ኢዮብ 30 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 30:1-31

1“አሁን ግን በዕድሜ ከእኔ የሚያንሱ፣

ከመንጋዬ ጠባቂ ውሾች ጋር እንዳይቀመጡ፣

አባቶቻቸውን የናቅኋቸው፣

እነዚህ ይሣለቁብኛል።

2ጕልበት የከዳቸው፣

የክንዳቸው ብርታት ምን ፋይዳ ይሞላልኝ ነበር?

3ከችጋርና ከራብ የተነሣ ጠወለጉ፤

ሰው በማይኖርበት በረሓ፣

በደረቅም ምድር በሌሊት ተንከራተቱ።30፥3 ወይም ተሠቃዩ

4ከቍጥቋጦ ምድር ጨው ጨው የሚል አትክልት ለቀሙ፤

ምግባቸውም የክትክታ ሥር ነበር።

5ከኅብረተ ሰቡ ተለይተው ተባረሩ፤

ሰዎች እንደ ሌባ ይጮኹባቸዋል።

6በዐለት መካከል በምድር ጕድጓድ፣

በደረቅ ሸለቆ ዋሻ ውስጥ ለመኖር ተገደዱ።

7በጫካ ውስጥ ያናፋሉ፤

በእሾኻማ ቍጥቋጦ መካከልም ይታፈጋሉ።

8ስማቸው የማይታወቅ አልባሌ ናቸው፤

ከምድሪቱም ተባርረዋል።

9“አሁን ግን ልጆቻቸው በዘፈን ይሣለቁብኛል፤

በእነርሱም ዘንድ መተረቻ ሆኛለሁ።

10ይጸየፉኛል፣ ወደ እኔም አይቀርቡም፤

ያለ ምንም ይሉኝታ በፊቴ ይተፋሉ።

11እግዚአብሔር የቀስቴን አውታር ስላላላውና በመከራም ስለ መታኝ፣

በፊቴ መቈጠብን ትተዋል።

12በቀኜ በኩል ባለጌዎች30፥12 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ሆ! ብለው ተነሡብኝ፤

ለእግሬም ወጥመድ ዘረጉ፤

የዐፈር ድልድልም አዘጋጁብኝ።

13መንገድ ዘጉብኝ፤

የሚገታቸው30፥13 ወይም ማንም ሊረዳው አይችልም አሉ። ሳይኖር፣

ሊያጠፉኝ ተነሡ።

14በሰፊ ንቃቃት ውስጥ እንደሚመጣ ሰው መጡብኝ፤

በፍርስራሽም መካከል እየተንከባለሉ ደረሱብኝ።

15በድንጋጤ ተውጫለሁ፤

ክብሬ በነፋስ እንደሚወሰድ ተወስዷል፤

በሰላም መኖሬም እንደ ደመና እልም ብሎ ጠፍቷል።

16“አሁን ነፍሴ በውስጤ ዐለቀች፤

የመከራ ዘመንም ይዞኛል።

17ደዌ በሌሊት ዐጥንቴን ይበሳል፤

የሚቈረጥመኝም ፋታ አይሰጠኝም።

18እግዚአብሔር በታላቅ ኀይሉ ልብሴን30፥18 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን፣ እንደ ልብስ ሆኖብኛል ይላል። ጨምድዷል፤

በልብሴም ክሳድ ዐንቆ ይዞኛል።

19እርሱ ጭቃ ውስጥ ጥሎኛል፤

እኔም ከዐፈርና ከዐመድ አልተሻልሁም።

20“እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ ጮኽሁ፤ ነገር ግን አልመለስህልኝም፤

በፊትህም ቆምሁ፤ አንተ ግን ዝም አልኸኝ።

21ተመልሰህ ጨካኝ ሆንህብኝ፤

በክንድህም ብርታት አስጨነቅኸኝ።

22ወደ ላይ ነጥቀህ በነፋስ ፊት አበረርኸኝ፤

በዐውሎ ነፋስም ወዲያ ወዲህ ወዘወዝኸኝ።

23ለሕያዋን ሁሉ ወደ ተመደበው ስፍራ፣

ወደ ሞት እንደምታወርደኝ ዐውቃለሁ።

24“የተጐዳ ሰው ተጨንቆ ድረሱልኝ ብሎ ሲጮኽ፣

በርግጥ ክንዱን የሚያነሣበት ማንም የለም።

25በመከራ ውስጥ ላሉት አላለቀስሁምን?

ለድኾችስ ነፍሴ አላዘነችምን?

26ነገር ግን መልካም ስጠብቅ፣ ክፉ ነገር ደረሰብኝ፤

ብርሃንንም ስጠባበቅ፣ ጨለማ መጣብኝ።

27በውስጤ ያለው ነውጥ አላቋረጠም፤

የመከራ ዘመንም መጣብኝ።

28በፀሓይ አይደለም እንጂ፣ ጠቋቍሬ እዞራለሁ፤

በጉባኤ መካከል ቆሜ ለርዳታ እጮኻለሁ።

29የቀበሮች ወንድም፣

የጕጕቶችም ባልንጀራ ሆኛለሁ።

30ቈዳዬ ጠቍሮ ተቀረፈ፤

ዐጥንቴም በትኵሳት ነደደ።

31በገናዬ ለሐዘን፣

እንቢልታዬም ለልቅሶ ተቃኝቷል።

King James Version

Job 30:1-31

1But now they that are younger than I have me in derision, whose fathers I would have disdained to have set with the dogs of my flock.30.1 younger…: Heb. of fewer days than I 2Yea, whereto might the strength of their hands profit me, in whom old age was perished? 3For want and famine they were solitary; fleeing into the wilderness in former time desolate and waste.30.3 solitary: or, dark as the night30.3 in…: Heb. yesternight 4Who cut up mallows by the bushes, and juniper roots for their meat. 5They were driven forth from among men, (they cried after them as after a thief;) 6To dwell in the clifts of the valleys, in caves of the earth, and in the rocks.30.6 caves: Heb. holes 7Among the bushes they brayed; under the nettles they were gathered together. 8They were children of fools, yea, children of base men: they were viler than the earth.30.8 base…: Heb. men of no name 9And now am I their song, yea, I am their byword. 10They abhor me, they flee far from me, and spare not to spit in my face.30.10 and…: Heb. and withhold not spittle from 11Because he hath loosed my cord, and afflicted me, they have also let loose the bridle before me. 12Upon my right hand rise the youth; they push away my feet, and they raise up against me the ways of their destruction. 13They mar my path, they set forward my calamity, they have no helper. 14They came upon me as a wide breaking in of waters: in the desolation they rolled themselves upon me.

15Terrors are turned upon me: they pursue my soul as the wind: and my welfare passeth away as a cloud.30.15 my soul: Heb. my principal one 16And now my soul is poured out upon me; the days of affliction have taken hold upon me. 17My bones are pierced in me in the night season: and my sinews take no rest. 18By the great force of my disease is my garment changed: it bindeth me about as the collar of my coat. 19He hath cast me into the mire, and I am become like dust and ashes. 20I cry unto thee, and thou dost not hear me: I stand up, and thou regardest me not. 21Thou art become cruel to me: with thy strong hand thou opposest thyself against me.30.21 become…: Heb. turned to be cruel30.21 thy…: Heb. the strength of thy hand 22Thou liftest me up to the wind; thou causest me to ride upon it, and dissolvest my substance.30.22 substance: or, wisdom 23For I know that thou wilt bring me to death, and to the house appointed for all living. 24Howbeit he will not stretch out his hand to the grave, though they cry in his destruction.30.24 grave: Heb. heap 25Did not I weep for him that was in trouble? was not my soul grieved for the poor?30.25 in trouble: Heb. hard of day? 26When I looked for good, then evil came unto me: and when I waited for light, there came darkness. 27My bowels boiled, and rested not: the days of affliction prevented me. 28I went mourning without the sun: I stood up, and I cried in the congregation. 29I am a brother to dragons, and a companion to owls.30.29 owls: or, ostriches 30My skin is black upon me, and my bones are burned with heat. 31My harp also is turned to mourning, and my organ into the voice of them that weep.