ኢዮብ 3 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 3:1-26

ኢዮብ ይናገራል

1ከዚህ በኋላ፣ ኢዮብ አፉን ከፍቶ የተወለደበትን ቀን ረገመ፤ 2እንዲህም አለ፤

3“የተወለድሁበት ቀን ይጥፋ፤

‘ወንድ ልጅ ተፀነሰ’ የተባለበት ሌሊት።

4ያ ቀን ጨለማ ይሁን፤

እግዚአብሔር ከላይ አይመልከተው፤

ብርሃንም አይብራበት።

5ጨለማና የሞት ጥላ3፥5 ወይም ከባድ ጥላ ይውረሱት፤

ደመናም በላዩ ላይ ይረፍ፤

ብርሃኑን ጽልመት ይዋጠው።

6ያ ሌሊት በድቅድቅ ጨለማ ይያዝ፤

ከዓመቱ ቀናት ጋር አይቈጠር፤

ከወራቱ በአንዱም ውስጥ አይግባ።

7ያ ሌሊት መካን ይሁን፤

እልልታም አይሰማበት።

8ሌዋታንን ለማነሣሣት የተዘጋጁ፤

ቀንንም3፥8 ወይም ባሕርን የሚረግሙ ያን ቀን ይርገሙት።

9አጥቢያ ኮከቦቹ ይጨልሙ፤

ብርሃንን እየጠበቀ ይጣ፤

የንጋት ጮራ ሲፈነጥቅ አይይ።

10መከራን ከዐይኔ ይሰውር ዘንድ፣

የእናቴን ማሕፀን ደጅ በላዬ አልዘጋምና።

11“ምነው ገና ስወለድ በጠፋሁ!

ምነው ከማሕፀን ስወጣ በሞትሁ!

12የሚቀበሉኝ ጕልበቶች፤

የሚያጠቡኝ ጡቶች ለምን ተገኙ?

13ይህን ጊዜ በሰላም በተኛሁ፣

አንቀላፍቼም ባረፍሁ ነበር፤

14አሁን ፈርሶ የሚታየውን ስፍራ ለራሳቸው ካሠሩት፣

ከምድር ነገሥታትና ከአማካሪዎች ጋር፣

15ቤታቸውን በብር ከሞሉ፣

ወርቅም ከነበራቸው ገዦች ጋር ባረፍሁ ነበር።

16ወይም እንደ ተቀበረ ጭንጋፍ፣

ብርሃንም እንዳላየ ሕፃን በሆንሁ ነበር።

17በዚያ ክፉዎች ማወካቸውን ይተዋሉ፤

ደካሞችም በዚያ ያርፋሉ፤

18ምርኮኞች እንደ ልባቸው ይቀመጣሉ፤

ከእንግዲህም የአስጨናቂዎቻቸውን ጩኸት አይሰሙም።

19ትንሹም ትልቁም በዚያ ይገኛል፤

ባሪያው ከጌታው ነጻ ወጥቷል።

20“በመከራ ላሉት ብርሃን፣

ነፍሳቸው ለተማረረች ሕይወት ለምን ተሰጠ?

21ሞትን በጕጕት ለሚጠብቁና ለማያገኙት፣

ከተሰወረ ሀብት ይልቅ ለሚሹት፣

22ወደ መቃብር ሲቃረቡ ደስ እያላቸው፣

በሐሤት ለሚሞሉ ሕይወት ለምን ተሰጠ?

23መንገዱ ለተሰወረበት ሰው፤

እግዚአብሔርም በዐጥር ላጠረው፣

ሕይወት ለምን ተሰጠ?

24ትካዜ ምግብ ሆኖኛልና፤

የሥቃይ ጩኸቴም እንደ ውሃ ይፈስሳል።

25የፈራሁት ነገር መጥቶብኛል፤

የደነገጥሁበትም ደርሶብኛል።

26ሰላም የለኝም፤ ርጋታም የለኝም፤

ሁከት እንጂ ዕረፍት የለኝም።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 3:1-26

约伯咒诅自己

1后来,约伯开口咒诅自己的生日, 2说:

3“愿我出生的那日和怀我的那夜灭没。

4愿那日一片黑暗,

被天上的上帝遗忘,

没有阳光照耀。

5愿那日被黑暗和阴影笼罩,

被密云覆盖,

被阴暗淹没。

6愿那夜被幽暗吞噬,

不列在年日中,

不算在岁月里。

7愿那夜无人生育,

毫无快乐之声。

8愿那些咒诅白日、

能惹动海怪的人,

咒诅那夜。

9愿那夜的晨星昏暗,

等不到晨光的出现,

看不见黎明的眼帘。

10因为那夜没有关闭我母胎的门,

以致让我看见患难。

11“为何我不出生时就夭折,

出母胎时就断气?

12为何要把我抱在膝上,

用乳汁哺育我?

13不然我早已安然躺卧、长眠安息,

14与世上的君王和谋臣作伴——他们建造的宫殿已荒废,

15与房屋堆满金银的王侯同眠。

16为何我没有像未见天日就流产的婴儿一样消逝?

17那里,恶人不再搅扰,

疲惫者得到安息,

18被囚者得到安宁,

听不见监工的斥责。

19尊贵与卑贱的人都在那里,

奴仆不再受主人的辖制。

20“为何赐光给受苦的人,

赐生命给心灵痛苦的人?

21他们等候死亡却等不到,

他们求死胜于求宝藏。

22他们归入坟墓时非常快乐,

欣喜若狂。

23为何赐生命给前路渺茫、

被上帝围困的人?

24我以叹息为食,

呻吟如水涌流。

25我害怕的事发生了,

我恐惧的事来临了。

26我不得安宁,

不得平静,

不得安息,

只有苦难。”