ኢያሱ 7 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 7:1-26

የአካን ኀጢአት

1እስራኤላውያን ግን ዕርም የሆነውን ነገር7፥1 በዚህም ሆነ በቍጥር 11፡12፡13 እና 15 ላይ የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠት ማለት ነው። ለራሳቸው በመውሰድ በደሉ፤ ይህም ከይሁዳ ነገድ የሆነው አካን የከርሚ ልጅ፣ የዘንበሪ7፥1 1ዜና 2፥6 እና የሰብዓ ሊቃናት ትርጉም ይመ፤ በዚህም ሆነ በቍጥር 17 እና 18 ላይ ዕብራይስጡ “ዘብዴ” ይላል። ልጅ፣ የዛራ ልጅ ዕርም ከሆነው ነገር ስለ ወሰደ የእግዚአብሔር ቍጣ በእስራኤል ልጆች ላይ ነደደ።

2ኢያሱ ከቤቴል በስተ ምሥራቅ ካለችው ከቤት አዌን አጠገብ ወደምትገኘው ወደ ጋይ ከኢያሪኮ ሰዎችን ልኮ፣ “ወደዚያ ውጡ፤ አገሪቱንም ሰልሉ” አላቸው፤ ሰዎቹም ወጥተው ጋይን ሰለሉ።

3ወደ ኢያሱም ተመልሰው፣ “ጋይን ለመውጋት ሕዝቡ ሁሉ መሄድ አያስፈልገውም፤ በዚያ ያለው ሕዝብ ጥቂት ስለሆነ፣ ከተማዪቱን ለመውጋት ሁለት ወይም ሦስት ሺሕ ሰው ስለሚበቃ ሕዝቡ ሁሉ ወደዚያ በመሄድ አይድከም” አሉት። 4ስለዚህ ሦስት ሺሕ ያህል ሰው ወጣ፤ ከጋይም ሰዎች ፊት ሸሸ፤ 5የጋይም ሰዎች እስራኤላውያንንም ከከተማዪቱ ቅጥር በር ጀምሮ እስከ ሽባሪም7፥5 ወይም እስከ “ድንጋይ መፍለጫው” ተብሎ መተርጐም ይችላል። ድረስ በማባረር ቍልቍለቱ ላይ መቷቸው፤ ከእነርሱም ሠላሳ ስድስት ያህል ሰው ገደሉባቸው። ከዚህ የተነሣም የሕዝቡ ልብ ቀለጠ፤ እንደ ውሃም ፈሰሰ።

6በዚህ ጊዜ ኢያሱ ልብሱን ቀደደ፤ በእግዚአብሔርም ታቦት ፊት በግንባሩ ተደፋ፤ የእስራኤል ሽማግሌዎችም እንደዚሁ አደረጉ፤ በራሳቸውም ላይ ትቢያ ነሰነሱ። 7ኢያሱም እንዲህ አለ፤ “ወዮ! ልዑል እግዚአብሔር ሆይ፤ ዮርዳኖስን አሻግረህ ይህን ሕዝብ ወደዚህ ያመጣኸው ለአሞራውያን አሳልፈህ በመስጠት እንዲያጠፉን ነውን? ምነው ሳንሻገር እዚያው ማዶ በቀረን ኖሮ! 8ጌታ ሆይ፤ እስራኤል በጠላቱ ፊት ሲሸሽ እኔ ምን ልበል? 9ከነዓናውያንና ሌሎቹ የምድሪቱ ነዋሪዎች ሁሉ ይህን ሲሰሙ ይከቡናል፤ ስማችንንም ከምድር ገጽ ያጠፉታል፤ እንግዲህ ስለ ታላቁ ስምህ ስትል የምታደርገው ምንድን ነው?”

10እግዚአብሔር ኢያሱን እንዲህ አለው፤ “ተነሥ! ለምን በግንባርህ ተደፋህ? 11እስራኤል በድሏል፤ እንዲጠብቁ ያዘዝኋቸውን ቃል ኪዳኔን ጥሰዋል፤ ዕርም የሆነውን ነገር ወስደዋል፤ ሰርቀዋል፤ ዋሽተዋል፤ የወሰዱትንም ከራሳቸው ንብረት ጋር ደባልቀዋል። 12እንግዲህ እስራኤላውያን ጠላቶቻቸውን ለመቋቋም ያልቻሉት በዚህ ምክንያት ነው። ጀርባቸውን አዙረው የሸሹትም ለጥፋት በመዳረጋቸው ነው። ዕርም የሆነውን ነገር ከመካከላችሁ ካላጠፋችሁ፣ ከዚህ በኋላ ከእናንተ ጋር አልሆንም።

13“ተነሣ፤ ሕዝቡን ቀድስ፤ እንዲህም በላቸው፤ ‘እስራኤል ሆይ፤ እርም የሆነ ነገር በመካከላችሁ ስላለ፣ ይህን ካላስወገዳችሁ ጠላቶቻችሁን ለመቋቋም እንደማትችሉ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ተናግሯልና ለነገ ራሳችሁን ለማዘጋጀት ሰውነታችሁን ቀድሱ።

14“ ‘ማለዳ በየነገድ በየነገዳችሁ ሆናችሁ ቅረቡ፤ እግዚአብሔር የሚለየው ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ሆኖ ከሕዝቡ መካከል ወደ ፊት ይወጣል፤ እንዲሁም እግዚአብሔር የሚለየው ጐሣ በየቤተ ሰቡ ሆኖ ወደ ፊት ይወጣል፤ እግዚአብሔር የሚለየው ቤተ ሰብ ደግሞ በግለ ሰብ በግለ ሰብ ሆኖ ወደ ፊት ይወጣል። 15ዕርሙ የተገኘበት ሰው፣ እርሱና ያለው ሁሉ በእሳት ይቃጠላል፤ የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን አፍርሷል፤ በእስራኤልም ዘንድ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟልና።’ ”

16በማግስቱም ጧት ኢያሱ ማልዶ ተነሣ፤ እስራኤልንም በየነገድ በየነገዳቸው ሆነው እንዲቀርቡ አደረገ፤ ከዚያም የይሁዳ ነገድ ተለየ። 17የይሁዳንም ጐሣዎች ወደ ፊት አቀረበ፤ ከእነዚህም የዛራን ጐሣ ለየ፤ እነዚህን ደግሞ በየቤተ ሰባቸው እንዲወጡ አደረገ፤ ከእነዚህም ዘንበሪ ተለየ። 18ኢያሱ የዘንበሪን ቤተ ሰብ አባላት አንድ በአንድ ወደ ፊት እንዲቀርቡ አደረገ፤ ከዚያም ከይሁዳ ነገድ የሆነውም የዛራ ልጅ፣ የዘንበሪ ልጅ፣ የከርሚ ልጅ አካን ለብቻው ተለየ።

19ኢያሱም አካንን፣ “ልጄ ሆይ፤ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብርን ስጥ7፥19 እውነትን ለመናገር የሚደረግ መሐላ ነው።፤ ለእርሱም ተናዘዝ፤ ያደረግኸውን ሳትደብቅ ንገረኝ” አለው።

20አካንም መልሶ ኢያሱን እንዲህ አለው፤ “እውነት ነው! የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን በድያለሁ፤ ያደረግሁትም ይህ ነው፤ 21ከምርኮው ዕቃ መካከል ከሰናዖር7፥21 አንዳንድ ቅጆች “ባቢሎን” ይላሉ። የመጣ አንድ የሚያምር ካባ፣ ሁለት መቶ ሰቅል7፥21 2.3 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብርና7፥21 0.6 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ክብደቱ አምሳ ሰቅል የሚሆን የወርቅ ቡችላ አይቼ ጐመጀሁ፤ ወሰድኋቸውም፤ ዕቃውም ብሩ ከታች ሆኖ፣ በድንኳኔ ውስጥ መሬት ተቀብሯል።”

22በዚህ ጊዜ ኢያሱ መልእክተኞች ላከ፤ እነርሱም ወደ ድንኳኑ ሮጡ፤ በዚያም ብሩ ከታች ሆኖ ዕቃው እንደ ተቀበረ አገኙ። 23ከድንኳኑም አውጥተው፣ ኢያሱና እስራኤላውያን ሁሉ ወዳሉበት አምጥተው በእግዚአብሔር ፊት አኖሩ።

24ኢያሱም ከመላው እስራኤል ጋር ሆኖ፣ የዛራን ልጅ አካንን፣ ብሩን፣ ካባውን፣ የወርቁን ቡችላ፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቹን፣ የከብቱን መንጋ፣ አህዮቹንና በጎቹን እንዲሁም ድንኳኑንና የእርሱ የሆነውን ሁሉ ወደ አኮር ሸለቆ አስወሰደ። 25ኢያሱም፣ “እንዲህ ያለውን መከራ ለምን አመጣብህን? እነሆ፤ ዛሬ በአንተም ላይ እግዚአብሔር መከራ ያመጣብሃል” አለው።

ከዚያም እስራኤል በሙሉ በድንጋይ ወገሩት፤ የቀሩትንም እንደዚሁ ከወገሩ በኋላ በእሳት አቃጠሏቸው። 26በአካንም ላይ እስከ ዛሬ ድረስ የሚታየውን ታላቅ የድንጋይ ቍልል ከመሩበት፤ ከዚያም እግዚአብሔር ከአስፈሪ ቍጣው ተመለሰ። ስለዚህ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያ ስፍራ የአኮር7፥26 አኮር” ማለት ችግር ወይም መከራ ማለት ነው። ሸለቆ ተባለ።

Thai New Contemporary Bible

โยชูวา 7:1-26

บาปของอาคาน

1แต่ชนอิสราเอลไม่ซื่อสัตย์เกี่ยวกับของที่ต้องอุทิศถวาย7:1 คำนี้ในภาษาฮีบรูหมายถึงสิ่งของหรือบุคคลที่ถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าแล้วไม่อาจเรียกคืนได้ มักจะต้องทำลายให้หมดสิ้นไป เช่นเดียวกับข้อ 11,12,13 และ 15 อาคานบุตรคารมีผู้เป็นบุตรของศิมรี7:1 หรือศับดีเช่นเดียวกับข้อ 17 และ 18 (ดู1พศด.2:6) ผู้เป็นบุตรของเศราห์เผ่ายูดาห์ได้แอบเก็บบางสิ่งไว้ ดังนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงพระพิโรธอิสราเอล

2ครั้งนั้นโยชูวาส่งคนจากเมืองเยรีโคไปเมืองอัยซึ่งอยู่ใกล้เบธอาเวนทางทิศตะวันออกของเบธเอล และสั่งพวกเขาว่า “จงไปสืบดูสภาพแถบนั้น” ดังนั้นพวกเขาจึงไปสำรวจดูเมืองอัย

3พวกเขากลับมารายงานโยชูวาว่า “ไม่ต้องนำพลทั้งหมดไปรบกับอัย ส่งเพียงสองหรือสามพันคนไปยึดก็พอ ไม่ต้องให้ประชากรทั้งหมดเหนื่อยยาก เพราะที่นั่นมีเพียงไม่กี่คน” 4ดังนั้นจึงมีทหารออกไปราวสามพันคน แต่ต้องแตกพ่ายหนีจากชาวเมืองอัย 5คนอิสราเอลราว 36 คนถูกฆ่าตายขณะบุกเข้าตีเมือง และอีกจำนวนมากถูกชาวเมืองอัยไล่ฆ่าฟันจากประตูเมืองถึงเหมืองหิน7:5 หรือเชบาริม ประชาชนอิสราเอลก็ระทดท้อขวัญเสียไป

6โยชูวาจึงฉีกเสี้อผ้าหมอบกราบซบหน้าลงกับพื้นด้านหน้าหีบพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าจนถึงเวลาเย็น บรรดาผู้อาวุโสของอิสราเอลก็ทำเช่นเดียวกัน และโปรยฝุ่นใส่ศีรษะของตน 7โยชูวากราบทูลว่า “ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต เหตุใดจึงทรงนำเหล่าประชากรนี้ข้ามแม่น้ำจอร์แดนมาสู่เงื้อมมือชาวอาโมไรต์ให้เขาทำลายเรา? พวกข้าพระองค์น่าจะพอใจที่จะอาศัยฝั่งข้างโน้นของแม่น้ำจอร์แดน 8ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า ข้าพระองค์จะพูดอย่างไรดี ในเมื่ออิสราเอลพ่ายแพ้ศัตรูมาเช่นนี้? 9ชาวคานาอันและชนชาติใกล้เคียงได้ยินเรื่องนี้ ก็จะมารุมล้อมกวาดล้างข้าพระองค์ทั้งหลายให้สิ้นชื่อไปจากแผ่นดิน และจะเกิดอะไรขึ้นกับพระนามอันยิ่งใหญ่ของพระองค์?”

10องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโยชูวาว่า “จงลุกขึ้น! เจ้าหมอบกราบซบหน้าลงกับพื้นทำไม? 11อิสราเอลได้ทำบาป ฝ่าฝืนพันธสัญญาของเราซึ่งบัญชาให้เขาปฏิบัติ พวกเขาซุกซ่อนของที่ต้องอุทิศถวาย เขาขโมยและโกหก เก็บสิ่งเหล่านั้นไว้กับทรัพย์สินส่วนตัว 12ด้วยเหตุนี้เองชนชาติอิสราเอลจึงไม่สามารถต่อสู้กับศัตรู แต่ต้องพ่ายแพ้เพราะถูกกำหนดไว้ให้พินาศ เราจะไม่อยู่กับพวกเจ้าอีกต่อไป เว้นแต่ว่าเจ้าทั้งหลายได้ทำลายของที่ต้องอุทิศถวายซึ่งเราสั่งให้ทำลายไปเสียก่อน

13“ไปเถิด ไปชำระเหล่าประชากรให้บริสุทธิ์ และสั่งพวกเขาว่า ‘จงชำระตนให้บริสุทธิ์ เตรียมตัวสำหรับวันรุ่งขึ้น เพราะพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสดังนี้ว่า มีสิ่งที่ต้องอุทิศถวายอยู่ท่ามกลางพวกเจ้า อิสราเอลเอ๋ย เจ้าจะไม่สามารถต่อสู้กับศัตรูจนกว่าจะได้กำจัดสิ่งนั้นไป

14“ ‘เช้าวันพรุ่งนี้พวกเจ้าจงมารายงานตัวทีละเผ่า เผ่าที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงระบุ จงออกมาข้างหน้าทีละตระกูล ตระกูลที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงระบุ จงออกมาข้างหน้าทีละครอบครัว ครอบครัวที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงระบุ จงออกมาข้างหน้าทีละคน 15ผู้ที่ถูกจับได้ว่ามีของต้องอุทิศถวาย จะถูกเผาทำลายพร้อมทั้งข้าวของทุกอย่างของเขา เพราะเขาได้ละเมิดพันธสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าทำสิ่งที่น่าอับอายในอิสราเอล!’ ”

16เช้าตรู่วันรุ่งขึ้นโยชูวาจึงให้ชนอิสราเอลออกมาข้างหน้าทีละเผ่า จับได้เผ่ายูดาห์ 17ตระกูลต่างๆ ของยูดาห์ออกมาข้างหน้า จับได้ตระกูลเศราห์ ครอบครัวต่างๆ ของเศราห์ออกมาข้างหน้า จับได้ครอบครัวศิมรี 18โยชูวาให้ครอบครัวศิมรีออกมาทีละคน จับได้อาคานบุตรคารมีซึ่งเป็นบุตรศิมรี ซึ่งเป็นบุตรเศราห์แห่งเผ่ายูดาห์

19โยชูวาจึงกล่าวกับอาคานว่า “ลูกเอ๋ยจงถวายเกียรติแด่พระยาห์เวห์7:19 เป็นคำกำชับให้บอกความจริงพระเจ้าแห่งอิสราเอล และถวายสรรเสริญแด่พระองค์7:19 หรือสารภาพต่อพระองค์ บอกเราเถิดว่าเจ้าทำอะไรลงไป อย่าปิดบังไว้เลย”

20อาคานตอบว่า “เป็นความจริงที่ข้าพเจ้าได้ทำบาปต่อพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอล สิ่งที่ข้าพเจ้าทำลงไปคือ 21ในกองของที่ริบมาได้ ข้าพเจ้าเห็นเสื้อคลุมสวยงามจากบาบิโลน7:21 ภาษาฮีบรูว่าชินาร์ เงินหนักประมาณ 2.3 กิโลกรัม7:21 ภาษาฮีบรูว่า 200 เชเขล และทองแท่งหนักประมาณ 600 กรัม7:21 ภาษาฮีบรูว่า 50 เชเขล ข้าพเจ้าอยากได้ จึงนำมาฝังไว้ใต้พื้นดินในเต็นท์ของข้าพเจ้า โดยฝังเงินไว้ใต้สุด”

22โยชูวาจึงส่งคนไป พวกเขาวิ่งไปที่เต็นท์ของอาคาน พบของซ่อนอยู่ในเต็นท์ของเขา เงินถูกฝังไว้ใต้สุด 23เขานำของเหล่านั้นจากเต็นท์มายังโยชูวาและปวงชนอิสราเอล แล้ววางลงต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า

24แล้วโยชูวากับชนอิสราเอลทั้งปวงจึงนำอาคานบุตรเศราห์ เงิน เสื้อคลุม ทองแท่ง บรรดาบุตรชายและบุตรสาวของเขา วัว ลา แกะ เต็นท์ และ สมบัติทุกอย่างของเขาไปยังหุบเขาอาโคร์ 25โยชูวากล่าวว่า “ทำไมเจ้าจึงนำความเดือดร้อนมาสู่พวกเรา? วันนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงนำความเดือดร้อนมาสู่เจ้า”

แล้วชาวอิสราเอลทั้งปวงเอาหินขว้างใส่อาคานและครอบครัวจนตายและเผาร่างของพวกเขา 26แล้วเอาหินสุมทับอาคานเป็นพะเนิน ซึ่งยังคงอยู่ตราบทุกวันนี้ สถานที่นั้นจึงได้ชื่อว่าอาโคร์7:26 แปลว่า ความเดือดร้อน ตราบเท่าทุกวันนี้ แล้วพระพิโรธอันรุนแรงขององค์พระผู้เป็นเจ้าก็สงบลง