ኢዮብ 14 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 14:1-22

1“ከሴት የተወለደ ሰው፣

ዘመኑ ዐጭርና በመከራ የተሞላ ነው፤

2እንደ አበባ ይፈካል፤ ይረግፋልም፤

እንደ ጥላ ይፈጥናል፤ አይጸናምም።

3እንደዚህ ባለ ሰው ላይ ዐይንህን ታሳርፋለህን?

ለፍርድስ በፊትህ ታቀርበዋለህን?14፥3 ሰብዓ ሊቃናት፣ ቩልጌትና ሱርስት እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ታቀርበኛለህን? ይላል

4ከርኩስ ነገር ውስጥ ንጹሕን ማን ሊያወጣ ይችላል?

አንድ እንኳ የሚችል የለም!

5የሰው ዕድሜ አስቀድሞ የተወሰነ ነው፤

የወራቱንም ብዛት ወስነህ አስቀምጠሃል፤

ሊያልፈው የማይችለውንም ገደብ አኖርህለት።

6እንግዲህ ዘመኑን እንደ ምንደኛ እስኪፈጽም ድረስ፣

ፊትህን ከእርሱ መልስ፤ ተወው።

7“ዛፍ እንኳ ቢቈረጥ፣

እንደ ገና ሊያቈጠቍጥ፣

አዳዲስ ቅርንጫፍም ሊያበቅል ተስፋ አለው።

8ሥሩ በምድር ውስጥ ቢያረጅ፣

ጕቶው በመሬት ውስጥ ቢበሰብስም፣

9የውሃ ሽታ ባገኘ ጊዜ ያቈጠቍጣል፤

እንደ ተተከለም ችግኝ ቅርንጫፍ ያወጣል።

10ሰው ግን ይሞታል፤ ክንዱንም ይንተራሳል፤

ነፍሱም ትወጣለች፤ ከእንግዲህስ የት ይገኛል?

11ውሃ ከባሕር ውስጥ እንደሚያልቅ፣

የወንዝ ውሃም ጠፍቶ እንደሚደርቅ፣

12እንደዚሁም ሰው ይተኛል፤ ቀናም አይልም፤

ሰማይ እስከሚያልፍ ድረስ አይነቃም፤

ከእንቅልፉም አይነሣም።

13“ምነው መቃብር14፥13 በዕብራይስጥ ሲኦል ማለት ነው። ውስጥ በሰወርኸኝ!

ቍጣህም እስከሚያልፍ በሸሸግኸኝ!

ምነው ቀጠሮ ሰጥተህ፣

ከዚያ በኋላ ባስታወስኸኝ!

14ሰው ከሞተ በኋላ ተመልሶ በሕይወት ይኖራል?

እድሳቴ14፥14 ወይም መፈታቴ እስከሚመጣ ድረስ፣

ተጋድሎ የሞላበትን ዘመኔን ሁሉ እታገሣለሁ።

15ትጠራኛለህ፤ እኔም እመልስልሃለሁ፤

የእጅህንም ሥራ ትናፍቃለህ።

16በዚያን ጊዜ በርግጥ ርምጃዬን ትከታተላለህ፤

ነገር ግን ኀጢአቴን አትቈጣጠርም።

17መተላለፌ በከረጢት ይቋጠራል፤

ኀጢአቴንም ትሸፍናለህ።

18“ተራራ እንደሚሸረሸርና እንደሚወድቅ፣

ዐለትም ከስፍራው እንደሚወገድ፣

19ውሃ ድንጋይን እንደሚቦረቡር፣

ጐርፍም ዐፈርን ዐጥቦ እንደሚወስድ፣

አንተም የሰውን ተስፋ ታጠፋለህ።

20አንድ ጊዜ ፈጽመህ ትበረታለህ፤ እርሱም ያልፋል፤

ገጽታውን ትቀይራለህ፤ ትሸኘዋለህም።

21ልጆቹ ቢከበሩ አያውቅም፤

ቢዋረዱም አያይም።

22የገዛ አካሉ ሕመም ብቻ ይሰማዋል፤

ለራሱም ብቻ ያለቅሳል።”

Japanese Contemporary Bible

ヨブ 記 14:1-22

14

1人はなんともろいものでしょう。

人生はなんと短く、苦しみに満ちているのでしょう。

2人は花のように咲いても、すぐにしおれ、

通り過ぎる雲の影のように

あっという間に消え失せます。

3あなたは、このようにはかない人間をきびしく責め、

あくまでさばこうとするのですか。

4生まれつき汚れている者に

どうしてきよさを求めることができましょう。

5あなたは人間に、

ほんのわずかな人生の期間を与えました。

それは月単位ではかれる程度の日数で、

それ以上、一分一秒でも延ばせません。

6だから、つかの間の休息を与えてください。

怒りに燃える目をそらして、

死ぬ前に、ほんの少しでも安らぎを与えてください。

7木には望みがある。

切り倒されても、やがて新しい芽を出し、

やわらかな枝を張る。

8-9たとえ根が老化し、根株が枯れても、

水さえあれば新しい苗木のように芽を吹き、枝を出す。

10しかし、人は違う。

死んで葬られると、その霊魂はどこへ行くのか。

11-12水が湖から蒸発し、日照りで川が干上がるように、

人は地に伏すと、永久に立ち上がらない。

目も覚まさず、眠りから起きることもない。

13あなたが私を死者のいる所に隠し、

あなたの怒りが過ぎるまで忘れ、

ずっとあとになって思い出してくださるとよいのに。

14人は死んでも生き返るかもしれません。

私はそのことに望みをかけているのです。

ですから、苦しみながらも

ひたすら死を待ち望むのです。

15私を呼んでください。いつでもみもとへまいります。

あなたは私のしたことに

ことごとく報いてくださるでしょう。

16ところが今、代わりに、

私にあとわずかしか生きることを許さず、

しかも、すべての過ちに目を留め、

17それを束にして証拠として私に突きつけます。

18-19山は崩れてなくなり、

水は石を打ち砕いて砂にし、

大水は土砂を押し流します。

そのように、人のすべての望みは絶えます。

20-21あなたはいつまでも人を打ち負かすので、

ついに人は舞台から姿を消します。

あなたは人をしわだらけの老人とし、

遠くへ追いやります。

だから、自分の子どもたちが栄誉を受けても、

失敗したり災難に会っても、

人にはそのことを知るすべがありません。

22人にはただ、悲しみと痛みだけしかないのです。」