ኢዮብ 10 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 10:1-22

1“ሕይወቴን እጅግ ጠላሁ፤

ስለዚህም ማጕረምረሜን ያለ ገደብ እለቅቃለሁ፤

በነፍሴም ምሬት እናገራለሁ።

2እግዚአብሔርን እንዲህ እለዋለሁ፤

በምን ላይ እንዳልተስማማን ንገረኝ እንጂ አትፍረድብኝ።

3የክፉዎችን ዕቅድ በደስታ እየተቀበልህ፣

እኔን ግን ስታስጨንቀኝ፣

የእጅህንም ሥራ ስታዋርድ ደስ ይልሃልን?

4አንተ ዐይንህ የሥጋ ለባሽ ዐይን ነውን?

ሟች የሆነ የሰው ልጅ እንደሚያይ ታያለህን?

5ዘመንህ እንደ ሟች ሰው ዘመን ነውን?

ወይስ ዓመታትህ እንደ ሰው ዓመታት ናቸውን?

6ታዲያ፣ በደልን የምትፈላልግብኝ፣

ኀጢአቴንም የምትከታተለው ለምንድን ነው?

7እኔ በደለኛ እንዳልሆንሁ፣

ከእጅህም ሊያስጥለኝ ማንም እንደማይችል አንተ ታውቃለህ።

8“እጅህ አበጀችኝ፤ ሠራችኝም፤

መልሰህ ደግሞ ታጠፋኛለህን?

9እንደ ሸክላ እንዳበጀኸኝ ዐስብ፤

አሁን ደግሞ ወደ ትቢያ ትመልሰኛለህን?

10እንደ ወተት አላፈሰስኸኝምን?

እንደ እርጎስ አላረጋኸኝምን?

11ቈዳና ሥጋ አለበስኸኝ፤

በዐጥንትና በጅማትም አገጣጥመህ ሠራኸኝ።

12ሕይወትን ሰጠኸኝ፤ በጎነትንም አሳየኸኝ፤

እንክብካቤህም መንፈሴን ጠበቀ።

13“ይህን ሁሉ ግን በልብህ ሸሸግህ፤

ነገሩ በዐሳብህ እንደ ነበር ዐውቃለሁ፤

14ኀጢአትን ብሠራ ትመለከተኛለህ፤

መተላለፌንም ሳትቀጣ አታልፍም።

15በደለኛ ብሆን ወዮልኝ፤

ንጹሕ ብሆንም፣ ራሴን ቀና አላደርግም፤

ውርደትን ተከናንቤአለሁና፤

በመከራም ተዘፍቄአለሁ።10፥15 ወይም መከራዬን ዐውቄአለሁ

16ራሴን ከፍ ከፍ ባደርግ፣ እንደ አንበሳ ታደባብኛለህ፤

አስፈሪ ኀይልህን ደጋግመህ ታሳየኛለህ፤

17አዳዲስ ምስክሮችን ታመጣብኛለህ፤

ቍጣህንም በላዬ ትጨምራለህ፤

ሰራዊትህም ተከታትሎ ይመጣብኛል።

18“ታዲያ ለምን ከማሕፀን አወጣኸኝ?

ምነው ዐይን ሳያየኝ በሞትሁ ኖሮ!

19ምነው ባልተፈጠርሁ!

ወይም ከማሕፀን ቀጥታ ወደ መቃብር በወረድሁ!

20ጥቂት የሆነው ዘመኔ እያለቀ አይደለምን?

ከሥቃዬ ፋታ እንዳገኝ ተወት አድርገኝ፤

21ወደማልመለስበት ስፍራ፣

ወደ ጨለማና ወደ ሞት ጥላ10፥21 ወይም ከባድ ጥላ እንዲሁም 22 አገር ከመሄዴ በፊት፣

22ብርሃኑ እንደ ጨለማ ወደ ሆነበት፣

የሞት ጥላ ወዳረበበበት፣ ሥርዐት የለሽ ወደ ሆነ ምድር፣

ድቅድቅ ጨለማ ወደ ሰፈነበት አገር ሳልሄድ ተወኝ።”

Ketab El Hayat

أيوب 10:1-22

1قَدْ كَرِهْتُ حَيَاتِي، لِهَذَا أُطْلِقُ الْعَنَانَ لِشَكْوَايَ، وَأَتَحَدَّثُ عَنْ أَشْجَانِي فِي مَرَارَةِ نَفْسِي، 2قَائِلاً لِلهِ: لَا تَسْتَذْنِبْنِي. فَهِّمْنِي لِمَاذَا تُخَاصِمُنِي؟ 3أَيَحْلُو لَكَ أَنْ تَظْلِمَ وَتَنْبِذَ عَمَلَ يَدِكَ، وَتُحَبِّذَ مَشُورَةَ الأَشْرَارِ؟ 4أَلَكَ عَيْنَا بَشَرٍ، أَمْ كَنَظَرِ الإِنْسَانِ تَنْظُرُ؟ 5هَلْ أَيَّامُكَ مِثْلُ أَيَّامِ الإِنْسَانِ، أَمْ سِنُوكَ فِي قِصَرِ سِنِيِ الْبَشَرِ، 6حَتَّى تَبْحَثَ عَنْ إِثْمِي وَتُنَقِّبَ عَنْ خَطَايَايَ؟ 7فَأَنْتَ عَالِمٌ أَنِّي لَسْتُ مُذْنِباً، وَأَنَّهُ لَا مُنْقِذَ مِنْ يَدِكَ.

8قَدْ كَوَّنَتْنِي يَدَاكَ وَصَنَعَتَانِي بِجُمْلَتِي، وَالآنَ الْتَفَتَّ إِلَيَّ لِتَسْحَقَنِي! 9اذْكُرْ أَنَّكَ جَبَلْتَنِي مِنْ طِينٍ، أَتُرْجِعُنِي بَعْدُ إِلَى التُّرَابِ؟ 10أَلَمْ تَصُبَّنِي كَاللَّبَنِ وَتُخَثِّرْنِي كَالْجُبْنِ؟ 11كَسَوْتَنِي جِلْداً وَلَحْماً، فَنَسَجْتَنِي بِعِظَامٍ وَعَصَبٍ. 12مَنَحْتَنِي حَيَاةً وَرَحْمَةً، وَحَفِظَتْ عِنَايَتُكَ رُوحِي. 13كَتَمْتَ هَذِهِ الأُمُورَ فِي قَلْبِكَ، إِلّا أَنِّي عَلِمْتُ أَنَّ هَذَا قَصْدُكَ.

14إِنْ أَخْطَأْتُ فَأَنْتَ تُرَاقِبُنِي، وَلا تُبْرِئُنِي مِنْ إِثْمِي. 15إِنْ أَذْنَبْتُ فَوَيْلٌ لِي. وَإِنْ كُنْتُ بَارّاً لَا أَرْفَعُ رَأْسِي، لأَنِّي مُمْتَلِئٌ هَوَاناً وَنَاظِرٌ مَذَلَّتِي، 16وَإِنْ شَمَخْتُ بِرَأْسِي تَقْتَنِصُنِي كَالأَسَدِ، ثُمَّ تَعُودُ فَتَصُولُ عَلَيَّ. 17تُجَدِّدُ شُهُودَكَ ضِدِّي، وَتُضْرِمُ غَضَبَكَ عَلَيَّ، وَتُؤَلِّبُ جُيُوشاً تَتَنَاوَبُ ضِدِّي.

18لِمَاذَا أَخْرَجْتَنِي مِنَ الرَّحِمِ؟ أَلَمْ يَكُنْ خَيْراً لَوْ أَسْلَمْتُ الرُّوحَ وَلَمْ تَرَنِي عَيْنٌ؟ 19فَأَكُونُ كَأَنِّي لَمْ أَكُنْ فَأُنْقَلُ مِنَ الرَّحِمِ إِلَى الْقَبْرِ. 20أَلَيْسَتْ أَيَّامِي قَلِيلَةً؟ كُفَّ عَنِّي لَعَلِّي أَتَمَتَّعُ بِبَعْضِ الْبَهْجَةِ، 21قَبْلَ أَنْ أَمْضِيَ إِلَى حَيْثُ لَا أَعُودُ، إِلَى أَرْضِ الظُّلْمَةِ وَظِلِّ الْمَوْتِ، 22إِلَى أَرْضِ الظُّلْمَةِ الْمُتَكَاثِفَةِ وَالْفَوْضَى، حَيْثُ الإِشْرَاقُ فِيهَا كَاللَّيْلِ الْبَهِيمِ».