ኢያሱ 22 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 22:1-34

ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ርስት ያገኙ ነገዶች ወደ ቤታቸው ተመለሱ

1በዚህ ጊዜ ኢያሱ የሮቤልንና የጋድን ነገዶች፣ እንዲሁም የምናሴን ነገድ እኩሌታ ጠርቶ 2እንዲህ አላቸው፤ “የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ያዘዘውን ሁሉ ጠብቃችኋል፤ እኔም ያዘዝኋችሁን በሙሉ ፈጽማችኋል፤ 3ከረጅም ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ወንድሞቻችሁን አልተዋችሁም፤ አምላካችሁ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ተልእኮ በሚገባ ተወጥታችኋል። 4አሁንም አምላካችሁ እግዚአብሔር በሰጣችሁ ተስፋ መሠረት ወንድሞቻችሁን አሳርፏቸዋል፤ ስለዚህ የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ከዮርዳኖስ ማዶ ርስት አድርጎ በሰጣችሁ ምድር ወዳለው ቤታችሁ ተመለሱ። 5የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ፣ አምላካችሁን እግዚአብሔርን እንድትወዱ፣ በመንገዱ ሁሉ እንድትሄዱ፣ ትእዛዙን እንድትፈጽሙ፣ እርሱንም አጥብቃችሁ እንድትይዙት እንዲሁም በፍጹም ልባችሁ፣ በፍጹም ነፍሳችሁ እንድታገለግሉት የሰጣችሁን ትእዛዙንና ሕጉን ነቅታችሁ ጠብቁ።”

6ከዚያም ኢያሱ መርቆ አሰናበታቸው፤ እነርሱም ወደ ቤታቸው ተመለሱ። 7ሙሴ ለምናሴ ነገድ እኩሌታ በባሳን ምድር ርስት ሰጥቷቸው ነበር፤ ለቀረው እኩሌታ ደግሞ ኢያሱ ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ከወንድሞቻቸው ጋር ርስት ሰጣቸው። ኢያሱ ወደ ቤታቸው እንዲገቡ ባሰናበታቸው ጊዜ መረቃቸው፤ 8እንዲህም አላቸው፤ “ብዙ ሀብት ይዛችሁ ማለትም አያሌ የከብት መንጋ፣ ብርና ወርቅ፣ ናስና ብረት እንዲሁም ቍጥሩ እጅግ የበዛ ልብስ ይዛችሁ ወደ ቤታችሁ ተመለሱ፤ ከጠላት የተገኘውንም ይህን ምርኮ ከወንድሞቻችሁ ጋር ተካፈሉት” አላቸው።

9ስለዚህ የሮቤልና የጋድ ነገዶች እንዲሁም የምናሴ ነገድ እኩሌታ እስራኤላውያንን ከነዓን ውስጥ ባለችው በሴሎ ትተው፣ በእግዚአብሔር ትእዛዝ በሙሴ አማካይነት ወደ ተቀበሏት ርስታቸው፣ ወደ ገለዓድ ምድር ተመለሱ።

10የሮቤልና የጋድ እንዲሁም የምናሴ ነገድ እኩሌታ በከነዓን ምድር ወዳለችው፣ ዮርዳኖስ አጠገብ ወደምትገኘው ገሊሎት ወደ ተባለች ስፍራ ሲደርሱ በወንዙ አጠገብ ግዙፍ መሠዊያ ሠሩ። 11የእስራኤላውያን ይዞታ በሆነችው በከነዓናውያን ምድር ወሰን በገሊሎት ላይ መሠዊያ መሥራታቸውን ሌሎቹ እስራኤላውያን በሰሙ ጊዜ፣ 12በእነርሱ ላይ ለመዝመት የእስራኤል ማኅበር ሁሉ በሴሎ ተሰበሰቡ።

13ስለዚህም እስራኤላውያን የካህኑ የአልዓዛርን ልጅ ፊንሐስን በገለዓድ ምድር ወደሚኖሩት ወደ ሮቤልና ወደ ጋድ እንዲሁም ወደ ምናሴ ነገድ እኩሌታ ላኩ፤ 14ከእርሱም ጋር እያንዳንዱን የእስራኤልን ነገድ የሚወክሉ ዐሥር አለቆች አብረው ላኩ፤ እነዚህም እያንዳንዳቸው ከእስራኤላውያን ጐሣዎች የተውጣጡ የየቤተ ሰቡ አለቆች ነበሩ።

15እነርሱም በገለዓድ ምድር ወዳሉት ወደ ሮቤላውያን፣ ወደ ጋዳውያንና ወደ ምናሴ ነገድ እኩሌታ ሄደው እንዲህ አሏቸው፤ 16“መላው የእግዚአብሔር ጉባኤ እንዲህ ይላል፤ ‘በእስራኤል አምላክ ላይ እንዲህ ያለ ክሕደት የፈጸማችሁት ለምንድን ነው? እግዚአብሔርን ከመከተልስ እንዴት ወደ ኋላ ትላላችሁ? እንዴትስ ዛሬ በእግዚአብሔር ላይ ዐምፃችሁ ለራሳችሁ መሠዊያ ትሠራላችሁ? 17በፌጎር የተሠራው ኀጢአት አይበቃንምን? ምንም እንኳ በእግዚአብሔር ጉባኤ ላይ መቅሠፍት ቢወርድም፣ እስከ ዛሬዪቱ ዕለት ድረስ ራሳችንን ከዚያች ኀጢአት አላነጻንም። 18እናንተ፣ አሁንም እግዚአብሔርን ከመከተል ወደ ኋላ ትላላችሁን?

“ ‘ዛሬ እናንተ በእግዚአብሔር ላይ ብታምፁ፣ እርሱ ደግሞ ነገ በመላው እስራኤል ጉባኤ ላይ ይቈጣል። 19የወረሳችኋት ምድር ረክሳ እንደ ሆነ፣ የእግዚአብሔር ማደሪያ ወደ ተተከለበት ወደ እግዚአብሔር ምድር መጥታችሁ ከእኛ ጋር ርስት ተካፈሉ፤ ነገር ግን ከአምላካችን ከእግዚአብሔር መሠዊያ በስተቀር ሌላ መሠዊያ ሠርታችሁ በእግዚአብሔርም ሆነ በእኛ ላይ አታምፁ። 20የዛራ ልጅ አካን፣ ዕርም የሆነውን ነገር በመውሰድ ኀጢአት ስለ ሠራ፣ በመላው የእስራኤል ጉባኤ ላይ ቍጣ አልመጣምን? በሠራው ኀጢአት የሞተውም22፥20 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠት ማለት ነው። እርሱ ብቻ አልነበረም።’ ”

21ከዚያም የሮቤልና የጋድ ነገዶች እንዲሁም የምናሴ ነገድ እኩሌታ ለእስራኤል ጐሣ መሪዎች እንዲህ ሲሉ መለሱላቸው፤ 22“ኀያሉ አምላክ፣ እግዚአብሔር! ኀያሉ አምላክ፣ እግዚአብሔር! እርሱ ያውቃል! እስራኤልም ይህን ይወቅ! ይህ የተደረገው በማመፅ ወይም ለእግዚአብሔር ባለመታዘዝ ከሆነ፣ ዛሬ አትማሩን! 23መሠዊያውን የሠራነው እግዚአብሔርን ከመከተል ወደ ኋላ ለማለት፣ የሚቃጠል መሥዋዕትና የእህል ቍርባን ልናሳርግበት ወይም የኅብረት መሥዋዕት22፥23 በዚህና በቍጥር 27 ላይ በትውፊት የሰላም መሥዋዕት በመባል ይታወቃል። ልናቀርብበት አስበን ከሆነ፣ ራሱ እግዚአብሔር ይበቀለን።

24“እኛማ ይህን ያደረግነው፣ ወደ ፊት ዘሮቻችሁ ለዘሮቻችን እንዲህ እንዳይሏቸው ፈርተን ነው፤ ‘ከእስራኤል አምላክ ከእግዚአብሔር ጋር ምን ግንኙነት አላችሁ? 25እናንት የሮቤልና የጋድ ልጆች፤ እግዚአብሔር ዮርዳኖስን በመካከላችን መለያ ድንበር ስላደረገው፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ድርሻ የላችሁም።’ ስለዚህ ዘሮቻችሁ፣ የእኛ ዘር እግዚአብሔርን እንዳይፈራ ሊያደርጉ ይችላሉ።

26“እኛም ‘እንነሣና መሠዊያ እንሥራ፤ የምንሠራው መሠዊያ ግን ለሚቃጠል መሥዋዕት ወይም ለሌላ መሥዋዕት ማቅረቢያ አይውልም’ ያልነው ለዚህ ነው። 27በሌላም በኩል የሚቃጠል መሥዋዕታችንን፣ ሌላውን ቍርባናችንንና የኅብረት መሥዋዕታችንን ይዘን በተቀደሰው ስፍራ እግዚአብሔርን እንደምናመልክ መሠዊያው በእኛና በእናንተ እንዲሁም በሚቀጥሉት ትውልዶች መካከል ምስክር ይሆናል። ስለዚህ ወደ ፊት ዘሮቻችሁ ዘሮቻችንን፣ ‘ከእግዚአብሔር ዘንድ ድርሻ የላችሁም’ ሊሏቸው አይችሉም።

28“እኛም፣ ‘ወደ ፊት እኛንም ሆነ ዘሮቻችንን እንዲህ የሚሉ ከሆነ፣ “እነሆ፤ አባቶቻችን የሠሩትን የእግዚአብሔርን መሠዊያ ምሳሌ ተመልከቱ፤ ይህ በእኛና በእናንተ መካከል ምስክር እንዲሆን እንጂ፣ ለሚቃጠል መሥዋዕትና ለሌላ መሥዋዕት ማቅረቢያ አይደለም” ብለን እንመልሳለን’ አልን።

29“በማደሪያው ድንኳን ፊት ካለው ከእግዚአብሔር መሠዊያ ሌላ፣ ለሚቃጠል መሥዋዕት ወይም ለእህል ቍርባን እንዲሁም ለሌላ መሥዋዕት ማቅረቢያ የሚሆን መሠዊያ በመሥራት ዛሬ በእግዚአብሔር ላይ እናምፅን? እርሱን ማምለካችንንም እንተውን? ይህ ከእኛ ይራቅ!”

30ካህኑ ፊንሐስና የእስራኤላውያን የጐሣ መሪዎች የነበሩት የማኅበረ ሰቡ አለቆች የሮቤል፣ የጋድና የምናሴ ወገኖች ያሉትን በሰሙ ጊዜ ተደሰቱ። 31የካህኑ የአልዓዛር ልጅ ፊንሐስም፣ የሮቤልን የጋድንና የምናሴን ወገኖች “በዚህ ነገር እግዚአብሔርን አልበደላችሁምና፣ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር መሆኑን ዛሬ ዐውቀናል፤ እነሆ እስራኤላውያንን ከእግዚአብሔር እጅ አድናችኋል” አላቸው።

32ከዚያም የካህኑ የአልዓዛር ልጅ ፊንሐስና መሪዎቹ፣ ከሮቤልና ከጋድ ወገኖች ጋር በገለዓድ ምድር ከተነጋገሩ በኋላ፣ ወደ ከነዓን ተመልሰው፣ ሁኔታውን ለእስራኤላውያን ነገሩ። 33እስራኤላውያንም ይህን ሲሰሙ ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ፤ ከዚያም የሮቤልና የጋድ ወገኖች የሚኖሩበትን አገር በጦርነት ለማጥፋት የመሄድን ነገር አላነሡም።

34የሮቤልና የጋድ ወገኖችም፣ እግዚአብሔር አምላክ ለመሆኑ ይህ በመካከላችን ምስክር ነው፤ በማለት መሠዊያውን “ምስክር” ብለው ጠሩት።

Thai New Contemporary Bible

โยชูวา 22:1-34

เผ่าทางด้านตะวันออกกลับบ้าน

1แล้วโยชูวาเรียกชุมนุมเผ่ารูเบน กาด และมนัสเสห์ครึ่งเผ่า 2และกล่าวกับพวกเขาว่า “ท่านทั้งหลายได้ทำทุกสิ่งตามที่โมเสสผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้าบัญชาไว้ และเชื่อฟังคำสั่งของข้าพเจ้าทุกอย่าง 3ท่านไม่ได้ละทิ้งพี่น้อง แต่ปฏิบัติหน้าที่ซึ่งพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงมอบหมายมาเป็นเวลานานจนถึงทุกวันนี้ 4บัดนี้พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงโปรดประทานการหยุดพักแก่พี่น้องของท่านตามที่ทรงสัญญาไว้ ฉะนั้นจงกลับไปยังบ้านของท่านในดินแดนอีกฟากหนึ่งของแม่น้ำจอร์แดนซึ่งโมเสสผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้าได้มอบให้ท่านแล้ว 5แต่จงตั้งใจปฏิบัติตามบทบัญญัติและกฎเกณฑ์ซึ่งโมเสสผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้าได้มอบไว้กับท่าน คือจงรักพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน จงดำเนินตามทางทั้งสิ้นของพระองค์ จงปฏิบัติตามพระบัญชา จงยึดมั่นในพระองค์ และปรนนิบัติพระองค์ด้วยสุดจิตสุดใจเถิด”

6โยชูวาจึงอวยพรพวกเขาและส่งกลับไปยังดินแดนของเขา 7(โมเสสได้มอบดินแดนบาชานให้เผ่ามนัสเสห์ครึ่งเผ่า ส่วนอีกครึ่งเผ่า โยชูวาได้มอบดินแดนทางฟากตะวันตกของแม่น้ำจอร์แดนให้ครอบครองร่วมกับพี่น้องเผ่าอื่นๆ) โยชูวาส่งพวกเขากลับบ้านและอวยพรพวกเขา 8พร้อมทั้งกล่าวว่า “จงกลับบ้านไปพร้อมกับทรัพย์สมบัติมากมาย ทั้งฝูงสัตว์ เงิน ทอง ทองสัมฤทธิ์ และเหล็ก พร้อมทั้งเสื้อผ้าอาภรณ์จำนวนมาก และจงแบ่งทรัพย์สมบัติที่ยึดมาจากศัตรูให้แก่พี่น้องของท่าน”

9ดังนั้นบรรดาคนเผ่ารูเบน กาด และมนัสเสห์ครึ่งเผ่าจึงจากชนอิสราเอลที่ชิโลห์ในคานาอัน เพื่อกลับสู่กิเลอาดอันเป็นดินแดนกรรมสิทธิ์ของตนซึ่งได้มาตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าได้บัญชาผ่านทางโมเสส

10เมื่อพวกเขามาถึงเกลีโลทใกล้แม่น้ำจอร์แดนในแผ่นดินคานาอัน ชนเผ่ารูเบน กาด และมนัสเสห์ครึ่งเผ่าได้สร้างแท่นบูชาขนาดใหญ่ขึ้นใกล้ๆ แม่น้ำจอร์แดนนั้น 11เมื่อชาวอิสราเอลได้ยินว่าพวกเขาได้สร้างแท่นบูชาขึ้นที่เกลีโลท ชายแดนคานาอันใกล้แม่น้ำจอร์แดนในเขตแดนอิสราเอล 12ประชากรอิสราเอลทั้งหมดก็มาชุมนุมกันที่ชิโลห์เตรียมรบกับพวกเขา

13ดังนั้นชนอิสราเอลจึงส่งฟีเนหัสบุตรปุโรหิตเอเลอาซาร์มายังดินแดนกิเลอาดเพื่อพบเผ่ารูเบน กาด และมนัสเสห์ครึ่งเผ่านั้น 14มีผู้นำสิบคนจากสิบเผ่าของอิสราเอลมาด้วย แต่ละคนเป็นหัวหน้าครอบครัวจากตระกูลต่างๆ ของชนอิสราเอล

15เมื่อพวกเขามาถึงกิเลอาดก็กล่าวกับเผ่ารูเบน กาด และเผ่ามนัสเสห์ครึ่งเผ่านั้นว่า 16“ชุมนุมประชากรทั้งสิ้นขององค์พระผู้เป็นเจ้ากล่าวว่า ‘เหตุใดท่านจึงทรยศต่อพระเจ้าแห่งอิสราเอลเช่นนี้? ท่านถือดีอย่างไรจึงบังอาจหันหนีจากองค์พระผู้เป็นเจ้าและสร้างแท่นบูชาของตัวเองเป็นการกบฏต่อพระองค์ในตอนนี้? 17ยังไม่เข็ดหลาบอีกหรือกับบาปของเราที่เปโอร์? ซึ่งเดี๋ยวนี้ก็ยังไม่ได้ชำระตนเองจากบาปนั้น ทั้งๆ ที่ภัยพิบัติตกแก่ชุมชนขององค์พระผู้เป็นเจ้า! 18และบัดนี้ท่านกำลังหันหนีจากองค์พระผู้เป็นเจ้าอีกหรือ?

“ ‘หากท่านกบฏต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าวันนี้ พรุ่งนี้พระองค์จะทรงพระพิโรธชุมชนอิสราเอลทั้งหมด 19หากแผ่นดินที่ท่านครอบครองเป็นมลทิน ก็จงข้ามมายังดินแดนขององค์พระผู้เป็นเจ้าที่ซึ่งพลับพลาขององค์พระผู้เป็นเจ้าตั้งอยู่ มาแบ่งปันดินแดนกับเรา แต่อย่าได้กบฏต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าหรือต่อพวกเราโดยสร้างแท่นบูชาของตนเอง นอกเหนือจากแท่นบูชาของพระยาห์เวห์พระเจ้าของเรา 20เมื่ออาคานบุตรเศราห์ทุจริตเรื่องของต้องอุทิศถวาย22:20 คำนี้ในภาษาฮีบรูหมายถึงสิ่งของหรือบุคคลที่ถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าแล้วไม่อาจเรียกคืนได้ มักจะต้องทำลายให้หมดสิ้นไป พระพิโรธตกอยู่แก่ชุมชนอิสราเอลทั้งหมดไม่ใช่หรือ? ไม่ใช่เขาคนเดียวที่ตายไปเพราะบาปนั้น’ ”

21แล้วชนรูเบน กาด และมนัสเสห์ครึ่งเผ่าจึงตอบบรรดาหัวหน้าตระกูลของอิสราเอลว่า 22“องค์ทรงฤทธิ์ พระเจ้าพระยาห์เวห์! องค์ทรงฤทธิ์ พระเจ้าพระยาห์เวห์! พระองค์ทรงทราบ! และอิสราเอลจงทราบเถิด! หากนี่เป็นการกบฏหรือไม่เชื่อฟังองค์พระผู้เป็นเจ้าวันนี้ก็อย่าไว้ชีวิตเราเลย 23หากเราสร้างแท่นบูชาของเราเอง เพื่อหันเหจากองค์พระผู้เป็นเจ้าและถวายเครื่องเผาบูชา เครื่องธัญบูชา หรือเครื่องสันติบูชาบนแท่น ก็ขอให้องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงจัดการกับเราด้วยพระองค์เองเถิด

24“เปล่าเลย! เราสร้างแท่นนี้ขึ้นมาก็เพราะเราเกรงว่าในอนาคตลูกหลานของท่านอาจจะกล่าวกับลูกหลานของเราว่า ‘ท่านมีสิทธิ์อะไรในการนมัสการพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอล? 25องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงตั้งแม่น้ำจอร์แดนเป็นพรมแดนกั้นระหว่างเรากับท่าน พวกท่าน คนรูเบนและกาด! ไม่มีสิทธิ์มีส่วนอะไรในองค์พระผู้เป็นเจ้า’ แล้วลูกหลานของท่านจะทำให้ลูกหลานของเราเลิกยำเกรงองค์พระผู้เป็นเจ้า

26“ฉะนั้นเราจึงกล่าวว่า ‘ให้เราเตรียมพร้อมและสร้างแท่นบูชาขึ้น ไม่ใช่สำหรับถวายเครื่องเผาบูชาหรือเครื่องบูชาต่างๆ’ 27แต่ตรงกันข้าม แท่นนี้จะเป็นพยานระหว่างเรากับท่านและคนรุ่นต่อๆ ไปว่าเราจะนมัสการองค์พระผู้เป็นเจ้าด้วยเครื่องเผาบูชา เครื่องสันติบูชา และเครื่องถวายต่างๆ ของเราที่สถานนมัสการของพระองค์ แล้วในอนาคตลูกหลานของท่านไม่อาจพูดกับลูกหลานของเราว่า ‘ท่านไม่มีสิทธิ์มีส่วนอะไรในองค์พระผู้เป็นเจ้า’

28“และพวกเรากล่าวว่า ‘หากพวกเขากล่าวเช่นนี้กับเราหรือลูกหลานของเรา เราก็จะตอบว่าดูแท่นบูชาจำลองขององค์พระผู้เป็นเจ้าซึ่งบรรพบุรุษของเราได้สร้างขึ้นสิ ไม่ใช่สำหรับถวายเครื่องบูชาหรือเครื่องเผาบูชา แต่เป็นพยานระหว่างเรากับท่าน’

29“ขอให้การนั้นห่างไกลจากเราเถิด ในวันนี้เราจะไม่กบฏต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าหรือหันเหจากพระองค์ โดยสร้างแท่นบูชาสำหรับเครื่องเผาบูชา เครื่องธัญบูชา หรือเครื่องบูชาต่างๆ แทนที่แท่นบูชาของพระยาห์เวห์พระเจ้าของเราซึ่งตั้งอยู่หน้าพลับพลาของพระองค์”

30เมื่อปุโรหิตฟีเนหัสและผู้นำทั้งปวงของชุมชนซึ่งเป็นหัวหน้าตระกูลต่างๆ ของชนอิสราเอลได้ยินคำกล่าวจากเผ่ารูเบน กาด และมนัสเสห์เช่นนี้ก็พอใจ 31ปุโรหิตฟีเนหัสบุตรเอเลอาซาร์ตอบชนรูเบน กาด และมนัสเสห์ว่า “วันนี้เรารู้แล้วว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าสถิตกับพวกเรา เพราะว่าท่านไม่ได้ทำผิดต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าในเรื่องนี้ บัดนี้ท่านได้ช่วยชนอิสราเอลให้พ้นจากพระหัตถ์ขององค์พระผู้เป็นเจ้า”

32แล้วปุโรหิตฟีเนหัสบุตรเอเลอาซาร์และบรรดาผู้นำจึงกลับจากการพบกับชนเผ่ารูเบนและกาดในกิเลอาด มายังคานาอันและรายงานชนอิสราเอล 33พวกเขาพากันดีใจที่ได้ฟังเรื่องราวและสรรเสริญพระเจ้า และพวกเขาไม่ได้พูดกันถึงเรื่องจะสู้รบเพื่อทำลายดินแดนของเผ่ารูเบนและกาดอีก

34ชนเผ่ารูเบนและกาดตั้งชื่อแท่นนั้นว่า “พยานระหว่างเราว่าพระยาห์เวห์ทรงเป็นพระเจ้า”