ኢዮብ 38 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 38:1-41

እግዚአብሔር ተናገረ

1እግዚአብሔርም በዐውሎ ነፋስ ውስጥ ሆኖ ለኢዮብ መለሰለት፤ እንዲህም አለው፤

2“ዕውቀት በጐደለው ቃል፣

ዕቅዴን የሚያጨልም ይህ ማን ነው?

3እስቲ እንደ ወንድ ወገብህን ታጠቅ፤

እኔ ልጠይቅህ፣

አንተም መልስልኝ።

4“ምድርን በመሠረትሁ ጊዜ አንተ የት ነበርህ?

በርግጥ የምታስተውል ከሆንህ ንገረኝ።

5ካወቅህ፣ መጠኗን ለይቶ ማን ወሰነ?

በላይዋስ መለኪያ ገመድ የዘረጋ ማን ነው?

6መሠረቶቿ ምን ላይ ተተከሉ?

የማእዘን ድንጋይዋንስ ማን አቆመ?

7ይህም የሆነው የንጋት ከዋክብት በዘመሩበት ጊዜ፣

መላእክትም38፥7 ወይም፣ የእግዚአብሔር ልጆች እልል ባሉበት ጊዜ ነበር።

8“ባሕር ከማሕፀን በወጣ ጊዜ፣

በር የዘጋበት ማን ነው?

9ደመናውን ልብሱ፣

ጨለማንም መጠቅለያው አደረግሁለት፣

10ድንበር ወሰንሁለት፤

መዝጊያና መወርወሪያውን አበጀሁለት።

11‘እስከዚህ ድረስ ትመጣለህ፤ ማለፍ ግን አትችልም፤

የዕቡይ ማዕበልህም ገደብ ይህ ነው’ አልሁት።

12“ከተወለድህ ጀምሮ ንጋትን አዝዘህ ታውቃለህን?

ወይስ ወጋገን ስፍራውን እንዲይዝ አድርገሃል?

13በዚህም የምድርን ዳርቻ ይዞ፣

ክፉዎችን ከላይዋ እንዲያራግፍ አድርገሃልን?

14ምድር ከማኅተም በታች እንዳለ የሸክላ ጭቃ ቅርጿ ይወጣል፤

ቅርጿ እንደ ልብስ ቅርጽ ጐልቶ ይታያል።

15ክፉዎች ብርሃናቸውን ተከልክለዋል፤

ከፍ ያለው ክንዳቸውም ተሰብሯል።

16“ወደ ባሕር ምንጭ ወርደህ ታውቃለህን?

ወይስ ወደ ጥልቀቱ ገብተህ በመሠረቱ ላይ ተመላልሰሃልን?

17የሞት ደጆች ተገልጠውልሃልን?

የሞትንስ ጥላ በሮች አይተሃልን?

18የምድርን ስፋት ታውቃለህን?

ይህን ሁሉ ዐውቀህ ከሆነ፣ ንገረኝ።

19“ወደ ብርሃን መኖሪያ የሚያደርሰው መንገድ የትኛው ነው?

የጨለማ መኖሪያስ ወዴት ነው?

20ወደ ማደሪያቸው ልትወስዳቸው ትችላለህን?

የመኖሪያቸውን መንገድ ታውቃለህ?

21ያን ጊዜ ተወልደሃል! ዕድሜህ ትልቅ ነውና፣

አንተስ በርግጥ ሳታውቅ አትቀርም!

22“ወደ በረዶው መጋዘን ገብተሃልን?

የዐመዳዩንስ ማከማቻ አይተሃልን?

23ይኸውም ለመከራ ጊዜ፣

ለጦርነትና ለውጊያ ቀን ያስቀመጥሁት ነው።

24መብረቅ ወደሚሠራጭበት ቦታ የሚያደርሰው መንገድ፣

የምሥራቅም ነፋስ በምድር ላይ ወደሚበተንበት ስፍራ የሚወስደው የትኛው ነው?

25ለዝናብ መውረጃን፣

ለመብረቅም መንገድን ያበጀ ማን ነው?

26በዚህም ማንም የማይኖርበትን ምድር፣

ሰውም የሌለበትን ምድረ በዳ የሚያጠጣ፣

27ባድማውንና በረሓውን መሬት የሚያጠግብ፣

ሣርም እንዲበቅልበት የሚያደርግ ማን ነው?

28ዝናብ አባት አለውን?

የጤዛን ጠብታ ማን ወለደው?

29በረዶ ከማን ማሕፀን ይወጣል?

የሰማዩንስ ዐመዳይ ማን ይወልዳል?

30ውሆች እንደ ድንጋይ ይጠነክራሉ፤

የጥልቁ ገጽ እንደ በረዶ ይጋገራል።

31“ፕልያዲስ የተባሉትን ውብ ከዋክብት ልትለጕም፣

ወይም የኦርዮንን ማሰሪያ ልትፈታ ትችላለህን?

32ማዛሮት የተባለውን የከዋክብት ክምችት በወቅቱ38፥32 ወይም በወቅቱ የሚወጣ የንጋት ኮከብ ልታወጣ፣

ወይም ድብ የተባለውን ኮከብና ልጆቹን ልትመራ ትችላለህ?

33የሰማያትን ሥርዐት ታውቃለህ?

ይህንስ በምድር ላይ እንዲሠለጥን ማድረግ ትችላለህ?

34“ድምፅህን ወደ ደመናት አንሥተህ፣

ራስህን በጐርፍ ማጥለቅለቅ ትችላለህን?

35መብረቆችን መስደድ ትችላለህ?

እነርሱስ፣ ‘እነሆ፤ እዚህ አለን’ ይሉሃል?

36ለልብ38፥36 በዕብራይስጡ የዚህ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ጥበብን፣

ለአእምሮም ማስተዋልን የሰጠ ማን ነው?

37ትቢያ ሲጠጥር፣

ጓሎችም እርስ በርስ ሲጣበቁ፣

38ደመናትን ለመቍጠር ጥበብ ያለው ማን ነው?

የሰማያትንስ የውሃ ገንቦ ዘንበል ማድረግ ማን ይችላል?

39“ለአንበሳዪቱ ዐድነህ ግዳይ ታመጣለህን?

የተራቡ የአንበሳ ግልገሎችንስ ታጠግባለህን?

40እነርሱ በዋሻ ውስጥ ያደባሉ፤

በደን ውስጥም ይጋደማሉ።

41ልጆቿ ወደ እግዚአብሔር ሲጮኹ፣

ምግብ ዐጥተው ሲንከራተቱ፣

ለቍራ መብልን የሚሰጥ ማን ነው?

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 38:1-41

耶和华回答约伯

1那时,耶和华从旋风中回答约伯说:

2“是谁用无知的话蒙蔽我的旨意?

3你要像勇士一样束腰备战,

我来提问,你来回答。

4“我立大地根基的时候,你在哪里?

你若那么聪明,请告诉我。

5你可知道谁为大地定的尺寸?

谁用准绳把它丈量?

6是什么支撑大地的根基?

谁为它安放的基石?

7当时晨星齐声歌唱,

众天使都发出欢呼。

8“大海从母胎奔腾而出时,

谁为它划定界限?

9是我为大海披上云彩,

为它裹上厚厚的幽暗。

10是我为它划定界限,

并安上门和闩,

11说,‘你到此为止,不可越界;

你狂傲的波涛要停在这里。’

12“你生平可曾向晨曦发号施令,

为黎明的曙光指定岗位,

13使阳光普照大地,

抖出藏匿的恶人?

14日光使大地改观,如泥上盖印,

万物如衣服般显出颜色。

15恶人得不到光明,

强横的臂膀必折断。

16你可曾到过大海的源头,

走过深渊的底部?

17死亡之门可曾向你显露?

你可曾见过幽冥之门?

18你知道大地有多广阔吗?

你若知道,就告诉我吧。

19“哪条路通往光明的居所?

哪里是黑暗的住处?

20你能把它们带回原处吗?

你认识通往其居所的路吗?

21你肯定知道,

因为那时你已出生,

你的寿数又很长久!

22“你曾到过雪库,

或见过雹仓吗?

23那是我为降灾之时,

为争战之日而预备的。

24光从哪条路散开?

东风从哪条路吹向大地?

25谁为豪雨开水道,

为雷电辟路径,

26使雨水降在杳无人烟之地,

降在无人居住的旷野,

27以滋润荒凉不毛之地,

使土地长出青草?

28雨水有父亲吗?

谁生的露珠?

29冰出自谁的胎?

谁生的天上的霜?

30水变得坚硬如石,

深渊表面凝结成冰。

31“你能系住昴星的结,

解开参星的带吗?

32你能按季节领出星座,

引导北斗及其众星吗?

33你知道天的定律吗?

你能使地服从天律吗?

34你能号令云彩,

使倾盆大雨覆盖你吗?

35你能命闪电发出,

让它听候调遣吗?

36谁将智慧放在人胸中?

谁使人内心有聪明?

37-38尘土结成硬团,

土块黏在一起时,

谁能凭智慧数算云彩?

谁能倾倒天上的水囊?

39-40“狮子卧在洞中,

壮狮埋伏在隐秘处,

你能为它们猎取食物,

使它们饱餐吗?

41乌鸦的幼雏饿得飞来飞去,

向上帝哀鸣时,

谁供应乌鸦食物?