ኢያሱ 19 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 19:1-51

ለስምዖን ነገድ የተመደበው ድርሻ

19፥2-10 ተጓ ምብ – 1ዜና 4፥28-33

1ሁለተኛው ዕጣ ለስምዖን ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ ርስታቸውም ዙሪያውን በይሁዳ ነገድ ርስት የተከበበ ነበር፤ 2ይህም የሚከተሉትን ያካትታል፤

ቤርሳቤህ፣ ሤባ፣ ሞላዳ፣ 3ሐጸር ሹዓል፣ ባላ፣ ዔጼም፣ 4ኤልቶላድ፣ በቱል፣ ሔርማ፣ 5ጺቅላግ፣ ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሳ፣ 6ቤተ ለባኦትና ሻሩሔን ነበሩ፤ እነዚህ ዐሥራ ሦስት ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።

7ዐይን፣ ሪሞን፣ ዔቴርና ዓሻን የተባሉት አራት ከተሞቻቸውና መንደሮቻቸው፣ 8ደግሞም እስከ ባዕላትብኤር ወይም ኔጌብ ውስጥ እስካለው እስከ ራማት ድረስ ባሉት ከተሞች ዙሪያ የሚገኙት መንደሮች ሁሉ ከእነዚሁ ጋር ይጠቃለላሉ።

እንግዲህ በየጐሣው የተደለደለው የስምዖን ነገድ ርስት ይህ ነበር። 9የይሁዳ ነገድ የያዘው ርስት እጅግ ሰፊ ስለ ነበር፣ ከይሁዳ ነገድ ድርሻ ተከፍሎ ለስምዖን ነገድ በርስትነት ተሰጠ። ከዚህ የተነሣም የስምዖን ነገድ በይሁዳ ነገድ ድርሻ ርስት ሊካፈል ቻለ።

ለዛብሎን ነገድ የተመደበው ድርሻ

10ሦስተኛው ዕጣ ለዛብሎን ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤

የርስታቸውም ድንበር እስከ ሣሪድ ይደርሳል። 11ወደ ምዕራብም በመሄድ በመርዓላ በኩል ያልፋል፤ ደባሼትን ተጠግቶም በዮቅንዓም አጠገብ እስካለው ወንዝ ድረስ ይዘልቃል። 12ከሣሪድም ወደ ምሥራቅ በመታጠፍ፣ የፀሓይ መውጫ ወደ ሆነው አገር ወደ ኪስሎትታቦር በመዝለቅ እስከ ዳብራት ሄዶ ወደ ያፊዓ ያቀናል። 13ከዚያም ወደ ምሥራቅ በመቀጠል፣ ወደ ጋትሔፍርና ወደ ዒትቃጺን ይዘልቃል፤ ከዚያ ደግሞ ወደ ሪሞን በመሄድ ወደ ኒዓ ይታጠፋል። 14በስተ ሰሜንም በኩል ወደ ሐናቶን ይዞርና በይፍታሕኤል ሸለቆ ላይ ይቆማል።

15ደግሞም ቀጣትን፣ ነህላልን፣ ሺምሮንን፣ ይዳላንና ቤተ ልሔምን ይጨምራል፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ሁለት ከተሞች ናቸው።

16እነዚህ ሁሉ ለዛብሎን ነገድ ርስት ሆነው ለየጐሣ ለየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮቻቸው ነበሩ።

ለይሳኮር ነገድ የተመደበው ድርሻ

17አራተኛው ዕጣ ለይሳኮር ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ 18ምድራቸውም የሚከተሉትን ያካትታል፤

ኢይዝራኤል፣ ከስሎት፣ ሱነም፣ 19ሐፍራይም፣ ሺኦን፣ አናሐራት፣ 20ረቢት፣ ቂሶን፣ አቤጽ፣ 21ሬሜት፣ ዐይንጋኒም፣ ዐይንሐዳ እንዲሁም ቤትጳጼጽ።

22ድንበራቸውም ታቦርና፣ ሻሕጹማን፣ ቤትሳሚስን ይነካና በዮርዳኖስ ላይ ያቆማል።

እነዚህ ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ስድስት ከተሞች ናቸው።

23እነዚህ ለይሳኮር ነገድ ርስት ሆነው ለየጐሣ ለየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮቻቸው ነበሩ።

ለአሴር ነገድ የተመደበው ድርሻ

24አምስተኛ ዕጣ ለአሴር ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ 25ምድራቸውም የሚከተሉትን ያካትታል፤

ሔልቃት፣ ሐሊ፤ ቤጤን፣ አዚፍ፣ 26አላሜሌክ፣ ዓምዓድ እንዲሁም ሚሽአል። ድንበሩ በስተ ምዕራብ ቀርሜሎስንና ሺሖርሊብናትን ይነካል፤ 27ከዚያም በምሥራቅ በኩል ወደ ቤትዳጎን ይመለስና ዛብሎንንና የይፍታሕኤልን ሸለቆ ይዞ፣ ካቡልን በስተ ግራ በመተው በሰሜን በኩል ወደ ቤትዔሜቅና ወደ ንዒኤል ይቃናል። 28በመቀጠልም ወደ ዔብሮን19፥28 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን ጥቂት ቅጆች ኢያ 21፥30 ይመ፣ አብዩን ይላሉ።፣ ወደ ረአብ፣ እንዲሁም ወደ ሐሞንና ወደ ቃና ሽቅብ ወጥቶ እስከ ታላቁ ሲዶና ይደርሳል። 29ድንበሩ ወደ ራማ ከዞረ በኋላ ወደ ተመሸገው ወደ ጢሮስ ከተማ ታጥፎ ወደ ሖሳ ይመለስና በአክዚብ በኩል ሜድትራኒያን ባሕር ደርሶ ይቆማል፤ 30ይህም የዑማን፣ የአፌቅንና የረአብን ምድር ይጨምራል።

በዚህም ሃያ ሁለት ከተሞችና መንደሮቻቸው ይገኛሉ።

31እነዚህ ለአሴር ነገድ ሆነው በየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮቻቸው ነበሩ።

ለንፍታሌም ነገድ የተመደበው ድርሻ

32ስድስተኛው ዕጣ ለንፍታሌም ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤

33ድንበራቸውም ከሔሌፍና በጸዕነኒም ካለው ከትልቁ የወርካ ዛፍ ይነሣና በአዳ ሚኔቄብና በየብኒኤል ዐልፎ ወደ ለቁም በመምጣት ዮርዳኖስ ላይ ይቆማል፤ 34ድንበሩ በአዝኖት ታቦር ያልፍና ወደ ምዕራብ በመታጠፍ ሑቆቅ ላይ ይቆማል፤ ይኸው ድንበር በደቡብ ዛብሎንን፣ በምዕራብ አሴርን፣ በምሥራቅ ዮርዳኖስን ይነካል19፥34 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ነገር ግን የዕብራይስጡ ቅጅ ምሥራቅ ይሁዳንና ዮርዳኖስን ይከብባል ይላል።

35የተመሸጉትም ከተሞች እነዚህ ናቸው፤ ጺዲም፣ ጼር፣ ሐማት፣ ረቃት፣ ኬኔሬት፣ 36አዳማ፣ ራማ፣ አሦር፣ 37ቃዴስ፣ ኤድራይ፣ ዐይንሐጾር፣ 38ይርኦን፣ ሚግዳልኤል፣ ሖሬም፣ ቤትዓናትና ቤትሳሚስ።

እነዚህ ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ዘጠኝ ከተሞች ናቸው።

39እነዚህ ለንፍታሌም ነገድ ርስት ሆነው በየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮች ነበሩ።

ለዳን ነገድ የተመደበው ድርሻ

40ሰባተኛው ዕጣ ለዳን ነገድ በየጐሣው ወጣ፤ 41የወረሱትም ምድር የሚከተሉትን ያካትታል፤

ጾርዓ፣ ኤሽታኦል፣ ዒርሼሜሽ፣ 42ሸዕለቢን፣ ኤሎን፣ ይትላ፣ 43ኤሎን፣ ተምና፣ አቃሮን፣ 44ኢልተቄ፣ ገባቶን፣ ባዕላት፣ 45ይሁድ፣ ብኔብረቅ፣ ጋትሪሞን፣ 46ሜያርቆንና በኢዮጴ ፊት ለፊት ያለው ርቆን።

47ነገር ግን የዳን ዘሮች ርስታቸው አልበቃቸውም፣ ወደ ሌሼም ወጥተው አደጋ በመጣል ያዟት፤ ሰዎቹንም በሰይፍ ስለት ፈጅተው ይዞታቸው አደረጓት፤ በዚያው ሰፈሩ፤ ስሟንም ለውጠው በአባታቸው ስም ዳን አሏት።

48እነዚህ ለዳን ነገድ ርስት ሆነው በየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮች ነበሩ።

ለኢያሱ የተመደበው ድርሻ

49እስራኤላውያን ድርሻ ድርሻቸውን ከያዙ በኋላ፣ ለነዌ ልጅ ለኢያሱ በመካከላቸው ርስት ሰጡት፤ 50እግዚአብሔር ባዘዘውም መሠረት በኰረብታማው የኤፍሬም ምድር የምትገኘውን ተምናሴራ የምትባለውን የፈለጋትን ከተማ ሰጡት፤ እርሱም ከተማዪቱን ሠራ፤ መኖሪያውም አደረጋት።

51እንግዲህ ካህኑ አልዓዛር፣ የነዌ ልጅ ኢያሱና የእስራኤል ነገድ የየጐሣ መሪዎች ሴሎ ላይ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ፣ በእግዚአብሔር ፊት ዕጣ ያደላደሉት ርስት ይህ ነው፤ የምድሪቱንም አከፋፈል በዚህ ሁኔታ ፈጸሙ።

O Livro

Josué 19:1-51

O território de Simeão

(1 Cr 4.28-33)

1A terra dada à tribo de Simeão:

A tribo de Simeão recebeu o seguinte lote de terra, incluindo parte da que fora previamente dada a Judá. 2A porção doada incluía as seguintes cidades com as localidades da sua jurisdição:

Berseba, Seba, Molada, 3Hazar-Sual, Balá, Ezem, 4Eltolade, Betul, Horma, 5Ziclague, Bete-Marcabote, Hazar-Susa, 6Bete-Lebaote, Saruem; treze cidades com as suas aldeias.

7Aim, Rimom, Eter, e Asã; quatro cidades com as suas aldeias. 8As cidades mais para o sul, como Baalate-Beer (também conhecida por Rama no Negueve) foram igualmente dadas à tribo de Simeão.

9Portanto, a herança que a tribo de Simeão recebeu veio parcialmente daquilo que tinha anteriormente sido dado a Judá, visto que o lote de Judá foi considerado demasiado grande para esta tribo.

O território de Zebulão

10A terra dada à tribo de Zebulão:

A terceira tribo a receber a sua concessão foi Zebulão. O seu limite começava a sul de Saride. 11Dali rodava para oeste, indo passar perto de Marala e de Dabesete, até que atingia a leste o ribeiro de Jocneão. 12Na outra direção a linha de demarcação ia para leste até à beira de Quislote-Tabor, e dali para Daberate e Jafia. 13Depois continuava para o nascente, passando Gate-Hefer, Ete-Cazim e Rimom, voltando para Neá. 14O limite norte de Zebulão era por Hanatom e terminava no vale de Ifta-El.

15-16As cidades destas áreas, além das já mencionadas, eram Catate, Naalal, Simrom, Idala e Belém, com os seus respetivos arredores. No total eram doze as localidades de Zebulão.

O território de Issacar

17A terra dada à tribo de Issacar: A quarta tribo a herdar terra foi Issacar. 18O seu território incluía as seguintes cidades:

Jezreel, Quesulote, Sunem, 19Hafaraim, Siom, Anacarate, 20Rabite, Quisiom, Ebes, 21Remete, En-Ganim, En-Hada, Bete-Pazez,

22-23Tabor, Saazima e Bete-Semes; dezasseis cidades ao todo, cada uma com as localidades dos seus arredores. A linha limite de Issacar terminava no rio Jordão.

O território de Aser

24A terra dada à tribo de Aser:

A quinta tribo a receber terra foi Aser. 25Os seus limites incluíam estas cidades: Helcate, Hali, Beten, Acsafe, 26Alameleque, Amade e Misal. A linha balizadora a ocidente ia do Carmelo até Sior-Libnate, 27infletia para leste, para Bete-Dagom, e chegava a Zebulão, ao vale de Ifta-El, correndo a norte de Bete-Emeque e de Neiel. Depois passava a leste de Cabul, 28de Ebrom, Reobe, Hamom e Caná, até à grande Sídon. 29Então a linha divisória dirigia-se na direção de Ramá e da cidade fortificada de Tiro e chegava ao mar Mediterrâneo em Hosa. O território incluía também Maalabe, Aczibe, 30-31Umá, Afeque e Reobe.

Um total de vinte e duas cidades, mais as aldeias ao redor.

O território de Naftali

32A terra dada à tribo de Naftali:

A sexta tribo a receber a sua herança foi a tribo de Naftali. 33-34A sua demarcação começava em Judá no carvalho de Zaananim e estendia-se através de Adami-Nequebe, de Jabneel e de Lacum, acabando no rio Jordão. O limite ocidental começava perto de Helefe e corria junto de Azenote-Tabor; junto de Hucoque juntava-se, coincidindo com a demarcação de Zebulão a sul, com a de Aser a poente e com o rio Jordão a oriente.

35As cidades fortificadas que se incluíam neste território eram: Sidim, Zer, Hamate, Racate, Quinerete, 36Adama, Ramá, Hazor, 37Quedes, Edrei, En-Hazor, 38-39Irom, Migdal-El, Horem, Bete-Anate e Bete-Semes.

Ao todo, eram dezanove cidades, mais as aldeias ao redor.

O território de Dan

40A terra dada à tribo de Dan: A última a receber terra foi Dan. 41As cidades que se incluíam na sua área eram:

Zora, Estaol, Ir-Semes, 42Saalabim, Aijalom, Itla, 43Elom, Timna, Ecrom, 44Elteque, Gibetom, Baalate, 45Jeude, Bene-Beraque, Gate-Rimom, 46Me-Jarcom, Racom, e também o território junto de Jope.

47Mas parte deste território mostrou-se difícil de ser conquistado; por isso, a tribo de Dan capturou a cidade de Lesem, matou a população e passou a viver ali, dando à cidade o nome de Dan, o nome do pai da tribo.

48Este foi o território que ficou a pertencer à tribo de Dan, incluindo cidades e aldeias.

O território de Josué

49Foi desta forma que a terra foi repartida por todas as tribos, segundo as demarcações aqui indicadas. Além disso, a nação de Israel decidiu atribuir um pedaço especial do território a Josué; 50pois o Senhor dissera que poderia ficar com qualquer cidade que pretendesse; com efeito, ele escolheu Timenate-Sera na região das colinas de Efraim, a qual reconstruiu, passando a viver ali.

51Eleazar, o sacerdote, Josué e os chefes das tribos de Israel controlaram o ato em que foram tiradas à sorte, na presença do Senhor, as diversas porções em que a terra foi dividida. Isto realizou-se à entrada da tenda do encontro em Silo.