ኢዮብ 23 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 23:1-17

ኢዮብ

1ኢዮብም እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“ዛሬም ሐዘኔ መራራ ነው፤

እያቃሰትሁ እንኳ እጁ23፥2 በሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ በሱርስትና በዕብራይስጡ ላይ፣ እጅ በላዬ ይላል። በላዬ ከብዳለች።

3እርሱን የት እንደማገኘው ባወቅሁ፤

ወደ መኖሪያውም መሄድ በቻልሁ!

4ጕዳዬን በፊቱ አቀርብ ነበር፤

አፌንም በሙግት እሞላው ነበር።

5የሚመልስልኝ ቃል ምን እንደ ሆነ ባወቅሁ ነበር፤

የሚለኝንም ባስተዋልሁ ነበር።

6በታላቅ ኀይሉ ከእኔ ጋር ይሟገት ይሆን?

አይደለም፤ ይልቁን ያደምጠኛል።

7ቅን ሰው ጕዳዩን በእርሱ ፊት ያቀርባል፤

እኔም ከፈራጄ ለዘላለም ነጻ እሆናለሁ።

8“ዳሩ ግን ወደ ምሥራቅ ብሄድ፣ በዚያ የለም፤

ወደ ምዕራብም ብሄድ፣ እርሱን አላገኘውም፤

9በሰሜን እየሠራ ሳለ አላየውም፤

ወደ ደቡብ በሚዞርበት ጊዜ ደብዛው አይገኝም።

10ግን እኔ የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፤

ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለሁ።

11እግሮቼ ርምጃውን በጥብቅ ተከታትለዋል፤

ፈቀቅ ሳልል መንገዱን ጠብቄአለሁ።

12ከአፉ ከወጣው ትእዛዝ አልራቅሁም፣

የአንደበቱን ቃል ከዕለት እንጀራዬ አብልጬ ይዣለሁ።

13“እርሱ ግን ራሱን ችሎ ብቻውን የሚኖር ነው፤ የሚቋቋመውስ ማን ነው?

እርሱ የፈቀደውን ያደርጋል።

14በእኔ ላይ የወሰነውን ይፈጽማል፤

ይህን የመሰለ ዕቅድም ገና ብዙ አለው።

15በፊቱ የደነገጥሁትም ለዚህ ነው፤

ይህን ሁሉ ሳስብ እፈራለሁ።

16እግዚአብሔር ልቤን አባባው፤

ሁሉንም የሚችል አምላክ አስደነገጠኝ።

17ይህም ሆኖ ሳለ ጨለማው፣

ፊቴንም የጋረደው ጽልመት ልሳኔን አልዘጋውም።

Ketab El Hayat

أيوب 23:1-17

أيوب

1أَيُّوبُ: 2«إِنَّ شَكْوَايَ الْيَوْمَ مُرَّةٌ، وَلَكِنَّ الْيَدَ الَّتِي عَلَيَّ أَثْقَلُ مِنْ أَنِينِي. 3أَيْنَ لِي أَنْ أَجِدَهُ فَأَمْثُلَ أَمَامَ كُرْسِيِّهِ، 4وَأَعْرِضَ عَلَيْهِ قَضِيَّتِي وَأَمْلأَ فَمِي حُجَجاً، 5فَأَطَّلِعَ عَلَى جَوَابِهِ وَأَفْهَمَ مَا يَقُولُهُ لِي؟ 6أَيُخَاصِمُنِي بِعَظَمَةِ قُوَّتِهِ؟ لا! بَلْ يَلْتَفِتُ مُتَرَئِّفاً عَلَيَّ. 7هُنَاكَ يُمْكِنُ لِلْمُسْتَقِيمِ أَنْ يُحَاجَّهُ، وَأُبْرِئُ سَاحَتِي إِلَى الأَبَدِ مِنْ قَاضِيَّ. 8وَلَكِنْ هَا أَنَا أَتَّجِهُ شَرْقاً فَلا أَجِدُهُ، وَإِنْ قَصَدْتُ غَرْباً لَا أَشْعُرُ بِهِ، 9أَطْلُبُهُ عَنْ شِمَالِي فَلا أَرَاهُ وَأَلْتَفِتُ إِلَى يَمِينِي فَلا أُبْصِرُهُ.

10وَلَكِنَّهُ يَعْرِفُ الطَّرِيقَ الَّتِي أَسْلُكُهَا، وَإذَا امْتَحَنَنِي أَخْرُجُ كَالذَّهَبِ 11اقْتَفَتْ قَدَمَايَ إِثْرَ خُطَاهُ، وَسَلَكْتُ بِحِرْصٍ فِي سُبُلِهِ وَلَمْ أَحِدْ. 12لَمْ أَتَعَدَّ عَلَى وَصَايَاهُ، وَذَخَرْتُ فِي قَلْبِي كَلِمَاتِهِ. 13وَلَكِنَّهُ مُتَفَرِّدٌ وَحْدَهُ فَمَنْ يَرُدُّهُ؟ يَفْعَلُ مَا يَشَاءُ، 14لأَنَّهُ يُتَمِّمُ مَا رَسَمَهُ لِي، وَمَازَالَ لَدَيْهِ وَفْرَةٌ مِنْهَا. 15لِذَلِكَ أَرْتَعِبُ فِي حَضْرَتِهِ، وَعِنْدَمَا أَتَأَمَّلُ، يُخَامِرُنِي الْخَوْفُ مِنْهُ. 16فَقَدْ أَضْعَفَ اللهُ قَلْبِي، وَرَوَّعَنِي الْقَدِيرُ. 17وَمَعَ ذَلِكَ لَمْ تَسْكُنْنِي الظُّلْمَةُ، وَلا الدُّجَى غَشَّى وَجْهِي.