ኢዮብ 33 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 33:1-33

1“አሁን ግን ኢዮብ ሆይ፣ ንግግሬን ስማ፤

የምለውንም ሁሉ አድምጥ።

2እንግዲህ አፌን እከፍታለሁ፤

አንደበቴም ይናገራል።

3ቃሌ ከቅን ልብ ይወጣል፤

ከንፈሬም የማውቀውን በትክክል ይናገራል።

4የእግዚአብሔር መንፈስ ፈጥሮኛል፤

ሁሉን የሚችለውም አምላክ እስትንፋስ ሕይወት ሰጥቶኛል።

5የምትችል ከሆነ መልስልኝ፤

ተዘጋጅተህም በፊቴ ቁም።

6በእግዚአብሔር ፊት እኔም እንደ አንተው ነኝ፤

የተፈጠርሁትም ደግሞ ከዐፈር ነው።

7እኔን መፍራት የለብህም፤

እጄም ሊከብድብህ አይገባም።

8“በርግጥ የተናገርኸውን ሰምቻለሁ፤

እንዲህም ስትል አድምጫለሁ፤

9‘ኀጢአት የሌለብኝ ንጹሕ ነኝ፤

ከበደል ነጻ ነኝ፤ እድፈትም የለብኝም፤

10እግዚአብሔር ግን ሰበብ ፈልጎብኛል፤

እንደ ጠላቱም ቈጥሮኛል፤

11እግሬን በግንድ አጣብቋል፤

እንቅስቃሴዬንም ሁሉ ይከታተላል።’

12“ነገር ግን እግዚአብሔር ከሰው ስለሚበልጥ፣

ትክክል እንዳልሆንህ እነግርሃለሁ።

13የሰውን አቤቱታ33፥13 ወይም፣ ለምግባሩ ምንም እንደማይመልስ እንደማይሰማ፣

ለምን ታማርርበታለህ?

14ሰው ባያስተውለውም፣

እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፤

15ሰዎች ዐልጋቸው ላይ ተኝተው ሳሉ፣

ከባድ እንቅልፍ ሲወድቅባቸው፣

በሕልም፣ በሌሊትም ራእይ ይናገራል።

16በጆሯቸው ይናገራል፤

በማስጠንቀቂያም ያስደነግጣቸዋል፤

17ሰውን ከክፉ ሥራው ይመልሳል፤

ከትዕቢት ይጠብቃል፤

18ነፍሱን ከጕድጓድ፤33፥18 ወይም፣ ነፍሱን ከመቃብር

ሕይወቱንም ከሰይፍ33፥18 ወይም፣ ወንዝን ከመሻገር ጥፋት ያድናል።

19ደግሞም ሰው ታምሞ በዐልጋው ላይ ሳለ፣

በዐጥንቱ የዘወትር ሥቃይ ይገሥጸዋል፤

20ያኔም ሕይወቱ መብልን ትጠላለች፤

ነፍሱም ምርጥ ምግብን ትጠየፋለች።

21እንዳልነበረ ሆኖ ሥጋው ይመነምናል፤

ተሸፍኖ የነበረው ዐጥንቱም ገጥጦ ይወጣል።

22ነፍሱ ወደ ጕድጓድ፣33፥22 ወይም፣ ነፍሱ ወደ ሞት

ሕይወቱም ወደ ሞት33፥22 ወይም፣ ወደ ሙታን መልእክተኞች ትቀርባለች።

23“ሆኖም ትክክለኛውን መንገድ ለሰው ያመለክት ዘንድ፣

መካከለኛም ይሆንለት ዘንድ፣

ከሺሕ አንድ መልአክ ቢገኝ፣

24ለሰውየውም በመራራት፣

‘ቤዛ አግኝቼለታለሁና፣

ወደ ጕድጓድ33፥24 ወይም፣ ወደ መቃብር እንዳይወርድ አድነው’ ቢለው፣

25በዚህ ጊዜ ሥጋው እንደ ሕፃን ልጅ ገላ ይታደሳል፤

ወደ ወጣትነቱም ዘመን ይመለሳል።

26ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል፤ ሞገስም ያገኛል፤

የእግዚአብሔርን ፊት ያያል፤ ሐሤትም ያደርጋል፤

እግዚአብሔር ወደ ጽድቅ ቦታው ይመልሰዋል።

27ከዚያም ወደ ሰዎች መጥቶ እንዲህ ይላል፤

‘ኀጢአትን ሠርቻለሁ፤ ትክክል የሆነውን አጣምሜአለሁ፤

ነገር ግን የእጄን አላገኘሁም።

28ነፍሴ ወደ ጕድጓድ33፥28 ወይም፣ ወደ መቃብር እንዳልሄድ ታድጎኛል እንዳትወርድ፣

ታድጓታል፤ በሕይወትም ሆኜ ብርሃን አያለሁ።’

29“እግዚአብሔር ይህን ሁሉ፣

ሁለት ሦስት ጊዜ ለሰው ያደርጋል።

30ይኸውም የሕይወት ብርሃን ይበራለት ዘንድ፣

ነፍሱን ከጕድጓድ33፥30 ወይም፣ ነፍሱን ከሞት ለመመለስ ነው ለመመለስ ነው።

31“ኢዮብ ሆይ፤ ልብ ብለህ ስማኝ፤

እኔ ልናገር፤ አንተ ዝም በል።

32የምትለው ካለህ፣ መልስ ስጠኝ፤

ትክክለኛነትህንም ማወቅ እፈልጋለሁና ተናገር፤

33አለዚያ፣ ዝም ብለህ ስማኝ፤

እኔም ጥበብን አስተምርሃለሁ።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約伯記 33:1-33

1約伯啊,請聽我言,

請留心聽我每一句話。

2我要開口發言,

我話已在舌尖。

3我的話發自正直的心,

我的口如實陳明道理。

4上帝的靈創造了我,

全能者的氣賦予我生命。

5如果你能,就反駁我,

站出來與我辯論。

6在上帝面前,我與你無異,

也是泥土造的。

7所以你不用懼怕我,

我不會對你施加壓力。

8「你的話已進到我耳中,

我聽見你說,

9『我純全無過,

我清白無罪,

10上帝卻挑我的錯,

與我為敵;

11祂給我戴上腳鐐,

鑒察我的一舉一動。』

12「我來答覆你,你的話沒有道理,

因為上帝比世人大。

13你為何向祂抱怨,

說祂不理會世人的話?

14上帝一再用各種方式說話,

然而世人卻不明白。

15人躺在床上沉睡時,

在夢境和夜間的異象中,

16上帝開啟他們的耳朵,

用警告驚嚇他們,

17使他們離開罪惡,

不再驕傲,

18以免他們的靈魂墜入深坑,

他們的性命被刀劍奪去。

19「人因受罰而臥病在床,

骨頭疼痛不止,

20以致毫無食慾,

對佳餚心生厭惡。

21他日漸消瘦,

只剩下骨頭。

22他的靈魂臨近深坑,

他的生命瀕臨死亡。

23如果一千天使中有一位能做他的中保,

指示他當行的事,

24上帝33·24 上帝」希伯來文是「他」,也可能指天使。就會憐憫他,說,『別讓他下墳墓,

我已得到他的贖金。』

25那時,他的皮肉將嫩如孩童,

他將恢復青春的活力。

26他向上帝禱告時必蒙悅納,

他歡呼著朝見上帝,

再度被祂視為義人。

27他會當眾歌唱說,

『我犯了罪,顛倒是非,

祂卻沒有按我的罪報應我。

28祂救贖我的靈魂,使之免下深坑,

使我的生命得見光明。』

29「看啊,這都是上帝的作為,

祂一次次地恩待世人,

30從深坑救回人的靈魂,

使他沐浴生命之光。

31約伯啊,留心聽我說,

不要作聲,我要發言。

32你若有話,就答覆我;

你只管說,我願看到你的清白。

33否則,請聽我言;

不要作聲,我要傳授你智慧。」