ኢያሱ 9 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 9:1-27

የገባዖን ሰዎች የፈጸሙት ማታለል

1በዮርዳኖስ ምዕራብ ባለው በተራራማው አገር፣ በቈላማው ምድር እንዲሁም እስከ ሊባኖስ በሚደርሰው በመላው በታላቁ ባሕር9፥1 የሜድትራኒያን ባሕር ነው። ዳርቻ የነበሩት የኬጢያውያን፣ የአሞራውያን፣ የከነዓናውያን፣ የፌርዛውያን፣ የኤዊያውያን፣ የኢያቡሳውያን ነገሥታት ይህን በሰሙ ጊዜ፣ 2ኢያሱንና እስራኤልን ለመውጋት በአንድነት መጡ።

3የገባዖን ሰዎች ግን ኢያሱ በኢያሪኮና በጋይ ላይ ያደረገውን በሰሙ ጊዜ፣ 4ለማታለል ፈለጉ፤ ስለዚህም ያረጀ ስልቻና የተጣፈ አሮጌ የወይን ጠጅ አቍማዳ በአህያ የጫነ9፥4 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ የቩልጌት፣ የሱርስቱ ትርጕም እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ቅጅ፣ “የሚያስፈልጋቸውን ነገር አዘጋጁ፤ በአህዮቻቸውም ላይ ጫኑ” ይላሉ። መልእክተኛ መስለው ሄዱ። 5ሰዎቹም ያረጀና የተጠጋገነ ነጠላ ጫማ አድርገዋል፤ አሮጌ ልብስ ለብሰዋል፤ ለስንቅ የያዙት እንጀራም በሙሉ የደረቀና የሻገተ ነበር። 6ከዚያም ኢያሱ ወደ ሰፈረበት ወደ ጌልገላ ሄደው ኢያሱንና የእስራኤልን ሰዎች፣ “የመጣነው ከሩቅ አገር ነው፤ ከእኛ ጋር ቃል ኪዳን ግቡ” አሏቸው።

7የእስራኤልም ሰዎች ለኤዊያውያኑ፣ “እናንተ የምትኖሩት እዚሁ ቅርብ ቢሆንስ? ታዲያ ከእናንተ ጋር እንዴት ቃል ኪዳን እንገባለን?” አሏቸው።

8እነርሱም ኢያሱን፣ “እኛ ባሪያዎችህ ነን” አሉት።

ኢያሱ ግን፣ “እናንተ እነማን ናችሁ? የመጣችሁትስ ከየት ነው?” ሲል ጠየቃቸው።

9እነርሱም እንዲህ ብለው መለሱለት፤ “እኛ ባሪያዎችህ የአምላካህን የእግዚአብሔርን ዝና ሰምተን፣ እጅግ ሩቅ ከሆነ አገር መጥተናል፤ ዝናውንና በግብፅ ያደረገውንም ሁሉ ሰምተናል፤ 10እንዲሁም ከዮርዳኖስ ማዶ ባሉት በሁለቱ የአሞራውያን ነገሥታት ማለትም በሐሴቦን ንጉሥ በሴዎን፣ አስታሮትን ይገዛ በነበረው በባሳን ንጉሥ በዐግ ያደረገውን ሁሉ ነው። 11ሽማግሌዎቻችንና በአገራችን የሚኖሩት ሁሉ፣ ‘ለመንገዳችሁ የሚሆን ስንቅ ያዙ፤ ሄዳችሁም ተገናኟቸው፤ እኛ ባሮቻችሁ እንሆናለን፤ ከእኛ ጋር ቃል ኪዳን ግቡ በሏቸው’ አሉን። 12ይህ የያዝነው እንጀራ ወደ እናንተ ለመምጣት ከቤታችን በተነሣንበት ቀን ትኵስ ነበር፤ አሁን ግን እንዴት እንደ ደረቀና እንደ ሻገተ ተመልከቱ። 13እነዚህ የወይን ጠጅ አቍማዳዎቻችን ያን ጊዜ ስንሞላቸው አዲስ ነበሩ፤ አሁን ግን እንዴት እንደ ተቀዳደዱ ተመልከቱ፤ ልብሳችንና ጫማችንም ብዙ መንገድ በመጓዛችን ዐልቀዋል።”

14የእስራኤልም ሰዎች ከስንቃቸው ላይ ጥቂት ወሰዱ፤ ስለ ጕዳዩ ግን እግዚአብሔርን አልጠየቁም ነበር። 15ኢያሱም በሰላም ለመኖር የሚያስችላቸውን ቃል ኪዳን ከእነርሱ ጋር አደረገ፤ የጉባኤውም መሪዎች ይህንኑ በመሐላ አጸኑላቸው።

16እስራኤላውያን ከገባዖን ሰዎች ጋር ቃል ኪዳኑን ካደረጉ ከሦስት ቀን በኋላ፣ ሰዎቹ እዚያው አጠገባቸው የሚኖሩ ጎረቤቶቻቸው መሆናቸውን ሰሙ። 17ስለዚህ እስራኤላውያን ተጕዘው በሦስተኛው ቀን ገባዖን፣ ከፊራ፣ ብኤሮትና ቂርያትይዓይሪም ወደ ተባሉት የገባዖን ሰዎች ወደሚኖሩባቸው ከተሞች መጡ። 18ሆኖም እስራኤላውያን አልወጓቸውም፤ የጉባኤው መሪዎች በእስራኤል አምላክ በእግዚአብሔር ስም ምለውላቸው ነበርና።

ማኅበሩም ሁሉ በመሪዎቹ ላይ አጕረመረሙ፤ 19ነገር ግን መሪዎቹ ሁሉ ለማኅበሩ እንዲህ ሲሉ መለሱ፤ “በእስራኤል አምላክ በእግዚአብሔር ስም ስለማልንላቸው፣ አሁን ጕዳት ልናደርስባቸው አንችልም። 20እንዲህ እናደርግላቸዋለን፤ የገባንላቸውን መሐላ በማፍረስ ቍጣ እንዳይደርስብን፣ በሕይወት እንዲኖሩ እንዲሁ እንተዋቸዋለን፤ 21ነገር ግን ለማኅበረ ሰቡ በሙሉ ዕንጨት እየቈረጡ ውሃ እየቀዱ ይኑሩ።” ስለዚህ መሪዎቹ የገቡላቸው ቃል ተጠበቀ።

22ከዚያም ኢያሱ የገባዖንን ሰዎች ጠርቶ እንዲህ አላቸው፤ “እዚሁ አጠገባችን መኖራችሁ የታወቀ ሆኖ ሳለ፣ ‘የምንኖረው ከእናንተ በራቀ ስፍራ ነው’ ብላችሁ ያታለላችሁን ለምንድን ነው? 23ስለዚህ አሁን የተረገማችሁ ናችሁ፤ ጥቂቶቻችሁም ለአምላኬ ቤት ምንጊዜም ዕንጨት ቈራጭ፣ ውሃ ቀጂ ባሮች ትሆናላችሁ።”

24እነርሱም ለኢያሱ እንዲህ ብለው መለሱለት፤ “አምላክህ እግዚአብሔር ባሪያውን ሙሴን እንዳዘዘው፣ ምድሪቱን በሙሉ ለእናንተ እንደሚሰጣችሁና ነዋሪዎቿንም ከፊታችሁ እንደሚያጠፋቸው በርግጥ ለእኛ ለባሪያዎችህ ተነግሮናል፤ ስለዚህ ከእናንተ የተነሣ ለሕይወታችን በመሥጋት ይህን አድርገናል። 25እነሆ፤ አሁን በእጅህ ውስጥ ነን፤ በጎና ትክክል መስሎ የታየህን ነገር ሁሉ አድርግብን።”

26ስለዚህ ኢያሱ የገባዖንን ሰዎች ከእስራኤላውያን እጅ አዳናቸው፤ እነርሱም አልገደሏቸውም። 27በዚያችም ዕለት ኢያሱ የገባዖንን ሰዎች ለማኅበረ ሰቡና እግዚአብሔር በሚመርጠው ስፍራ ለሚቆመው የእግዚአብሔር ለሆነው መሠዊያ እስከ ዛሬ ድረስ ዕንጨት ቈራጮችና ውሃ ቀጂዎች አደረጋቸው።

Bibelen på hverdagsdansk

Josvabogen 9:1-27

Gibeonitterne narrer Josva

1-2I landet vest for Jordanfloden boede der en række folkeslag, nemlig hittitterne, amoritterne, kana’anæerne, perizzitterne, hivvitterne og jebusitterne. Deres landområder dækkede højsletterne midt i landet, kystsletterne ud mod Middelhavet og skrænterne midt imellem. Nogle boede mod nord oppe ved Libanons bjerge. Da kongerne for alle disse folkeslag hørte, hvad der var sket med Jeriko og Aj, sluttede de sig sammen for at gøre fælles sag imod Josva og Israels folk. 3Men da de hivvitter, som boede omkring byen Gibeon, hørte om Jerikos og Ajs totale udslettelse, 4forsøgte de at redde livet ved list. En gruppe af dem lagde gamle sadler og sprukne vinsække på deres æsler, 5tog laset tøj og lappede sandaler på, og tørt, muggent brød med som proviant, og så rejste de af sted for at forhandle med Josva. 6Da de kom til israelitternes lejr ved Gilgal, sagde de til Josva og de ledende mænd i Israel: „Vi er kommet fra et fjernt land for at slutte fredspagt med jer.”

7Israelitterne svarede: „Hvordan kan vi være sikre på, at I ikke bor her i nærheden? For hvis det er tilfældet, kan vi ikke slutte fredspagt med jer.”

8De svarede: „Vi vil være jeres slaver.”

„Men hvem er I?” spurgte Josva. „Og hvor kommer I fra?”

9„Vi kommer fra et meget fjernt land,” svarede de. „Vi har hørt om jeres vældige Gud og alle de undere, han gjorde i Egypten. 10Vi har også hørt, hvad I gjorde ved de to amoritterkonger øst for Jordanfloden, kong Sihon af Heshbon og kong Og af Bashan, som boede i Ashtarot. 11Derfor sagde vores ledere og landsmænd til os: ‚Tag proviant med og begiv jer ud på den lange rejse. Opsøg israelitterne og sig, at vi er villige til at lade dem regere over os, hvis de vil slutte fred med os.’ 12Se det her brød, som vi tog med hjemmefra. Det var helt nybagt, da vi tog af sted, men nu er det tørt og muggent. 13Se på vores vinsække. De var nye, da vi fyldte vin i dem, men nu er de sprukne. Og vores tøj og sandaler er blevet helt slidt op på den lange rejse.”

14De israelitiske ledere inspicerede deres brød, men de spurgte ikke Herren til råds. 15Josva sluttede derefter fred med dem, og de israelitiske ledere bekræftede aftalen med en bindende ed.

16Tre dage efter at fredsaftalen var indgået, blev israelitterne klar over, at folkene i virkeligheden boede i nærheden. 17Straks tog israelitterne af sted og nåede på den tredje dag frem til hivvitternes byer Gibeon, Kefira, Be’erot og Kirjat-Jearim. 18Men de angreb dem ikke, for deres ledere havde lovet dem fred i Herrens, Israels Guds, navn. Da beklagede israelitterne sig over for deres ledere.

19Men lederne svarede: „Vi har i Israels Guds navn aflagt ed på ikke at ville røre dem. 20Så vi er tvunget til at lade dem være, for hvis vi bryder løftet, rammes vi af Guds vrede. 21Men vi vil gøre dem til vores slaver, så de må hugge brænde og bære vand for os.” Sådan overholdt israelitterne deres løfte til gibeonitterne.

22Men Josva samlede nu deres ledere og spurgte: „Hvorfor løj I for os og sagde, at I kom fra et fjernt land, når I i virkeligheden bor her? 23Som straf skal I rammes af forbandelsen. Fra nu af skal I altid være vores slaver og hugge brænde og bære vand til brug i vores Guds hus.”

24„Vi gjorde det, fordi vi hørte, at Herren, din Gud, havde givet sin tjener Moses befaling om at erobre hele landet og udslette befolkningen,” svarede de. „Vi var bange for, at I ville slå os ihjel. 25Men nu er vi jeres slaver, og I kan gøre med os, som I vil.”

26Josva tillod altså ikke israelitterne at dræbe dem, 27men gjorde dem i stedet til slaver, som skulle hugge brænde og hente vand til israelitterne og til Herrens alter, hvor end Herren ville have det bygget. Den ordning står stadig ved magt.