ኢዮብ 24 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 24:1-25

1“ሁሉን የሚችል አምላክ ለምን የፍርድ ቀን አይወስንም?

እርሱን የሚያውቁትስ ለምን ያን ቀን እንዲያው ይጠባበቃሉ?

2ሰዎች ድንበር ይገፋሉ፤

የሰረቁትን መንጋ ያሰማራሉ።

3የድኻ ዐደጉን አህያ ቀምተው ይሄዳሉ፤

የመበለቲቱንም በሬ በመያዣነት ይወስዳሉ።

4ችግረኛውን ከመንገድ ያስወግዳሉ፤

የምድሪቱም ድኾች ይሸሸጋሉ።

5በምድረ በዳ እንዳሉ የሜዳ አህዮች፣

ድኾች ምግብ ፍለጋ ይራወጣሉ፤

ከበረሓው ምድር ለልጆቻቸው ምግብ ይሻሉ።

6ከሜዳ መኖ ይሰበስባሉ፤

ከክፉዎች የወይን ቦታም ይቃርማሉ።

7ዕራቍታቸውን ያለ ልብስ ያድራሉ፤

በብርድም ጊዜ የሚለብሱት የላቸውም።

8ከተራራ በሚወርድ ዝናብ በስብሰዋል፤

መጠለያ ዐጥተው ቋጥኝ ዐቅፈዋል።

9አባት የሌለው ልጅ ከዕቅፍ ተነጥቋል፤

የድኻውም ልጅ በዕዳ ተይዟል።

10ዕራቍታቸውን ያለ ልብስ ይሄዳሉ፤

ነዶ ይሸከማሉ፤ ግን ይራባሉ።

11በየተረተሩ24፥11 ወይም ከወፍጮዎች መካከል የወይራ ዘይት ማለት ነው፤ ሆኖም የዚህ ቃል የዕብራይስጡ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። የወይራ ዘይት ያወጣሉ፤

ወይን እየጠመቁ፣ ራሳቸው ግን ይጠማሉ፤

12የሟቾች ጣር ጩኸት ከከተማዋ ይሰማል፤

የቈሰሉት ሰዎች ነፍስ ለርዳታ ይጮኻል፤

እግዚአብሔር ግን ተጠያቂዎቹን ዝም ብሏል።

13“በብርሃን ላይ የሚያምፁ፣

ጐዳናውን የማያውቁ፣

በመንገዱም የማይጸኑ አሉ።

14ቀኑ ሲመሽ፣ ነፍሰ ገዳይ ይነሣል፤

ድኾችንና ችግረኞችን ይገድላል፤

በሌሊትም እንደ ሌባ ያደባል፤

15አመንዝራ በዐይኑ ድንግዝግዝታን ይጠባበቃል፤

‘ማንም አያየኝም’ ብሎ ያስባል፤

ፊቱንም ይሸፍናል።

16በጨለማ፣ ቤት ሰርስረው ይገባሉ፤

በቀን ግን ይሸሸጋሉ፤

ብርሃንንም አይፈልጉም።

17ድቅድቅ ጨለማ ለሁላቸው እንደ ንጋት24፥17 ወይም ለእነርሱ ንጋት እንደ ሞት ጥላ ነው ነው፤

አሸባሪውን ጨለማ24፥17 ወይም ከሞት ጥላ ማለት ነው። ይወዳጃሉ።

18“ይሁን እንጂ፣ በውሃ ላይ የሚኵረፈረፍ ዐረፋ ናቸው፤

የወይን ቦታው ሰው የማይደርስበት፣

ርስታቸው ርጉም ነው።

19ድርቅና ሙቀት የቀለጠውን በረዶ ከቦታው እንደሚያስወግድ፣

ሲኦልም24፥19 አንዳንድ ቅጆች፣ መቃብር ይሉታል ኀጢአተኞችን ትነጥቃለች።

20የተሸከመቻቸው ማሕፀን ትረሳቸዋለች፤

ትል ይቦጠቡጣቸዋል፤

ክፉዎች እንደ ዛፍ ይሰበራሉ፤

የሚያስታውሳቸውም የለም።

21የማትወልደውን መካኒቱን ይቦጠቡጣሉ፤

ለመበለቲቱም አይራሩም።

22ነገር ግን እግዚአብሔር ብርቱዎችን በኀይሉ ጐትቶ ይጥላል፤

ቢደላደሉም የሕይወት ዋስትና የላቸውም።

23ያለ ሥጋት እንዲኖሩ ትቷቸው ይሆናል፤

ዐይኖቹ ግን በመንገዳቸው ላይ ናቸው።

24ለጥቂት ጊዜ ከፍ ከፍ ይላሉ፤ ሆኖም ይጠፋሉ፤

ዝቅ ዝቅ ብለው፤ እንደ ሌሎቹ ይከማቻሉ።

እንደ እህል ራስም ይታጨዳሉ።

25“ይህ እንዲህ ካልሆነማ፣ የሚያስተባብለኝ ማን ነው?

ቃሌን ከንቱ የሚያደርገውስ ማን ነው?”

King James Version

Job 24:1-25

1Why, seeing times are not hidden from the Almighty, do they that know him not see his days? 2Some remove the landmarks; they violently take away flocks, and feed thereof.24.2 feed…: or, feed them 3They drive away the ass of the fatherless, they take the widow’s ox for a pledge. 4They turn the needy out of the way: the poor of the earth hide themselves together. 5Behold, as wild asses in the desert, go they forth to their work; rising betimes for a prey: the wilderness yieldeth food for them and for their children. 6They reap every one his corn in the field: and they gather the vintage of the wicked.24.6 corn: Heb. mingled corn, or, dredge24.6 they gather…: Heb. the wicked gather the vintage 7They cause the naked to lodge without clothing, that they have no covering in the cold. 8They are wet with the showers of the mountains, and embrace the rock for want of a shelter. 9They pluck the fatherless from the breast, and take a pledge of the poor. 10They cause him to go naked without clothing, and they take away the sheaf from the hungry; 11Which make oil within their walls, and tread their winepresses, and suffer thirst. 12Men groan from out of the city, and the soul of the wounded crieth out: yet God layeth not folly to them.

13They are of those that rebel against the light; they know not the ways thereof, nor abide in the paths thereof. 14The murderer rising with the light killeth the poor and needy, and in the night is as a thief. 15The eye also of the adulterer waiteth for the twilight, saying, No eye shall see me: and disguiseth his face.24.15 disguiseth…: Heb. setteth his face in secret 16In the dark they dig through houses, which they had marked for themselves in the daytime: they know not the light. 17For the morning is to them even as the shadow of death: if one know them, they are in the terrors of the shadow of death.

18He is swift as the waters; their portion is cursed in the earth: he beholdeth not the way of the vineyards. 19Drought and heat consume the snow waters: so doth the grave those which have sinned.24.19 consume: Heb. violently take 20The womb shall forget him; the worm shall feed sweetly on him; he shall be no more remembered; and wickedness shall be broken as a tree. 21He evil entreateth the barren that beareth not: and doeth not good to the widow. 22He draweth also the mighty with his power: he riseth up, and no man is sure of life.24.22 no…: or, he trusteth not his own life 23Though it be given him to be in safety, whereon he resteth; yet his eyes are upon their ways. 24They are exalted for a little while, but are gone and brought low; they are taken out of the way as all other, and cut off as the tops of the ears of corn.24.24 are gone: Heb. are not24.24 taken…: Heb. closed up 25And if it be not so now, who will make me a liar, and make my speech nothing worth?