ኢዮብ 37 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 37:1-24

1“ልቤ በዚህ በኀይል ይመታል፤

ከስፍራውም ዘለል ዘለል ይላል።

2ስሙ! የድምፁን ጩኸት ስሙ፤

ከአፉ የሚወጣውን ጕርምርምታ አድምጡ።

3መብረቁን ከሰማይ ሁሉ በታች ያባርቃል፤

ወደ ምድርም ዳርቻ ይልካል።

4ከዚያም በኋላ የድምፁ ጩኸት ይመጣል፤

በድምፁም ግርማ ያንጐደጕዳል፤

ድምፁ በተሰማ ጊዜ፣

መብረቁን የሚከለክል የለም።

5የእግዚአብሔር ድምፅ በሚያስደንቅ ሁኔታ ያንጐደጕዳል፤

እኛ የማናስተውለውንም ታላቅ ነገር ያደርጋል።

6በረዶውን፣ ‘በምድር ላይ ውደቅ’

ውሽንፍሩንም ‘ዶፍህን አውርደው’ ይላል።

7እርሱ የፈጠራቸው ሰዎች ሁሉ ሥራውን ያውቁ ዘንድ፣

እያንዳንዱ ሰው እንዳይሠራ ይገታዋል።37፥7 ወይም፣ ሰዎችን ሁሉ በኀይሉ ያስፈራቸዋል ማለትም ነው።

8እንስሳት ይጠለላሉ፤

በየዋሻቸውም ይቈያሉ።

9ዐውሎ ነፋስ ከማደሪያው፣

ብርድም ከብርቱ ነፋስ ይወጣል።

10የእግዚአብሔር እስትንፋስ በረዶ ያስገኛል፤

ሰፋፊ ውሆች ግግር በረዶ ይሆናሉ።

11ደመናትን ርጥበት ያሸክማቸዋል፤

መብረቁንም በውስጣቸው ይበትናል።

12ያዘዘውን ለመፈጸም፣

እርሱ በሚሰጠው መመሪያ፣

በመላው የምድር ገጽ ላይ ይሽከረከራሉ።

13ሰዎችን ለመቅጣት ደመና ያመጣል፤

ወይም በዚሁ ምድሩን አጠጥቶ37፥13 ወይም፣ ፍቅሩንም ለመግለጽ ደመናን ያመጣል ፍቅሩን ይገልጻል።

14“ኢዮብ ሆይ፤ ይህን ስማ፤

ቆም ብለህ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ዐስብ።

15እግዚአብሔር ደመናትን እንዴት እንደሚቈጣጠር፣

መብረቁንም እንዴት እንደሚያባርቅ ታውቃለህን?

16ደመናት ሚዛን ጠብቀው እንዴት እንደሚንሳፈፉ፣

በዕውቀቱ ፍጹም የሆነውን፣ የእርሱን ድንቅ ሥራ ታውቃለህን?

17ምድር በደቡብ ነፋስ ጸጥ ባለች ጊዜ፣

ከሙቀት የተነሣ በልብስህ ውስጥ የምትዝለፈለፍ ሆይ፤

18ከቀለጠ ናስ እንደ ተሠራ መስተዋት የጠነከረውን ሰማይ ሲዘረጋ፣

አብረኸው መዘርጋት ትችል ነበርን?

19“ከጨለማችን የተነሣ እኛ ጕዳያችንን መግለጽ አንችልም፤

ለእርሱ የምንለውን ንገረን።

20እኔ መናገር እንደ ፈለግሁ ሊነገረው ይገባልን?

ይዋጥ ዘንድ የሚጠይቅ ሰው አለን?

21እንግዲህ ነፋስ ሰማያትን ካጠራ በኋላ፣

እጅግ የምታበራዋን ፀሓይ፣

ሊመለከት የሚችል የለም።

22እንደ ወርቅ በሚያበራ ክብር ከሰሜን ይወጣል፤

እግዚአብሔር በሚያስፈራ ግርማ ይመጣል።

23ሁሉን የሚችል አምላክ ከአእምሯችን በላይ ነው፤ በኀይልና በፍርድ ታላቅ ነው፣

ጽድቁም ብዙ ነው፤ ማንንም አይጨቍንም።

24ስለዚህ፣ ሰዎች ይፈሩታል፤

በልባቸው37፥24 ወይም፣ በልባቸው አስተዋዮች ወደ ሆኑ አስተዋዮች እንደ ሆኑ የሚያስቡትን አይመለከትም?”

Het Boek

Job 37:1-24

Elihu wijst op Gods wonderen

1Vervolg van het betoog van Elihu:

‘Daarom ben ik vervuld van ontzag.

2Luister goed naar de donder van zijn stem.

3Hij rolt langs de hemel en de bliksemschichten schieten naar alle kanten van de aarde.

4Zij worden gevolgd door het onophoudelijke dreunen van de donder, de ontzagwekkende stem van zijn majesteit.

5Zijn stem klinkt op een geweldige manier door in de donder. Wij kunnen de omvang van zijn macht niet bevatten.

6Want Hij geeft sneeuw en regen opdracht om op de aarde te vallen.

7Dan ligt al het menselijke werk stil, zodat men overal zijn macht kan zien.

8De wilde dieren verbergen zich tussen de rotsen of in hun holen.

9De storm komt op vanuit het zuiden en vanuit het noorden komt de kou.

10God blaast over de rivieren en zelfs de grootste wateroppervlaktes bevriezen.

11Hij laadt de wolken met waterdamp en uit diezelfde wolken komt zijn bliksem.

12Hij stuurt de bliksemschichten met zijn hand en overal op aarde doen zij wat Hij beveelt.

13Hij stuurt de wolken als straf of—in zijn liefdevolle goedheid—als bemoediging voor de mensen.

14Luister, Job, sta stil en kijk naar de machtige wonderen van God!

15Weet u hoe God de wolken in de hand houdt en hoe Hij de bliksem daaruit tevoorschijn laat schieten?

16Begrijpt u hoe de wolken zo volmaakt kunnen zweven? Het is het wonderlijke werk van de Alwetende.

17Weet u waarom u het warm krijgt wanneer de wind uit het zuiden komt en het zulk rustig weer is?

18Kunt u zoals Hij de hemelkoepel maken, die zo hard is als een gegoten spiegel?

19-20 Als u denkt dat u zoveel weet, leer ons dan hoe wij tot God kunnen naderen. Want wij kunnen daar niet achter komen! Zouden wij Hem zo kunnen mededelen dat ik Hem wil spreken? Wil een mens levend worden opgeslokt?

21Want net zo min als wij in de zon kunnen kijken wanneer de wind alle wolken uit de lucht heeft weggedreven,

22zo min kunnen wij het oog richten op de ontzagwekkende majesteit van God, als Hij Zich vanuit de hemel over ons uitstort, gehuld in zijn duizelingwekkende pracht.

23Wij kunnen ons geen voorstelling maken van de macht van de Almachtige. Hij is zo rechtvaardig en goed dat Hij niemand zal onderdrukken.

24Geen wonder dat mensen overal ter wereld ontzag voor Hem hebben! Want zelfs de meest wijze man ter aarde maakt totaal geen indruk op Hem!’