ኢዮብ 37 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 37:1-24

1“ልቤ በዚህ በኀይል ይመታል፤

ከስፍራውም ዘለል ዘለል ይላል።

2ስሙ! የድምፁን ጩኸት ስሙ፤

ከአፉ የሚወጣውን ጕርምርምታ አድምጡ።

3መብረቁን ከሰማይ ሁሉ በታች ያባርቃል፤

ወደ ምድርም ዳርቻ ይልካል።

4ከዚያም በኋላ የድምፁ ጩኸት ይመጣል፤

በድምፁም ግርማ ያንጐደጕዳል፤

ድምፁ በተሰማ ጊዜ፣

መብረቁን የሚከለክል የለም።

5የእግዚአብሔር ድምፅ በሚያስደንቅ ሁኔታ ያንጐደጕዳል፤

እኛ የማናስተውለውንም ታላቅ ነገር ያደርጋል።

6በረዶውን፣ ‘በምድር ላይ ውደቅ’

ውሽንፍሩንም ‘ዶፍህን አውርደው’ ይላል።

7እርሱ የፈጠራቸው ሰዎች ሁሉ ሥራውን ያውቁ ዘንድ፣

እያንዳንዱ ሰው እንዳይሠራ ይገታዋል።37፥7 ወይም፣ ሰዎችን ሁሉ በኀይሉ ያስፈራቸዋል ማለትም ነው።

8እንስሳት ይጠለላሉ፤

በየዋሻቸውም ይቈያሉ።

9ዐውሎ ነፋስ ከማደሪያው፣

ብርድም ከብርቱ ነፋስ ይወጣል።

10የእግዚአብሔር እስትንፋስ በረዶ ያስገኛል፤

ሰፋፊ ውሆች ግግር በረዶ ይሆናሉ።

11ደመናትን ርጥበት ያሸክማቸዋል፤

መብረቁንም በውስጣቸው ይበትናል።

12ያዘዘውን ለመፈጸም፣

እርሱ በሚሰጠው መመሪያ፣

በመላው የምድር ገጽ ላይ ይሽከረከራሉ።

13ሰዎችን ለመቅጣት ደመና ያመጣል፤

ወይም በዚሁ ምድሩን አጠጥቶ37፥13 ወይም፣ ፍቅሩንም ለመግለጽ ደመናን ያመጣል ፍቅሩን ይገልጻል።

14“ኢዮብ ሆይ፤ ይህን ስማ፤

ቆም ብለህ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ዐስብ።

15እግዚአብሔር ደመናትን እንዴት እንደሚቈጣጠር፣

መብረቁንም እንዴት እንደሚያባርቅ ታውቃለህን?

16ደመናት ሚዛን ጠብቀው እንዴት እንደሚንሳፈፉ፣

በዕውቀቱ ፍጹም የሆነውን፣ የእርሱን ድንቅ ሥራ ታውቃለህን?

17ምድር በደቡብ ነፋስ ጸጥ ባለች ጊዜ፣

ከሙቀት የተነሣ በልብስህ ውስጥ የምትዝለፈለፍ ሆይ፤

18ከቀለጠ ናስ እንደ ተሠራ መስተዋት የጠነከረውን ሰማይ ሲዘረጋ፣

አብረኸው መዘርጋት ትችል ነበርን?

19“ከጨለማችን የተነሣ እኛ ጕዳያችንን መግለጽ አንችልም፤

ለእርሱ የምንለውን ንገረን።

20እኔ መናገር እንደ ፈለግሁ ሊነገረው ይገባልን?

ይዋጥ ዘንድ የሚጠይቅ ሰው አለን?

21እንግዲህ ነፋስ ሰማያትን ካጠራ በኋላ፣

እጅግ የምታበራዋን ፀሓይ፣

ሊመለከት የሚችል የለም።

22እንደ ወርቅ በሚያበራ ክብር ከሰሜን ይወጣል፤

እግዚአብሔር በሚያስፈራ ግርማ ይመጣል።

23ሁሉን የሚችል አምላክ ከአእምሯችን በላይ ነው፤ በኀይልና በፍርድ ታላቅ ነው፣

ጽድቁም ብዙ ነው፤ ማንንም አይጨቍንም።

24ስለዚህ፣ ሰዎች ይፈሩታል፤

በልባቸው37፥24 ወይም፣ በልባቸው አስተዋዮች ወደ ሆኑ አስተዋዮች እንደ ሆኑ የሚያስቡትን አይመለከትም?”

Japanese Contemporary Bible

ヨブ 記 37:1-24

37

1私の心はおののく。

2神の声である雷の音を聞け。

3雷が天を渡って来ると、

いなずまの閃光が四方八方に散る。

4そのあとで、耳をつんざくような雷鳴がとどろく。

神の威厳を告げ知らせているのだ。

5雷鳴は神の声に栄光を添える。

神の力の偉大さは測り知れない。

6神が雪や夕立や豪雨を地上に降らせると、

7すべての人は仕事の手を休め、神の力を認める。

8野獣は岩間やほら穴に避難する。

9雨は南から、寒さは北から来る。

10神が川の上に息を吹きかけると、

急流でさえ凍りつく。

11神が雲に水分を含ませると、

雲はいなずまをまき散らす。

12いなずまは神の命令どおり、地を行き巡る。

13神が嵐を起こすのは懲らしめのため、

また、いつくしみで人々を元気づけるためだ。

14ヨブさん、あなたには、神のすばらしい奇跡を

じっくり考えてもらいたい。

15あなたは、どのようにして神が自然界を支配し、

雲間にいなずまをひらめかすのか知っているだろうか。

16-17雲は完全な調和をもって見事につり合っているし、

南風が吹くと暑くなる。

いったいどうしてそうなるのか、知っているだろうか。

18あなたは神のように、

途方もなく大きな鏡のような空を

張り広げることができるだろうか。

19-20自分には豊富な知識があると考える人がいたら、

神に近づく方法を教えてもらいたい。

私たちはあまりにも鈍く、

何もわかっていないからだ。

はて、そんな知識で神に近づけるだろうか。

生きたままのみ込まれてもよいというのか。

21風が雲を吹き払うと、まぶしくて

太陽をまともに見ることができないように、

22天の切れ間から差し込む、

目のくらむような輝きを放つ

神の威厳を見つめることは不可能だ。

23全能者の力を推し量ることはできない。

しかし、神はこの上なく正しく、

思いやりにあふれているので、私たちを滅ぼさない。

24人々が神を恐れるのは不思議ではない。

世界最高の賢者も、

神を感心させることなどできないのだから。」