ኢዮብ 16 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 16:1-22

ኢዮብ

1ኢዮብም እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“ይህን የሚመስል ብዙ ነገር ሰምቻለሁ፤

እናንተ ሁላችሁ የምታስጨንቁ አጽናኞች ናችሁ።

3ይህ ከንቱ ንግግር አያልቅምን?

ትለፈልፍ ዘንድ የሚገፋፋህ ምንድን ነው?

4እናንተ በእኔ ስፍራ ብትሆኑ ኖሮ፣

እኔም እንደ እናንተ መናገር እችል ነበር፤

ቃላት አሳክቼ በመናገር፣

በእናንተ ላይ ራሴን መነቅነቅ በቻልሁ ነበር።

5ይልቁንም አንደበቴ ባበረታታችሁ፣

የከንፈሬም ማጽናናት ባሳረፋችሁ ነበር።

6“ብናገር ሕመሜ አይሻለኝም፤

ዝም ብልም አይተወኝም።

7እግዚአብሔር ሆይ አሁንስ አድክመኸኛል፤

ወገኖቼንም ሁሉ አጥፍተሃል።

8ጭምትርትር ያደረግኸኝ ምስክር ሆኖብኛል፣

ዐጥንቴን ያወጣው ክሳቴም ያጋልጠኛል።

9በቍጣው ሰነጠቀኝ፤ በጥላቻው አስጨነቀኝ፣

ጥርሱን ነከሰብኝ፤

ባላጋራዬ ክፉ ዐይኑን ተከለብኝ።

10ሰዎች በፌዝ አፋቸውን ከፈቱብኝ፤

በንቀት ጕንጬን ጠፈጠፉኝ፤

በአንድነትም በላዬ ተሰበሰቡ።

11እግዚአብሔር ለክፉዎች አሳልፎ ሰጠኝ፤

በጠማሞችም እጅ ጣለኝ።

12በሰላም እኖር ነበር፤ እርሱ ግን ሰባበረኝ፤

ዐንገቴን ይዞ አደቀቀኝ፤

ማነጣጠሪያ ዒላማው አደረገኝ፤

13የእርሱ ቀስተኞች ከበቡኝ፤

ያለ ርኅራኄ ኵላሊቴን ይበጣጥሳል፤

ሐሞቴን መሬት ላይ ያፈስሳል።

14ደጋግሞ ይቀጠቅጠኛል፤

እንደ ጦረኛም ተንደርድሮ ይመጣብኛል።

15“በቈዳዬ ላይ ማቅ ሰፍቻለሁ፤

ክብሬን በዐፈር ውስጥ ቀብሬአለሁ።

16ፊቴ ከልቅሶ የተነሣ ቀልቷል፤

ጨለማም በዐይኖቼ ቆብ ላይ ዐርፏል፤

17ነገር ግን በእጄ ዐመፅ አይገኝም፤

ጸሎቴም ንጹሕ ነው።

18“ምድር ሆይ፤ ደሜን አትሸፍኚ፤

ጩኸቴም ማረፊያ አያግኝ!

19አሁን እንኳ ምስክሬ በሰማይ አለ፤

ጠበቃዬም በላይ በአርያም ይገኛል።

20ወዳጆቼ በንቀት ቢመለከቱኝም፣16፥20 ወይም ወዳጆቼ አማላጅ ቢሆኑልኝም

ዐይኔ ወደ እግዚአብሔር ያነባል።

21ሰው ለወዳጁ እንደሚማልድ፣

በእግዚአብሔር ፊት የሚማልድ ሰው ምነው በተገኘ!

22“ከጥቂት ዓመታት በኋላ፣

ወደማልመለስበት መንገድ እሄዳለሁ።

Ketab El Hayat

أيوب 16:1-22

أيوب

1فَقَالَ أَيُّوبُ: 2«قَدْ سَمِعْتُ كَثِيراً مِثْلَ هَذَا الْكَلامِ وَأَنْتُمْ كُلُّكُمْ مُعَزُّونَ مُتْعِبُونَ. 3أَمَا لِهَذَا اللَّغْوِ مِنْ نِهَايَةٍ؟ وَمَا الَّذِي يُثِيرُكَ حَتَّى تَرُدَّ عَلَيَّ؟ 4فِي وُسْعِي أَنْ أَتَكَلَّمَ مِثْلَكُمْ لَوْ كُنْتُمْ مَكَانِي، وَأُلْقِيَ عَلَيْكُمْ أَقْوَالَ مَلامَةٍ، وَأَهُزَّ رَأْسِي فِي وُجُوهِكُمْ، 5بَلْ كُنْتُ أُشَجِّعُكُمْ بِنَصَائِحِي، وَأُشَدِّدُكُمْ بِتَعْزِيَاتِي.

6إِنْ تَكَلَّمْتُ لَا تُمْحَى كَآبَتِي، وَإِنْ صَمَتُّ، فَمَاذَا يُخَفِّفُ الصَّمْتُ عَنِّي؟ 7إِنَّ اللهَ قَدْ مَزَّقَنِي حَقّاً وَأَهْلَكَ كُلَّ قَوْمِي. 8لَقَدْ كَبَّلْتَنِي فَصَارَ ذَلِكَ شَاهِداً عَلَيَّ، وَقَامَ هُزَالِي لِيَشْهَدَ ضِدِّي. 9مَزَّقَنِي غَضَبُهُ، وَاضْطَهَدَنِي. حَرَّقَ عَلَيَّ أَسْنَانَهُ. طَعَنَنِي عَدُوِّي بِنَظْرَاتِهِ الْحَادَّةِ. 10فَغَرَ النَّاسُ أَفْوَاهَهُمْ عَلَيَّ، لَطَمُونِي تَعْيِيراً عَلَى خَدِّي، وَتَضَافَرُوا عَلَيَّ جَمِيعاً. 11أَسْلَمَنِي اللهُ إِلَى الظَّالِمِ، وَطَرَحَنِي فِي يَدِ الأَشْرَارِ. 12كُنْتُ مُطْمَئِنّاً مُسْتَقِرّاً، فَزَعْزَعَنِي الرَّبُّ وَقَبَضَ عَلَيَّ مِنْ عُنُقِي، وَحَطَّمَنِي وَنَصَبَنِي لَهُ هَدَفاً. 13حَاصَرَنِي رُمَاتُهُ وَشَقَّ كُلْيَتَيَّ مِنْ غَيْرِ رَحْمَةٍ، أَهْرَقَ مَرَارَتِي عَلَى الأَرْضِ. 14اقْتَحَمَنِي مَرَّةً تِلْوَ مَرَّةٍ، وَهَاجَمَنِي كَجَبَّارٍ. 15خِطْتُ مِسْحاً عَلَى جِلْدِي، وَمَرَّغْتُ عِزِّي فِي التُّرَابِ. 16احْمَرَّ وَجْهِي مِنَ الْبُكَاءِ، وَغَشِيَتْ ظِلالُ الْمَوْتِ أَهْدَابِي، 17مَعَ أَنَّنِي لَمْ أَقْتَرِفْ ظُلْماً، وَصَلاتِي مُخْلِصَةٌ.

18يَا أَرْضُ لَا تَسْتُرِي دَمِي، وَلا يَكُنْ لِصُرَاخِي قَرَارٌ. 19هُوَذَا الآنَ شَاهِدِي فِي السَّمَاءِ، وَكَفِيلِي فِي الأَعَالِي 20أَمَّا أَصْحَابِي فَهُمُ السَّاخِرُونَ بِي، لِذَلِكَ تَفِيضُ دُمُوعِي أَمَامَ اللهِ، 21لَكَمْ أَحْتَاجُ لِمَنْ يُدَافِعُ عَنِّي أَمَامَ اللهِ، كَمَا يُدَافِعُ إِنْسَانٌ عَنْ صَدِيقِهِ. 22إِذْ مَا إِنْ تَنْقَضِي سَنَوَاتُ عُمْرِي الْقَلِيلَةُ حَتَّى أَمْضِيَ فِي طَرِيقٍ لَا أَعُودُ مِنْهَا.