ፣

14ፍርሀትና መንቀጥቀጥ ያዘኝ፤

ዐጥንቶቼም ሁሉ ተናወጡ።

15መንፈስ ሽው ብሎ በፊቴ ዐለፈ፤

የገላዬም ጠጕር ቆመ።

16እርሱም ቆመ፣

ምን እንደ ሆነ ግን መለየት አልቻልሁም፤

አንድ ቅርጽ በዐይኔ ፊት ነበረ፤

በእርጭታ ውስጥ እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ፤

17‘ሥጋ ለባሽ ከእግዚአብሔር ይልቅ ጻድቅ ሊሆን ይችላልን?

ሰውስ ከፈጣሪው ይልቅ ንጹሕ ሊሆን ይችላልን?

18እግዚአብሔር በአገልጋዮቹ ላይ እምነት ካልጣለ፣

መላእክቱንም በስሕተታቸው ከወቀሠ፣

19ይልቁንስ በጭቃ ቤት የሚኖሩ፣

መሠረታቸው ከዐፈር የሆነ፣

ከብልም ይልቅ በቀላሉ የሚጨፈለቁ እንዴት ይሆኑ?

20በንጋትና በምሽት መካከል ይደቅቃሉ፤

ሳይታሰብም ለዘላለም ይጠፋሉ።

21ያለ ጥበብ ይሞቱ ዘንድ፣

የድንኳናቸው ገመድ አልተነቀለምን?’

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 4:1-21

以利法的责难

1提幔以利法回答说:

2“若有人向你进言,

你会厌烦吗?

可是,谁能忍住不说呢?

3你曾教导许多人,

使无力的手强壮。

4你的话使人免于跌倒,

你使颤抖的膝硬朗。

5但现在苦难一来,

你便灰心丧胆;

灾祸来临,

你便惊慌失措。

6你敬畏上帝还没有信心吗?

你行为纯全还没有盼望吗?

7你想一想,

哪有无辜的人灭亡?

哪有正直的人遭殃?

8据我所见,

播恶收恶,

种祸得祸。

9他们被上帝的气息所毁,

被上帝的怒气所灭。

10狮子咆哮,猛狮吼叫,

壮狮的牙齿被敲掉。

11雄狮因无食而死,

母狮的幼崽离散。

12“有信息暗暗地传给我,

一声低语传入我耳中。

13夜间人们沉睡的时候,

在搅扰思绪的异象中,

14恐惧袭来,

令我战栗不已,

全身发抖。

15有灵从我脸上拂过,

使我毛骨悚然。

16那灵停住,

我无法辨认其模样。

眼前出现一个形状,

寂静中听见有声音说,

17‘在上帝面前,世人岂算得上公义?

在创造主面前,凡人岂算得上纯洁?

18连上帝的仆人都无法令祂信任,

连祂的天使都被祂找出过错,

19更何况源自尘土、

住在土造的躯壳里、

脆弱如蛾的世人呢?

20早晚之间,他们便被毁灭,

永远消逝,无人察觉。

21他们帐篷的绳索被拔起,

他们毫无智慧地死去。’