ኢዮብ 36 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 36:1-33

1ኤሊሁ በመቀጠል እንዲህ አለ፤

2“በእግዚአብሔር ፈንታ ሆኜ የምለው አለኝ፤

ጥቂት ታገሠኝና እነግርሃለሁ።

3ዕውቀቴን ከሩቅ አመጣለሁ፤

ፈጣሪዬ ጻድቅ እንደ ሆነ እገልጻለሁ።

4ቃሌ ሐሰት እንዳልሆነ አረጋግጣለሁ፤

በዕውቀቱ ፍጹም የሆነ ሰው ከአንተ ጋር ነው።

5“እግዚአብሔር ኀያል ነው፤ ግን ማንንም አይንቅም፤

ኀያል፣ በዐላማውም ጽኑ ነው።

6ክፉዎችን በሕይወት አያኖርም፤

ለተቸገሩት ግን በቅን ይፈርዳል።

7ዐይኖቹን ከጻድቃን ላይ አያነሣም፤

ከነገሥታት ጋር በዙፋን ላይ ያስቀምጣቸዋል፤

ለዘላለምም ከፍ ከፍ ያደርጋቸዋል።

8ነገር ግን ሰዎች በሰንሰለት ቢታሰሩ፣

በመከራም ገመድ ቢጠፈሩ፣

9በእብሪት የፈጸሙትን በደል፣

ተግባራቸውን ይነግራቸዋል።

10ተግሣጽን እንዲሰሙ ያደርጋቸዋል፤

ከክፋታቸውም እንዲመለሱ ያዝዛቸዋል።

11ታዝዘው ቢያገለግሉት፣

ቀሪ ዘመናቸውን በተድላ፣

ዕድሜያቸውንም በርካታ ይፈጽማሉ።

12ባይሰሙ ግን፣

በሰይፍ36፥12 ወይም፣ ወንዙን ያቋርጣሉ ይጠፋሉ፤

ያለ ዕውቀትም ይሞታሉ።

13“ልባቸው ከእግዚአብሔር የራቀ፣ ቍጣን ያስተናግዳሉ፤

በሰንሰለት ባሰራቸውም ጊዜ እንኳ ወደ እርሱ አይጮኹም።

14በቤተ ጣዖት ውስጥ ዝሙት በሚፈጽሙት መካከል፣

ገና በወጣትነታቸው ይቀጫሉ።

15ነገር ግን የሚሠቃዩትን ከሥቃያቸው ያድናቸዋል፤

በመከራቸውም ውስጥ ይናገራቸዋል።

16“አንተንም ከመከራ መንጋጋ፣

ጭንቀት ወደሌለበት ወደ ሰፊ ስፍራ፣

ምርጥ ምግብ ወደ ሞላበት ማእድ ያወጣሃል።

17አሁን ግን ለክፉዎች የሚገባው ፍርድ በላይህ ተጭኗል፤

ፍርድና ብይን ይዘውሃል።

18ባለጠግነት እንዳያታልልህ፣

የእጅ መንሻ ብዛትም እንዳያስትህ ተጠንቀቅ።

19ባለጠግነትህም ሆነ ብርቱ ጥረትህ ሁሉ፣

ችግር ውስጥ እንዳትገባ ሊረዳህ ይችላልን?

20ሰዎች ከቤታቸው36፥20 በዕብራይስጥ ከ18-20 ያለው ክፍል ትርጕሙ በትክክል አይታወቅም። የሚወሰዱበትን፣

ሌሊት አትመኝ።

21ከመከራ ይልቅ መርጠኸዋልና፣

ወደ ክፋት እንዳትመለስ ተጠንቀቅ።

22“እነሆ፤ እግዚአብሔር በኀይሉ ከፍ ከፍ ብሏል፤

እንደ እርሱስ ያለ አስተማሪ ማን ነው?

23እርሱን መንገድ የሚመራው፣

ወይም ‘ይህን አጥፍተሃል’ የሚለው ማን ነው?

24ሰዎች በመዝሙር ያወደሱትን፣

የእርሱን ሥራ ማወደስ አትዘንጋ።

25ሰው ሁሉ አይቶታል፤

ሰዎችም በትኵረት ተመልክተውታል።

26እነሆ፤ እግዚአብሔር ከአእምሯችን በላይ ታላቅ ነው!

የዘመኑም ቍጥር ከመታወቅ ያልፋል።

27“የውሃን ነጠብጣብ ወደ ላይ ያተንናል፤

መልሶም በዝናብ መልክ በጅረቶች ላይ ያወርዳል፤

28ደመናት ጠል ያንጠባጥባሉ፤

ዶፍም በሰው ላይ ይወርዳል።

29ደመናትን እንዴት እንደሚዘረጋ፣

ከድንኳኑም እንዴት እንደሚያንጐደጕድ ሊረዳ የሚችል ማን ነው?

30መብረቁን በዙሪያው እንዴት እንደሚበትን ተመልከት፤

የባሕሩንም ወለል ይሸፍናል።

31እርሱ ሕዝብን የሚያስተዳድረው፣36፥31 ወይም፣ የሚያስተዳድረው ምግብንም አትረፍርፎ የሚሰጣቸው

በዚህ መንገድ ነው።

32እጆቹን በመብረቅ ይሞላቸዋል፤

ዒላማውንም እንዲመታ ያዝዘዋል።

33ነጐድጓዱ ውሽንፍር እንደሚከተለው ያመለክታል፤

ከብቶችም እንኳ መምጣቱን ይጠቍማሉ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約伯記 36:1-33

1以利戶又說:

2「再給我片刻,容我講明,

我還有話替上帝說。

3我要旁徵博引,

證明我的創造主公義。

4我的話絕非虛言,

知識全備者在你身旁。

5「上帝有大能,但不藐視人,

祂無所不知。

6祂不容惡人活命,

祂為窮苦人伸冤。

7祂時時看顧義人,

使他們與君王同坐寶座,

永遠受尊崇。

8他們若被鎖鏈捆綁,

被苦難的繩索纏住,

9祂就會指明他們的所作所為,

讓他們知道自己狂妄的罪愆。

10祂開啟他們的耳朵,使之受教,

督促他們離開罪惡。

11他們若聽從、事奉祂,

就可一生幸福,安享天年。

12否則,他們必死於刀下,

在無知中滅亡。

13不信上帝的人心存憤怒,

被上帝捆綁也不求救。

14他們盛年喪命,

與廟中的男妓一同夭亡。

15上帝藉苦難拯救受苦的人,

藉患難開通他們的耳朵。

16祂也要引領你脫離困境,

進入廣闊自由之地,

使你享受滿桌佳餚。

17「但惡人應受的審判落在你身上,

你難逃審判和懲罰。

18當心,不可因憤怒而嘲罵,

不可因贖金大就偏離正道。

19難道你呼求、使出渾身力氣,

就能脫離困境嗎?

20不要渴望黑夜來臨——

就是眾民被毀滅的時候。

21當心,不可轉向罪惡,

因你喜歡罪惡勝於苦難。

22看啊,上帝的能力無以倫比。

誰能像祂那樣賜人教誨?

23誰能為祂指定道路?

誰能說祂行事不義?

24人們都歌唱祂的作為,

你也要記得頌揚。

25祂的作為,萬民都已看見,

世人從遠處目睹。

26我們無法明白上帝的偉大,

祂的年歲無法數算。

27祂吸取水滴,

使之在雲霧中化為雨,

28從雲端沛然降下,

滋潤人間。

29誰能明白雲層的鋪展,

及祂幔幕發出的雷聲?

30祂在四圍鋪展閃電,

照亮大海的深處。

31祂藉此治理萬民,

賜下豐富的食物。

32祂手握閃電,

令它射向目標。

33雷聲顯明祂的作為,

就連牲畜也能察覺。